Gospel

@gospelfornation


ትክክለኛውንና እውነተኛውን ወንጌል የምስራች ለአለም ሁሉ የሚያበራውን #ኢየሱስ ብቻ ሚሰበክበት
contact us @tsegamulat

Gospel

23 Oct, 06:35


በተሞላ ነገር ላይ ለመጨመር መሞከር ትርፉ ማፍሰስ ነው!ዓለማዊነት እና ምኞቱ  የማይዘልቀን በእግዚአብሔር ቃል ስንሞላ ነው!ጌታ ኢየሱስ የዲያብሎስን ፈተና አሸንፎ ያሳየን ጥቅስ እየጠቀሰ ነው...''እንዲህ ተብሎ ተፅፏል''...።ጌታን ለመምሰል የሚያስፈልገን ፀጋ እና ሁሉ ነገር ተሰቶን ሳለ ደካማ የሆነው ለምን ይመስላችኃል?ዋርካ ትልቅ ዛፍ ከመሆኑ በፊት ዘር ነበር!ያለዘር ዕድገት ሆነ ፍሬ የለም!ስለዚህ ነው ጳውሎስ እኔ ተከልኩ አጵሎስ አጠጣ እግዚአብሔር ያሳድጋል ያለው።እምነት በቃሉ ነው ጊዜ ይጠብቅ እንጂ ዕድገትም በቃሉ ነው!!
ያለ እናት ጡት ወተት ህፃን እንዴት ያድግ ይሆን??

“ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”
  — 1ኛ ጴጥሮስ 2፥2-3

ዓለማዊ ምኞትን የምናሸንፈው በትግል ሳይሆን ቃሉን በመሞላት ነው!!

© ጌዴዎን ጡሚሶ (ዶ/ር)

Gospel

21 Oct, 10:16


ዛሬም ይቀጥላል

Gospel

17 Oct, 13:54


በብዙ ከተጠቀምንበት ፤ አኹንም እየተጠቀምንበት ካለው ከተወደደው ወንደማችንና አገልጋይ ፋሲል ጥጋቡ (ፋዮ) ጋር ልዩ የስልጠና ጊዜ ተዘጋጅትዋል፡፡ አንገብጋቢ በሆኑ ሁለት ርዕሰ ጉዳዮችና ተያያዥ ሀሳቦች ጋር ስልጠና ይሰጠናል፡፡ እግዚአብሔር መልካም ጊዜ ይሰጠናል ታዳጊዎችና ወጣቶች በፍፁም አይቀርም፡፡

Gospel

11 Oct, 08:19


ነገ መልካም ጊዜ ይኖረናል ይምጡና ይካፈሉ
ግጥሞች
ወግ
ፅሁፎች
የአንድ ሰው ጭውውት እና ዝማሬ አሰናድተን እንጠብቃኋለን

Gospel

08 Oct, 09:54


ወርሃዊው መርሃ ግብራችን ይቀጥላል

Gospel

05 Oct, 19:07


https://youtu.be/v7iOC9FI7JA

Gospel

26 Sep, 10:31


...ፈቃድህ...

ሊያነግሱት ፈልገው - ሊጠግቡ እንጀራ
ሊበሉ ሊጠጡ - እንዳይጎል ጎተራ
ሹመት ቢክቡለት - ከላዪ ደርበው
ከመንበሩ ወጥቶ - ዘውዱን እንዲያጠልቀው
"ካባህንም ደርብ - በትርህን ጨብጥ
ከቤተመንግስቱ - ከዙፋን ተቀመጥ"
ብለው ቢማፀኑት - ሊገዙለት ወደው
ክብር ካሉት ይልቅ - መስቀሉን ቢወደው
መራራውን ፅዋ - ከንግስና መርጦ
አብን አከበረው - ፈቀዱን አብልጦ
ደስታው ያ ነበረ - ክብሩ ያ ነበረ
በመስቀሉ ስቃይ - የልቡ ሰመረ
ወዳጆቹን እንኳ - ግራ የገባቸው
እንጀራ ሲሰጡት - ጠገብኩ ሚላቸው
ቢጠረጥሩትም - ከሠው እንዲበላ
መብሉ መጠጡ - የነፍሱ ተድላ
ዓላማው ስኬቱ - አይደለም ምቾቱ
የአባቱ ፈቃድ - ነበረ ምኞቱ

שמיים shamayim 🌄

Gospel

22 Sep, 10:40


ልጅህ አይደለሁ?
ወላጅ የሌለው፣ አሳዳጊም የበደለው ወደል መስዬ በጎዳና እንዲህ ስጎፈላ ለምን ዝም ትላለህ? ከስርዓትህ ስፈታ፣ አላዋቂነትም ሲፋንንብኝ አባት አይደለህ ለምን ገረፈህ አትመልሰኝም? ዝምታህ እኮ ያነቅዛል። በኖራ የተለሰነ መቃብር ኾኜ ሳሸረግድ በትርህን አንስተህ ስንፍናዬን ከላዬ ስለምን አትፍቅም? ከጉረኖ የወጣ፤ እረኛም የሌለው በገ ይመስል ስቅበዘበዝ ድምጽህን አንስተህ ስለምን ተመለስ አትለኝም? ግኡዝ እንኳ ይታዘዝሃል እኮ። ትዕቢት ልቤን ወጥሮ ሊያደቀኝ ሲቋምጥ ከልካይን ስለምን አትልክም?

በእርኩሰት ለሚዛብር፣ በአመጻም ለሚሰባ ሰው ከዝምታህ የከፋ ቅጣት ምን አለ? አባት አይደለህ ቁንጥጫህ የት ነው? ወንድም ጋሼ አይደለህ ኩርኩምህ ወዴት ነው? ተግሳጽህ ቅዱስ ነው በደልን ያርቃል። ዝምታህ ግን ያጎድላል!!! ለካ ቁጣህ ምሕረት ነው?! ለካ ዘለፋህ ርኅራሄ ነው! ለካ ዝምታህ ለራስ መተው ነው! መገረፍ እኮ የልጅ ነው። ዲቃላ ነው ማይቀጣ። ዕብ 12: 7-8

አልቃሻው ነብይ እንዳለ ፈጽመኽ ካልጣልክ በቀር መመለስ ያንተ ነው። ሰቆ 5:22። ወዳንተ ስትመልሰን ዘመናችን ይታደሳል። እንደ ተወደዱ ልጆችም መልሰን በአምላክትህ ሐሴት እናደርጋለን። ተግሳጽህ ሕያዋን ያደርገናል። እናም አባት ሆይ ግርዱን በበትርህ አስወግደህ፣ ብዙም ያፈራ ዘንድ ግንዱን ገረዘህ ለሕይወት አትርፈን!

© ኢብሳ ቡርቃ

Gospel

21 Sep, 12:53


The greatest sin of Christ-rejecters and the most damning work of Satan is #misrepresentation of the truth and its consequent deception.

~John MacArthur

Gospel

18 Sep, 13:44


‼️‼️‼️

Gospel

17 Sep, 05:32


ዛሬ!!!!

Gospel

16 Sep, 05:08


በተለያዩ ዘመናት ክርስቲያኖች የክርስቶስን መስቀል ገሸሽ ከማድረግ ይልቅ በሞቱ ሊመስሉት ምርጫቸው አድርገው የፅዮኑን ጉዞ መጓዛቸው እሙን ነው። በዚህ ዘመን ያለን የክርስቶስ ተከታይ የሆንን ክርስቲያኖች ‹‹ይህችን ፅዋ›› ለመሸሽና "መስቀል አልባ ክርስትና" ለመለማመድ የምንጠር ቆም ብለን ማሰብ ይጠበቅብናል፡፡ መስቀሉ ወደ ክብር የሚወስድ መንገድ ነው። ቃሉስ “መስቀሉን ተሸክሞ የማይከተለኝ ለኔ ሊሆን አይገባውም ”
ማቴ10፡ 38 (ዓ.መ.ት) አይደል የሚለው፡፡

"ይህች ፅዋ" የተሰኘው የመድረክ ስራም ይሄንን እውነት ለማውሳት የሚጥር ነው። ልዝብ የሆነውን የክርስቶስ መስቀል ተሸክሞ የሚጓዝ አማኝ ያለ ጥርጥር ከጽዮን መድረሱ አይቀርም።

የምትችሉ ነገ ማክሰኞ በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ከ11:00 ጀምሮ እንገናኝ ።

Gospel

06 Sep, 20:05


"ምንም ኣትስጡኝ ወይም ከሰጣቹኝ የመጽሃፍ ቅዱሱን ኢየሱስ ስጡኝ"
R.C Sproul

Gospel

13 Aug, 07:22


የዝማሬ የአምልኮ ምሽት
ዛሬ ከ11:30 ጀምሮ
አይቀርም

Gospel

03 Aug, 10:25


ሌላ ድግስ
የዛሬ ሳምንት 26ኛው ወርሃዊው የስነፅሁፍ ምሽታችን ይደረጋል ኑ አብረውን ያሳልፉ

Gospel

12 Jul, 05:33


አይቀርም

Gospel

29 Jun, 09:30


አንድ ሁለት እያለ 13ኛው አመት ላይ ደርሷል .... ዘንድሮ ግደል በሚል መሪ ቃል ይከበራል።

ኑ አብረን እናሳልፍ።