Последние посты Ethiopia Insider (@ethiopiainsidernews) в Telegram

Посты канала Ethiopia Insider  

Ethiopia Insider
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
15,399 подписчиков
651 фото
40 видео
Последнее обновление 06.03.2025 19:14

Последний контент, опубликованный в Ethiopia Insider на Telegram

Ethiopia Insider

06 Mar, 17:18

1,313

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በመንፈቅ ዓመት ውስጥ ከ6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የግብር ዕዳ መሰብሰቡን ገለጸ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ብቻ ከ6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የግብር ዕዳ መሰብሰቡን አስታወቀ። ቢሮው ያለባቸውን “ከ3.2 ቢሊዮን ብር በላይ የግብር ዕዳ ለመክፈል ፈቃደኛ አልሆኑም” ያላቸውን 62 ግለሰቦች ሀገር እንዳይወጡ ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ስም ዝርዝራቸውን ማስተላለፉን ገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 በጀት ዓመት ለመሰብሰብ ያቀደው ጠቅላላ የገቢ መጠን 230 ቢሊዮን ብር ነው።

የከተማ አስተዳደሩ በዘንድሮው በጀት ዓመት ከታክስ ገቢዎች ለማግኘት ያቀደው 150.1 ቢሊዮን ብር ሲሆን፤ እስከ መንፈቅ ዓመት 111.5 ቢሊዮን ብር ማግኘት መቻሉን ከሁለት ሳምንት በፊት በተካሄደው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ይፋ ተደርጓል።

የከተማይቱ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በዚሁ ጉባኤ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት፤ የከተማይቱ አስተዳደር “የታክስ መሰረትን በማስፋት” እንዲሁም “ብክነት እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል” የገቢ መጠኑን ማሳደግ መቻሉን ገልጸው ነበር።

ከንቲባዋ ለዚህ በማሳያነት የጠቀሱት፤ ለግብር ስረዛ የቀረቡ ዶክመንቶች ላይ ባለፉት ስድስት ወራት በተደረገ ፍተሻ “10 ቢሊዮን ብር ማዳን መቻሉን” ነው።

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 27፤ 2017 በይፋዊ የፌስ ቡክ ገጹ ባወጣው መረጃ፤ ባለፈው መንፈቅ ዓመት ውስጥ ከ6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የግብር ዕዳ መሰብሰቡን ገልጿል።

🔴ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15272/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

06 Mar, 15:28

2,193

የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በሁለት ክሶች ጥፋተኛ ተባሉ 

የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጸጋዬ ቱኬ፤ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረቡባቸው ሁለት ክሶች ጥፋተኛ ተባሉ። ፍርድ ቤቱ ትላንት ረቡዕ የካቲት 26፤ 2017 በዋለው ችሎት፤ በተመሳሳይ የክስ መዝገብ የተከሰሱ ሌሎች አራት ተከሳሾች ላይም የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ በተከሳሾቹ ላይ ያስተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ፤ “ስልጣንን ያለአግባብ በመገልገል”፣ “የመንግስትን ስራ በማያመች ሁኔታ በመምራት”፣ “የማይገባ ጥቅም በማግኘት ጉቦ በማቀባበል” እና “የሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት” የሙስና ወንጀል ነው። የሲዳማ ክልል ዐቃቤ ህግ፤ የቀድሞውን ከንቲባ ጨምሮ በአራት ተከሳሾች ላይ ክስ የመሰረተው ባለፈው ዓመት ሚያዝያ ወር ነበር።

ከአቶ ጸጋዬ ጋር በአንድ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ውስጥ የቀድሞው ከንቲባ ሚስት አባት የሆኑት አቶ ተሰማ ዳንጉሼ ይገኙበታል። የሀዋሳ ከተማ ኮንስትራክሽን እና ቤቶች ልማት መምሪያ ምክትል ኃላፊ የነበሩት አቶ ታሪኩ ታመነ ሌላኛው ተከሳሽ ሲሆኑ፤ እርሳቸው በሚመሩት ቢሮ ውስጥ መሀንዲሶች የነበሩት አቶ ታፈሰ ቱናሻ እና አቶ ሰይፉ ደሌሳም በዚሁ የክስ መዝገብ ስር ተካትተዋል።

የቀድሞው የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና ሁለቱ መሀንዲሶች ላይ የክልሉ ዐቃቤ ህግ ክስ ያቀረበው፤ በከተማ ተቋማዊነት እና መሰረተ ልማት ፕሮግራም (urban institutional and infrastructure development program) ስር ሲከናወኑ ከቆዩ አራት ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ ነው።

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15267/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

06 Mar, 04:33

3,323

ኢትዮጵያ በሩብ ዓመት ውስጥ ብቻ ከጥይት ሽያጭ 30 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ገቢ ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ

ኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ ለውጭ ሀገራት ከሸጠቻቸው ጥይቶች፤ “ከ30 ሚሊዮን ዶላር ያላነሰ” ገቢ ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ሀገሪቱ ለውጭ ሀገር ገበያ የሚቀርቡ ክላሽ፣ ስናይፐር፣ ብሬን፣ ዲሽቃ፣ ታንክ እና ሁሉንም አይነት መድፎች “የማምረት አቅም ያለው” ፋብሪካ መገንባቷንም አብይ አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ይህን ያሉት፤ በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ በቶኬ ኩታዬ ወረዳ የሚገኘውን የሆሚቾ ጥይት ፋብሪካ ትላንት ረቡዕ የካቲት 26፤ 2017 በጎበኙበት ወቅት ነው።

አብይ በዚሁ ወቅት በሰጡት ገለጻ፤ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ውስጥ “በተወሰነ ደረጃ” ጥይት እና መሳሪያ “የማምረት ሙከራዎች” እንደነበሩ አስታውሰዋል።

በ2015 ዓ.ም በአምቦ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው የሆሚቾ አሙኔሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ውስጥ ተከላው የተጀመረው ዘመናዊ ፋብሪካ፤ “ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ” ጥይቶችን እና የተለያዩ አይነት የጦር መሳሪያዎችን ወደ ማምረት መሸጋገሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ይፋ አድርገዋል።

በ2014 ዓ.ም “ጥይት እንገዛ ነበር” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፤ “እነዚህን አይነት ነገሮች ከመግዛት ወጥተን፣ አምርተን፣ ለሌሎች የምንሸጥ ሀገር መሆናችን እና በጣም በአጭር ጊዜ ውስጥ ይሄ አቅም ተገንብቶ በማየቴ በጣም ከፍተኛ ክብር እና ደስታ ይሰማኛል” ሲሉ ስሜታቸውን አጋርተዋል።

🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15258/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

04 Mar, 10:22

4,132

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሻሻለው ህገ መንግስት “ተፈጻሚ እንዳይሆን”፤ ለሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ አቤቱታ ቀረበ 

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት የዛሬ ሁለት ሳምንት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤው ላይ ያጸደቀው የክልሉ ህገ መንግስት ማሻሻያ፤ “የኢፌዲሪን ህገ መንግስት የሚቃረን ነው” ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲ የምክር ቤት አባላት “ተፈጻሚ እንዳይሆን” አቤቱታ አቀረቡ።

የምክር ቤት አባላቱ አቤቱታቸውን ያቀረቡት ለፌደራል የሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ነው። የሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ፤ በተለያዩ አካላት የሚቀርቡለትን ሕገ መንግስታዊ ጉዳዮችን የማጣራት ስልጣን ያለው ነው።

ጉባኤው በሚያደርገው ማጣራት መሰረት ህገ መንግስቱን መተርጎም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ለፌደሬሽን ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል። አጣሪ ጉባኤው፤ በተሻሻለው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ህገ መንግስት ላይ ትርጓሜ የሚጠይቅ አቤቱታ እንደቀረበለት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጧል።

ይህን አቤቱታ በትላንትናው ዕለት ያቀረቡት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት የቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦዴፓ) ተመራጭ የሆኑት አቶ አመንቴ ገሺ፣ አቶ ዮሐንስ ተሰማ እና ተስፋሁን ኪሉ ናቸው። ሶስቱ የቦዴፓ የክልል ምክር ቤት ተመራጮች የህገ መንግስት ትርጉም ከጠየቁባቸው ጉዳዮች ውስጥ፤ የክልሉን ምክር ቤት መቀመጫ ቁጥር ማደግን የተመለከተው ይገኝበታል።

በ1995 ዓ.ም የወጣው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ህገ መንግስት፤ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ቁጥር ከ100 እንደማይበልጥ ይደነግጋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት የካቲት 11 ባካሄደው መደበኛ ጉባኤው፤ የመቀመጫ ብዛቱን ከ99 ወደ 165 ከፍ አድርጓል።

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15236/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

03 Mar, 14:34

4,320

በአራት ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ተነሳ

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን “ህግን ተላልፈው ተገኝተዋል” በሚል በአራት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ጥሎት የነበረውን የእግድ እርምጃ’፤ “ማስጠንቀቂያ” በመስጠት ከዛሬ ጀምሮ ማንሳቱን አስታወቀ። ባለስልጣኑ እገዳውን ያነሳው፤ ከታገዱት ድርጅቶች ጋር ባደረገው ውይይት “በተፈጠረ መግባባት” እና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ያቀረበውን ምክረ ሃሳብ ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደሆነ አስታውቋል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የዛሬውን ውሳኔ ያስተላለፈው “በታገዱት ሁሉም ድርጅቶች” ላይ መሆኑን ዛሬ ሰኞ የካቲት 24፤ 2017 ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። ተቆጣጣሪ መስሪያ ቤቱ ባለፈው መንፈቅ ዓመት ብቻ በሰባት ድርጅቶች ላይ የእግድ ውሳኔ ማስተላለፉን ባለፈው ጥር ወር መጨረሻ በፓርላማ በተካሄደው የቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ መግለጹ ይታወሳል።

በዚሁ ጊዜ ውስጥ ከታገዱት መካከል አራቱ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ናቸው። “ከተቋቋሙበት ዓላማ ውጭ ተንቀሳቅሰዋል” በሚል ባለፈው ታህሳስ ወር አጋማሽ የታገዱት እነዚህ ድርጅቶች፤ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ)፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል (EHRDC)፣ የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (CARD) እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች (LHR) ናቸው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ▶️ https://ethiopiainsider.com/2025/15215/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

02 Mar, 09:32

5,800

ከአዲግራት ከተማ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 5.2 የተለካ ርዕደ መሬት ተከሰተ

ዛሬ እሁድ ከአዲግራት ከተማ 46 ኪሎ ሜትር በስተምስራቅ ርቀት ላይ በሚገኝ አካባቢ ላይ በሬክተር ስኬል 5.2 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት ገለጸ። ርዕደ መሬቱ የተከሰተው ከቀኑ 5 ሰዓት ከ14 ደቂቃ ላይ መሆኑንም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።

በኢትዮጵያ በአፋር ክልል ባሉ አካባቢዎች ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢከሰትም፤ በትግራይ ክልል ከተሞች አቅራቢያ ርዕደ መሬት ሲመዘገብ ግን በዚህ ዓመት የመጀመሪያው ነው። የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ቀጠና የተከሰተ መሆኑን የጠቆመው የአውሮፓ ሜዲትራንያን ሴይስሞሎጂ ማዕከል (EMSC)፤ መጠኑም በሬክተር ስኬል 5.3 የተለካ እንደሆነ አስታውቋል።

በኤርትራ ከአንድ ሳምንት በፊት የደረሰ ርዕደ መሬት በሬክተር ስኬል 4.6 ሆኖ ተመዝግቧል። የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተው በቀይ ባህር ሰሜናዊ አቅጣጫ ከአስመራ 24 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለ አካባቢ ነበር። በሀገሪቱ ባለፈው ታህሳስ ወር አጋማሽም እንዲሁ ተመሳሳይ ርዕደ መሬት ተመዝግቧል።

በሐምሌ 2015 ዓ.ም. በኤርትራ ባህር ዳርቻ ዳህላክ ደሴት አካባቢ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ተደጋጋሚ ንዝረቶች አስከትሎ እንደነበር ይታወሳል። ንዝረቱን በሽሬ፣ አዲግራት፣ አድዋ፣ አክሱም እና መቐለ ከተማ ያሉ ነዋሪዎች መስማታቸውን በወቅቱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸው ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

28 Feb, 15:11

6,171

ወንዞችን በቆሻሻ የሚበክሉ ግለሰቦችን እና ተቋማትን እስከ አንድ ሚሊዮን ብር የሚያስቀጣ ደንብ ተግባራዊ ሊደረግ ነው

በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ወንዞችን፤ በባህሪያቸው “አደገኛነት” ባላቸው ደረቅም ይሁን ፈሳሽ ቆሻሻ የሚበክሉ ድርጅቶችን አንድ ሚሊዮን ብር ቅጣት የሚጥል ደንብ ተግባራዊ ሊደረግ ነው።

ከመኖሪያ ቤቶች የሽንት ቤት አሊያም ማንኛውንም ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ እስከ 300 ሺህ ብር እንደሚያስቀጣ ደንቡ ይደነግጋል። የወንዞችን ብክለት ለመከላከል የሚያስችለውን ይህ ደንብ የጸደቀው፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባለፈው ታህሳስ ወር ባደረገው ስብሰባ ላይ ነው።

በደንቡ ላይ የሰፈሩ ድንጋጌዎች ከታህሳስ 2፤ 2017 ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆኑ በሰነዱ ላይ ቢገልጽም፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በዚህ መሰረት ገና መቅጣት አለመጀመሩን የመስሪያ ቤቱ ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከከተማይቱ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ጋር በመሆን፤ ደንቡን የተመለከተ ስልጠና እና የግንዛቤ ማስጨበጫ በትላንትናው እና በዛሬው ዕለት አካሄዷል።

ስልጠናው የተመረኮዘበት “የወንዞች ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል ደንብ”፤ በሰባት ክፍሎች እና በ21 አንቀጾች የተከፋፈለ ነው። በደንቡ መጨረሻ በአባሪነት የተካተተው ሰንጠረዥ፤ በወንዝ እና በወንዝ ዳርቻ ላይ ብክለት በሚፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚጣሉ አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣቶችን ዘርዝሯል።

🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15201/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

27 Feb, 17:32

6,093

በኢትዮጵያ ከሚከሰተው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ የ47 በመቶው መንስኤ “ዛፎች የሚፈጥሩት ንክኪ ነው” ተባለ 

በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚከሰት የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ 47 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ የሚይዘው፤ ዛፎች እና ቅርንጫፎች በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ የሚፈጥሩት ንኪኪ መሆኑ ተገለጸ።

በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ስርቆቶች እና ጉዳቶች የኃይል መቆራረጥ እንዲከሰት የሚያደርጉ ሌሎች ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ተነግሯል።

ይህ የተገለጸው፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ መስመሮችን የማስተዳደር እና የኤሌክትሪክ ኃይልን በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች የመሸጥ ኃላፊነት ያለፈበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፤ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 20፤ 2017 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል አቅርቦት እና ጥራትን ለማሻሻል በአጭር ጊዜ ለመተግበር ካቀዳቸው ተግባራት መካከል፤ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ውስጥ የገቡ ዛፎች እና ቅርንጫፎችን መቁረጥ አንዱ እንደሆነ የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጌቱ ገረመው በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።

በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ አደጋ የሚፈጥሩ ዛፎች እና ቅርንጫፎችን የመቁረጥ ተግባር ከሁለት ወር በፊት እንደተጀመረ የገለጹት አቶ ጌቱ፤ የስራው አፈጻጸም በአዲስ አበባ 50 በመቶ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ 30 በመቶ እንደደረሰ አስረድተዋል።

🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15194/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

26 Feb, 08:25

6,957

በመሬት መንቀጥቀጥ “ከፍተኛ ጉዳት” የደረሰበት የከሰም ስኳር ፋብሪካ፤ ሰራተኞቹን በመጪዎቹ ወራት ሊያሰናብት ነው 

ባለፉት ወራት በተደጋጋሚ በተከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦች “ከፍተኛ ጉዳት” የደረሰበት የከሰም ስኳር ፋብሪካ፤ ከአንድ ሺህ በላይ ሰራተኞቹን እስከ መጪው ግንቦት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ለማሰናበት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

የስኳር ፋብሪካው የሰራተኞች ማህበር በበኩሉ ሰራተኞቹ ሳይሰናብቱ ወደ ሌሎች ፋብሪካዎች እንዲበተኑ ለማድረግ ጥረት እያደረገ መሆኑን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታውቋል።

በስሩ ከአራት ሺህ በላይ ሰራተኞችን የሚያስተዳድረው የከሰም ስኳር ፋብሪካ፤ የቅድመ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የሰራተኞቹን የስራ ውል ያቋረጠው ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የካቲት 11 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ ነው።

በፋብሪካው የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ የተለጠፈው እና “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው ይህ ማስታወቂያ፤ የስራ ውላቸው የተቋረጠ ከአንድ ሺህ በላይ ሰራተኞችን ስም ዝርዝር የያዘ ነው።

ይኸው ማስታወቂያ፤ ፋብሪካው ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከታህሳስ 20 ጀምሮ በተደጋጋሚ የተከሰተው ርዕደ መሬት ባስከተለበት “ከፍተኛ ጉዳት” መሆኑን ያስረዳል።

የስኳር ፋብሪካው በዚህ ምክንያት “ስራውን ሙሉ ለሙሉ ያቆመ በመሆኑ”፤ በማስታወቂያው ስማቸው የተዘረዘረ ሰራተኞቹ የስራ ውል ከየካቲት 10፤ 2017 ጀምሮ “በቅደመ ማስጠንቀቂያ” መቋረጡንም አትቷል።

ይሁንና በዚያው ዕለት ፋብሪካው ማስተካከያ በማድረግ በለጠፈው ማስታወቂያ፤ ሰራተኞቹ ከየካቲት 10 ቀን ጀምሮ መሰናበታቸውን በማስቀረት ከዚሁ ቀን ጀምሮ እንደ የአገልግሎት ቆይታቸው ቅድመ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል።

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15186/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

24 Feb, 09:07

8,149

በአማራ ክልል ታስረው የነበሩ ሁሉም ዳኞች መለቀቃቸውን የክልሉ የዳኞች ማህበር አስታወቀ 

በአማራ ክልል እስከ ትላንት ድረስ በእስር ላይ የነበሩ ዳኞች ሙሉ ለሙሉ መለቀቃቸውን የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር አስታወቀ። ካለፈው ሁለት ወር ወዲህ እስከ አርብ የካቲት 14፤ 2017 ድረስ ባሉት ጊዜያት ከእስር የተለቀቁት ዳኞች ብዛት 36 እንደሆነ የማህበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኑ አሰፋ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

በክልሉ ታስረው የነበሩ ሁሉም ዳኞች መፈታታቸው የተገለጸው፤ የአማራ ክልል ምክር ቤት የዳኞች ያለመከሰስ መብትን ያካተተ የህግ ማሻሻያ ካጸደቀ ከአስር ቀናት በኋላ ነው።

በአማራ በተለያየ እርከን በሚገኙ ፍርድ ቤቶች የሚሰሩ ዳኞች ለእስር ይዳረጉ የነበረው፤ በሚይዟቸው መዝገቦች ላይ በሚሰጧቸው ውሳኔዎች ምክንያት እንደሆነ አቶ ብርሃኑ ገልጸዋል።

“አብዛኞቹ ከስራ ጋር የተገናኘ ነው። ምክንያቱ ‘ዋስትና ጋር ተያይዞ ለምን ፈቀዳችሁ? ለምን ትዕዛዝ ሰጣችሁ? ለምን እግድ ሰጣችሁ?’ [የሚል ነው]። ያው በፍርድ ቤት ዳኞች በህግ የተሰጣቸውን ስልጣን መሰረት አድርገው ሲሰሩ፤ ከአስፈጻሚው ጋር የሚገናኙ አለመግባባቶች ጋር መነሻ በማድረግ የታሰሩ ናቸው” ሲሉ የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት የእስሮቹን መንስኤ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አብራርተዋል።

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15176/

@EthiopiaInsiderNews