Latest Posts from EOTC ቤተ መጻሕፍት (@eotclibilery) on Telegram

EOTC ቤተ መጻሕፍት Telegram Posts

EOTC ቤተ መጻሕፍት
ይህ Channel የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍት፤ ስብከትች እንዲሁም የተለያዩ ለአብነት ትምህርት የሚሆኑ በድምፅ ፤ይሁን በጹሁፍ እንዲሁም በ Video ሚለቀቅበት Channl new
ተጨማሪ ወይም ሚፈልጉትን መፃህፍት

ብለው ይጠይቁን
ማስታወቂያም እንሰራለን በውስጥ መስመር ይጠይቁን
የሰማነዉን እንናገራለን!
ያየነዉን እንመሰክራለን!
45,502 Subscribers
1,904 Photos
79 Videos
Last Updated 01.03.2025 16:55

The latest content shared by EOTC ቤተ መጻሕፍት on Telegram


🚨 እውነት አንተ ኦርቶዶክስ ከሆንክ ይሄ ቻናል ሊያመልጥህ አይገባም

ሁሉንም ኦርቶዶክሳዊ ዜና እና መዝሙር በቀጥታ ስርጭት አንድ ላይ የሚያገኙበት ምርጥ አዲስ ቻናል jOin በማድረግ ይቀላቀሉ

💁‍♂️ ለ ኦርቶዶክሳዊያን ብቻ የተከፈቱ በኢትዮጵያ የመጀመርያዎቹ ኦርቶዶክሳዊ ቻናሎች ❤️❤️❤️

መቋሚያ
ብዙውን ከእንጨት የሚዘጋጅ እንደ በትር ዘለግ ያለ ከወደ ጫፉ መስቀል ቅርጽ ያለው ነው፤ በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው የ "ፐ" ቅርጽ ያለው አሊያም ድቡልቡል የሆነ ነው፤ ከወደ ጫፉ የሚደረገው ነገር የብር ፣የነሐስ ፣የወርቅ፣ የብረት፣ የቀንድ ና የእንጨት ሊሆን ይችላል

አገልግሎቱም
መደገፊያ ፣ መሞርኮዧ ና መዘመሚያ ሲሆን ይህም ከከበሮ እና ጸናጽል ጋር እንዲሁም ብቻውን ከማህሌት ላይ በዝማሜና በሽብሸባ ያገለግላል

ምስጢሩ
መቋሚያ የአዳም ተስፋና ከእመቤታችን ተወልዶ በዕጸ መስቀል ላይ የተሰቀለው የጌታችን የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው።

👉 አንድም መቋሚያ ያዕቆብ ትምህርተ መስቀል ያለበት በትር በፊቱ እያቆመ ይሰግድና ይጸልይ የነበረበት ምሳሌ ነው

👉ካህናት መቋሚያን በትከሻቸው አድርገው  ወዲህ ወዲያ ማለታቸው አይሁድ በዕለተ አርብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ መመውሰዳቸው

ዝማሜ ሚመሰለው በህማማተ ክርስቶስ ነው። መቋሚያው በመስቀል ይመሰላል።ካህናቱ መቋሚያቸው ከዜማ ጋር አስማምተው በዝማሜ ወቅት መቋሚያውን ወደ ግራ ወደ ቀኝ ማድረጋቸው አይሁድ ኢየሱስን አንዴ ወደግራ አንዴ ወደቀኝ ከነመስቀሉ ማንገላታታቸውን ለማስታወስ ነው። ከዛ ወደታች መሬቱን መምታታቸው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ግርፋቱ ሲበዛበት መሬት ላይ መውደቁን ያሳያል።

ጽናጽል
ከብር ከነሐስ-ከሌላም ብረት የሚሰራ፤ እንዲሿሿ ከብረት ቅጠል የሚደረግበት ሲሆን አገልግሎቱም ለእግዚአብሔር ክብር ይዘመርበታል። ጽናጽል ከከበሮ ጋር አብር የሚሄድ የዜማ መሳሪያ ነው

የብረት ቅጠሎቹ ሲያንሱ 5 ሲበዙ 7 ይሆናሉ። 5 ሲሆን አምስቱ አዕማደ ሚስጢር 7 ሲሆን በሰባቱ ሰማያት ይመሰላል።

👉2 የብረት ዘንጎች(የብረት ቅጠሎቹን የሚይዙት) ላይ ከታችኛው ላይ 2 የብረት ቅጠሎች የሚኖሩ ሲሆን ይህም ጌታችን ልደቶች  ማለትም ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከአብ ፤ ድህረ ዓለም ደግሞ ያለ አባት ከእመቤታችን መወለዱ ምሳሌ ነው

👉 የብረት ቅጠሎቹ 3 መሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው

👉ድምጹ ያማረና መልካም መሆኑ በመላእክት ዜማ ይመሰላል (ሰብሕዎ በጽናጽል ዘሠናይ ቃሉ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 150)
👉ጽናጽል ወዲህ ወዲያ ማለቱ ጌታችን የመንገላታቱ ምሳሌ ነው

ከበሮ
ከእንጨት ተዘጋጅቶ በጠፍርና በቆዳ የሚለጎም የዜማ መሳሪያ ነው።

ለክብረ በዓል ለበዓል ለበዓለ ንግሥ ዕለት ለእግዚአብሔር ክብር የሚመታ የሚመዘመርበት ነው

በከበሮ ወበመዝሙር ይዜምሩ ሎቱ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 149

ምስጢሩ-
አፉ ሁለት ነው፤ ጠባብ እና ሰፊ
   ሰፊው- ቁመት ደረት ምሉዕ በኩለሄ/እግዚአብሔር በሁሉ ሙሉ መሆኑን ሲሆን

ጠባቡ- ደግሞ ወልድ በአጭር ቁመት መወሰኑን የሚያመለክት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው

እንጨቱ ከቆዳ የተለጎመበት ጠፍር- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ የገረፉበት የግርፋቱ (የገላው ሰንበር) ምሳሌ ነው

ከበሮ የሚለብሰው ሱቲ ጌታችን የለበሰው ቀይ ግምጃ ምሳሌ ነው

የከበሮ አመታት ምስጢር
መጀመሪያ ከበሮ ተቀምጦ ቀስ እየተባለ ነው የሚመታው።

👉በመሬት መመታቱ ጌታችን አይሁድ በመሬት እየጎተቱ መምታታቸውን
👉በግራ እና በቀኝ ሲመታ ከቀኝ ሲመታ ወደ ግራ ከግራ ሲመታ ወደ ቀኝ ማዘንበሉን ለማስታወስ ነው
👉ከበሮ በትከሻ ተደርጎ ሲመታ ከወደቀበት እንደመቱት ፤በፍጥነት ሲመታ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሊሰቀል ሲቃረብ በፍጥነት መምታታቸውን ያስታውሰናል

የማሕሌት ተወዛዋዦች

ዛሬ ለወጉ ማሕሌት አንቀርም ፣ ቸብቸቦ ይጀመራል ፣ ወጣቶች ከበሮውን ለማንሳት ሪከርድ በሚያሻሽል ፍጥነት የከበሮውን ገመድ ከጀርባቸው ያዋሕዱታል (እንዲያው ወጣቶች ስንል በእድሜ ማለታችን አይደለም ቆብ የደፉ መስቀል የጨበጡ ቀጣይ በምናየው መልኩ የሚሳተፉትንም የሚገልጽ ቃል ነው እንጅ ) : አፍታም ሳይቆይ እንደ አሎሎ ወርዋሪ መሽከርከር ይጀመራል : አንድ እጅ ተዘርግቶ እስክስታው ይቀልጣል: ሁለት እግር ከፍ እያለ መዝለል ይጀመራል : አሁን በአንደበት የሚነገረው ስብሐተ እግዚአብሔር ነው መሬት ላይ ደግሞ ኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ ሁኗል : ነፍስ ምን እየተካሄደ እንዳለ ዘንግታለች : ስጋ ግን እየተንቀጠቀጠ ነው : የስሜት እሳት ተቀጣጥሏል : እሽሽሽሽሽሽ የሚል ማጀቢያ መሆኑ ነው ከአንደበት አትጠፋም : የሙቀቱ መጠን ከቁጥጥር እየወጣ ነው : ወደ ሴቶች ጉዞ ይጀመራል : አሁን ሴቶች በቅርበት እየተመለከቱ ነው ከበሮው ላይ ብትሩ ይበረታል : የዝላዩ ከፍታ ይጨምራል : ጿጿጿጿጿ የሚል የጽናጽል ድምጽ የሚያሰማ ቢኖርም ፈገግ ተብሎ ታልፎ ጭፈራው ይደራል : ሊቃውንቱ ቢናገሩም የተጠሉ ይሆናሉ : ነፍስ ከተኛች ቆይታለች ከዱካካዋ ልትነቃ አልቻለችም : ከጎን ከበሮ የሚመታው ጓደኛ በመቺው ትዕዛዝ አመታቱን እየቀረጸ ነው : Tik Tok ቀጣዩ የቪዲኦው መሰራጫ መድረክ ነው : የታይታ ክርስትና ! እንደ ፈሪሳውያን ሰው እንዲያይ ብሎ መዘመር ! ተቃራኒ ጾታ እያዩ መስፈንጠር ! በከበሮ ትዳር አይፈለግም ! መዝለል ፣ መሽከርከር ፣ መስፈንጠር፣ መንቀጥቀጥ ፣ እሽሽሽሽሽ ማለት ፣ ወደ ተቃራኒ ጾታ አንጋጦ መዞር ይቁሙ !

ሁለት እጅ ስላለህ እና መምታት ስለቻልክ ብቻ ከበሮ አትሸከም ምስጢሩን ተረዳ ያኔ ሲገባህ ዕንባህ ከዐይንህ ያለማቋረጥ ጉንጮችህን መወረጃ አድርጎ ሲጎርፍ ይታወቅሀል : ያኔ ልብህ እንጅ እግርህ አይዘልም : ያኔ የምትንቀጠቀጠው እግዚአብሔርን በመፍራት ይሆናል: ያኔ ስትዘል አፍአዊ ላብ ሳይሆን ሕሊናህ ይሆናል በተመስጦ የሚያልበው : ያኔ እንደ መላእክት የሰማይ የመቅደሱ በር እስኪከፈት እንዲዘምሩ አንተም የልቦናህ በር ተከፍቶ ለምስጋና ትታትራለህ ። አየኋት : አወቅኳት : ወደድኳት ብሎ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ የመላዕክትን ዝማሬ ሰምቶ መጦ ባቀናት ቤተክርስቲያን ምድራዊ ተወዛዋዦች ገብተናልና ወደ ልቦናችን እንመለስ ።

በወንዶች ብቻ የሚቆም ግብር አይደለም በአንስቶችም ተመሳሳይ ፍሬ አፍርቶ ተንዠርቅቆ እናገኘዋለን : በሰንበት ትምህርት ቤት እንዲሁ በአደባባይ በዓላት ቁጥራቸው ትቂት ያልሆኑ በከበሮ ላይ መከራ አጽንተው በመከራ ድር ተተብትበው ይኖራሉ : አንቲ ተቃራኒ ጾታሽ እንዲያይሽ ካልሆነ ምን ያሽከረክርሻል ? ምን ያዘልልሻል ? ወደ እነማን ፊትሽን ዙረሽስ ትመቻለሽ ? ወደፊት ወደ ኋላ ስትይ የክርስቶስን መገፋት ታስቢያለሽ ወይስ ወደፊት ሄደሽ ልብሽ የወደደውን ትፈቅጃለሽ ? ከንቱ ውዳሴን ሽተሽ በሰፈሩ የከበሮ አመታትሽ እንዲወራ ከሆነ እኅቴ ሆይ የገሀነም ደጃፍ ላይ ነሽና ሳትገቢ ተመለሽ! በአደባባይ ምድርን የሚያበራ እሳት ከማቀጣጠል በሕሊና መቅረዝ ትቂት መንፈሳዊ ማኅቶት ማብራት ይሻላል ! በእውነት እናስተውል ! እነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እኮ በዝማሬያቸው ሕሙም ይፈውሱ ነበር በእኛስ? ዘመርን ብለን እራሳችን ሕሙም ሆነን እንመለሳለን ! ወደ እነእንተና ለይቶልን በኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ እግዚአብሔር ቢመለክ ምን ችግር አለው ብለን የኅብረት ዘፋኞች ከመሆናችን በፊት ለብው ! አምላከ ያሬድ ወዳዊት ወእዝራ የቀናውን መንፈስ ያድለን ! የቅዱሳኑ ዝማሬ ወላዲተ ቃል ድንግል ማርያም በረድኤት አትለየን
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot

ክፍል ፪

ውድ የ አሐቲ ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቻችን ፣ እንደምን አላችሁ! ዛሬ ደግሞ እያንዳንዳችንን ክርስቲያኖች የሚመለከቱ ሥርዓቶችን እንመለከታለን። ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ማደሪያ እንደመሆኗ ሥርዓት እንዳላት ሁሉ፣ እያንዳንዱ ክርስቲያንም የእግዚአብሔር ማደሪያ እንደመሆኑ ሥርዓት አለው።

1. ለክርስቲያኖች የተሠሩ ሥርዓቶች

ቅዱስ ቃሉ ለእያንዳንዱ የቤተክርስቲያን አገልጋይ እንዲሁም ምእመን ሥርዓትን አስቀምጧል። ከእነዚህም መካከል፦

•  ለጳጳሳት፡- ዕድሜያቸው ከ50 ዓመት በላይ መሆን፣ ማየትና መስማት የተሳናቸው ወይም ጋኔን ያደረባቸው አለመሆን፣ ምሥጢራተ መጻሕፍትን ማወቅ፣ በምእመናን መመረጥ፣ ነውር የሌለባቸው፣ ትዕግስተኞችና የማይሰክሩ መሆን ይጠበቅባቸዋል። (ፍት.ነገ 1.5)
•  ለካህናት፡- 30 ዓመት ሳይሞላቸው ክህነትን አለመቀበል፣ አንድ ሚስት ብቻ ማግባት፣ አብዝቶ አለመጠጣትና አለመሰከር፣ የኃላፊነታቸውን ጥቅም አለመሻትና ለመማታት አለመፍጠን ተጠቃሽ ናቸው። (ፍት.ነገ 1.6 እና 1ኛ ጢሞ 3:1)
•  ለዲያቆናት፡- ጭምትነትን ገንዘብ ማድረግ፣ ነውርና ነቀፋ የሌለባቸው መሆን፣ እውነተኛ መሆን፣ ታዛዥነታቸው የተመሰከረላቸው መሆን፣ የማያዳሉና የማይሰክሩ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
•  ለምእመናን፡- መጠመቅ፣ ሥጋ ወደሙ መቀበል፣ ንስሐ መግባት፣ መጾም፣ መጸለይ፣ መስገድ፣ መመጽወት፣ ዐሥራት በኩራት ማውጣትና ልጆችን በሥርዓት ማሳደግ ተጠቃሽ ናቸው። (ፍት.ነገ 1.11)

2. ለምእመናን አንድነት የተሠራ ሥርዓት

ቤተክርስቲያን ምእመናን በኅብረት እንዲኖሩ ሥርዓቶችን ትሠራለች። ለምሳሌ፡-

•  ካህናት ሲቀድሱ ምእመናን በኅብረት ጸሎት ያደርሳሉ።
•  በጋራ ሆነው ይጸልያሉ።
•  በዓላትን በአንድነት ያከብራሉ።
•  በሰንበት ጽዋ ማኅበር በአንድነት ይጠጣሉ።
•  የቅዱሳንን መታሰቢያ በጋራ ያደርጋሉ።

3. የምእመናን መብትና ግዴታ

•  ግዴታዎች፡- መብዓ፣ አሥራት በኩራትና የሰበካ ጉባኤ መዋጮን በወቅቱ መክፈል እንዲሁም መጻሕፍትንና አልባሳትን መለገስ ተጠቃሽ ናቸው።
•  መብቶች፡- ትምህርተ ወንጌልን ማግኘት፣ ልጅ ሲወለድ ክርስትና ማስነሳት፣ ጸሎተ ሜሮን መቀባት፣ ቁርባን መውሰድ፣ በኃጢአት ሲወድቁ ከካህን ንስሐ መግባት፣ ሲታመሙ ጸሎተ ቀንዲል መቀባት፣ ጋብቻ ሲፈጽሙ ሥርዓተ ተክሊል ማድረግና ሲሞቱ ጸሎተ ፍትሐት ማግኘት ይገኙበታል።

እነዚህን ሥርዓቶች ጠብቀን በክርስትና ሕይወታችን እንድንጸና እግዚአብሔር ይርዳን!

ይህን መልዕክት ለሌሎችም በማጋራት ያወቅንውን እንድናሳውቅና ና በረከትን እንድናገኝ እንጋብዛችኋለን እንዲሁም ማንኛውም አይነት ጥያቄ ካላችሁ ግሩፑ ላይ አሳውቁን እንመልሳለን

የየካቲት 23 ስርዓተ መሕሌት

አባ መዓዛ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ትምህርት በቂ ችሎታ አላቸው ከሚባሉ መምህራን አንዱ ናቸው፡፡ እኒህ የቤተክርስቲያን ሊቅ ዕውቀታቸውን በበለጠ በዓለም ዐቀፍ ቋንቋ ለማሻሻል ባላቸው ፍላጎት መሠረት ወደ ኢየሩሳሌም አንግሊካን ቤተክርስቲያን ሴንት ጆርጅ ኮሌጅ ተላኩ፡፡ ወደፊት ጵጵስና የሚሾም ብለው ጃንሆይ በተናገሩት መሠረት የኤጲስ ቆጶስነት ትምህርት እንዲሠለጥኑ ነበር የተላኩት፡፡ ሁለት ዓመት ተኩል የቤተክርስቲያን አስተዳደር (Church History and Administration) ተምረው ተመለሱ፡፡ ከውጭ ሀገር እንደተመለሱ ከ1951-1960 ዓ.ም በተማሩት ትምህርት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካህናት አስተዳደሪ ሆነው ቤተክርስቲያንን በማገልገል ምእመናንን በማስተማር ሐዋርያዊ ግዴታቸውን ሲፈጽሙ ቆይተዋል፡፡

በዚሁ መካከል በ1958 ዓ.ም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል፡፡ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪ ሆነው እንኳን በበጎ ፈቃደኝነት ምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም እየተመላለሱ ያስተምሩ ነበር፡፡ በኋላም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዋና አስተዳዳሪ በመሆን አገልግለዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ወደ እንግሊዝ ሀገር ኦክስፎርድ ኦስሄትሮፕ የሚባል የካቶሊክ ኮሌጅ በ1961 ዓ.ም ተልከው በእንግሊዝ ሀገር ለአራት ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው (Bachelor of Divinity in Basic Philosophy Super mental and Developmental Psychology) ዲግሪ ተቀብለው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡
ከሀገርና ከቤተክርስቲያን የተቀበሉትን ታላቅ አደራ አክብረው ሀገራቸውን ለማገልገል በውጭ ሀገር የቀሰሙትን ሥልጣኔና ልምድ ለሀገራቸው የሚያውሉ ምሁራን በርካታ ናቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ካፈራቻቸው ሊቃውንት መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በምዕራቡ ዓለም በትምህርት ቆይታቸው በትምህርትና በልምድ ያካበቱትን ዕውቀት በተግባር ላይ ለማዋል የቻሉ ምሁር ናቸው፡፡ በዚህም መነሻ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ፣ የሰበታ ቤተ ደናግል የበላይ ኀላፊና የቦርድ አባል ሆነው አገልግለዋል፡፡ በባሕል ሚኒስቴርም በቋንቋ ጥናት አካዳሚ ውስጥ መርሐ ልሳን ተብሎ በሚታወቀው ክፍል በመምህርነት ሠርተዋል፡፡

በተፈሪ መኰንን ት/ቤት ውስጥ ከውጭ ሀገር በልዩ ልዩ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ኢየሱሳውያን ያስተምሩ ስለነበር ብዙ ጊዜ የሃይማኖት ግጭት ይፈጠር ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ተማሪዎች በመንፈሳዊ ዕውቀታቸው ጠንካሮች ስለነበሩ በሚያቀርቡት ጥያቄ በተማሪዎቹና በመምህራን መካካልም በየጊዜው ግጭት ይፈጠራል፡፡ ዐፄ ኃይለ ሥላሴም ጉዳዩን ሲያጣሩ የግብረ ገብነት መምህር እንደሌላቸው በተማሪዎቹ ስለተነገራቸው በአባ ሐና አቅራቢነት በዚያን ጊዜ ስማቸው አባ መዐዛ ቅዱሳን ወደ ጃንሆይ ቀርበው በግብረ ገብ መምህርነት እንዲቀጠሩ ስለፈቀዱ ለተፈሪ መኮንን ት/ቤት የግብረ ገብ መምህር ሆነው ተቀጥረው ከ1949 ዓ.ም እስከ 1954ዓ.ም ድረስ በግብረ ገብነት አስተማሪነታቸው አገልግለዋል፡፡

ብፁዕነታቸው በተፈሪ መኮንን ት/ቤት እያስተማሩ የምስካዬ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም በተጓዳኝ በትምህርት ቤቱ ግብረ ገብ የሚያስተምሯቸውን ተማሪዎች ሰፋ ያለ የሃይማኖት ትምህርት የሚቀስሙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ሲሉ በምስካዬ ኅዙናን መድኃ ኔዓለም ገዳም ወጣቶችን ስለሃይማኖት ማስተማር ጀመሩ፡፡ የዚህ አገልግሎት ፍጻሜም አንጋፋውን የተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት ለመመሥረት አብቅቶታል፡፡ ብፁዕነታቸውም የዚህ ሰንበት ት/ቤት ከመሥራቾቹ አባላት አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በወቅቱ ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ቋሚ ሰባኬ ወንጌል በመሆንም አገልግለዋል፡፡

ቅድስት ቤተክርስቲያን በሬዲዮ ትምህርት በምታስተምርበት ወቅት፤ አባ መዐዛ ቅዱሳን (በኋላ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል) በርቱዕ አንደበታቸው በብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ “ማኅበራዊ ኑሮ በቤተክርስቲያን'' እና “የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት” በተሰኙ አርእስተ ትምህርት ይሰጡ ነበር፡፡ ብፁዕነታቸው በሕይወት ዘመናቸው ካከናወኗቸው ተግባራት ለምእመናን በሬዲዮ ስብከተ ወንጌልን በማስተላለፍ የሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገሩ ነበር፡፡

በአርሲ ሀገረ ስብከት ከ1975 ዓ.ም ጀምሮ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በመሆን ለ33 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ በአርሲ ሀገረ ስብከት ቆይታቸውም በምእመናን የሚወደዱና የሚከበሩ ታላቅ አባት ነበሩ፡፡ ወደ አርሲ ሀገረ ስብከት በመጡበት የመጀመሪያ ሳምንታት ውስጥ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ ያሉትን ዐበይት ችግሮች ካጠኑ በኋላ በሀገረ ስብከቱ ውስጥ አንድም የወጣቶች እንቅስቃሴ የሚደረግበት አጥቢያ አለመኖሩንና ሰንበት ት/ቤቶችም የተዘጉና ወጣቶችም በቤተክርስቲያን አካባቢ እንዳይታዩና ከፍተኛ ክትትልና ቁጥጥር ይደረግባቸው እንደነበረ ካወቁ በኋላ <<የተሾምነው ምእመናንን ልንጠብቅ ነው እንጂ ልንበትን አይደለም፤ በቤተክርስቲያን ላይ ማንም ሊያዝዝ አይችልም ስለቤተክርስቲያን ኃላፊነቱ የእኛ ነው>> በማለት አቋማቸውን በአደባባይ ከመግለጻቸውም በላይ በዘመኑ በሥልጣን ላይ ከነበሩት የደርግ ሹማምንት ፊት ለፊት በመጋፈጥ ልጆቻቸውን ከጥቃት ታድገዋል፤ ተቋርጦ የነበረው የሰንበት ትምህርት ቤት እንዲቀጥል አድርገዋል፡፡
ብፁዕነታቸው የነገይቱ ቤተክርስቲያን ተረካቢ ወጣቶች መሆናቸውን ጠንቅቀው የሚያውቁ ስለሆነ በሀገረ ስብከታቸው ውስጥ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ለወጣቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲጠናከሩ አድርገዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ወደ አርሲ ሀገረ ስብከት ተመድበው ሲመጡ የነበሩት አብያተ ክርስቲያናት ቁጥር 117 (አንድ መቶ አሥራ ሰባት) ብቻ የነበሩ ሲሆን እርሳቸው በሕይወት በነበሩባቸው ዘመናት ከ300 (ሦስት መቶ) በላይ አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናትን በማስከተል ምእመናን በርቀት ምክንያት ሳይንገላቱ በአቅራቢያቸው ከቤተክርስቲያን አገልግሎት ተሳትፎ እንዲኖራቸው ከማድረጋቸውም በላይ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የይዞታ ማረጋገጫ እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡ 
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዕረፍት ምክንያት ከነሐሴ ወር 2004 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተመርጠው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ሆነው እስከተሾሙበት የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ በዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክነት ቅድስት ቤተክርስቲያን በመምራት አባታዊ ግዴታቸውን ተወጥተዋል፡፡

ብፁዕነታቸው ባደረባቸው ሕመም ምክንያት የካቲት 21 ቀን 2008 ዓ.ም ልክ በዛሬዋ ቀን ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ዐርፈው ሥርዓተ ቀብራቸው የካቲት 24 ቀን 2008 ዓ.ም በደብር ቅዱስ ደብረ መዓዛ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ተፈጽሟል፡፡

የብፁዕ አባታችን በረከታቸው ይደርብን፡፡
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery

ከማቴዎስ ወንጌል ጀምሮ እስከ ራእየ ዮሐንስ መጨረሻ፣ ትርጓሜ ፍትሐ ነገሥትን በእጃቸው የጻፉት ሊቀ ጳጳስ

<<የተሾምነው ምእመናንን ልንጠብቅ ነው እንጂ ልንበትን አይደለም፤ በቤተክርስቲያን ላይ ማንም ሊያዝዝ አይችልም ስለቤተክርስቲያን ኃላፊነቱ የእኛ ነው>> በሚለው ጽኑዕ አቋማቸው ይታወቃሉ፡፡ ትምህርትን አብዝተው የሚወድዱ እና ሰዎችም እንዲማሩ በብርቱ የሚደግፉ፤ ጾመ ድጓ፣ ምዕራፍ፣ ቅኔ፣ የዜማ፣ የአቋቋም፣ የብሉይ ኪዳንና ዐራቱን ብሔረ ኦሪት፣ የዳዊት ትርጓሜን ፣ ሐዲሳትን፣ ቅዳሴ ማርያምና ውዳሴ ማርያም፣ ኪዳን፣  ትምህርተ ኅቡዓት፣ ፍትሐ ነገሥት፣ በሀገር ውስጥ ከተማሯቸው ጥቂቱ ነው፡፡
ከትግራይ እስከ አርሲ ሀገረ ስብከት ጠባቂነት በጵጵስና ደረጃ ቤተክርስቲያንን ያገለገሉበት ከፍተኛ እርከን ቢሆንም በመምህርነትም ብዙ ዓመታትን ቅድስት ቤተክርስቲያን አገልግለዋል፤ በተለይ በብሥራተ ወንጌል የሬዲዮ አገልግሎታቸውን በእጅጉ ይወድዱታል ይኮሩበታልም፡፡ ከሊቃውንት ወገን የሚመደቡት፣ በአስተዳደር ዘመናቸውም ሙስሊሙን ከክርስቲያኑ አስማምተው፣ አዋድደውና አፋቅረው መርተዋል፤ የቀድሞ አባ መዐዛ ቅዱሳን የኋላው ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ካረፉ ዛሬ የካቲት 21/2017 ዓ.ም ዘጠኝ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡

ትውልዳቸው በምሥራቅ ትግራይ ክለተ አውላሎ አውራጃ አውዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጥቢያ ከአባታቸው አቶ ገብረ ሕይወት ፀዓዱ እና ከእናታቸው ወይዘሮ ወለተ ክርስቶስ ቢሻው ግንቦት 12 ቀን 1923 ዓ.ም ነው፡፡ ወላጆቻቸው ልጆችን እየወለዱ በተደጋጋሚ ይሞቱባቸው ስለነበር በጭንቀት ውስጥ ሳሉ ነው ብፁዕነታቸው የተወለዱት፡፡

አባታቸው ገና በጨቅላነታቸው በመሞታቸው በእናታቸው ዘንድ በስስት እየታዩ ነው ያደጉት፡፡ ከዚህም የተነሣ ባለቤታቸውንና ልጆቻቸውን ያጡት እናትም የሁሉም ምትክ የሆኑት ልጃቸውን ካሣዬ ብለው ስም አወጡላቸው፡፡ ትንሹ ካሣዬም የእናታቸውን ፍቅር ሳይጠግቡ፤ እናትም በስስት የሚመለከቱትን የልጃቸውን ስም ጠርተው በዐይናቸው አይተው ሳይጠግቡ በለጋነት ዕድሜያቸው እናታቸውን በሞት ተነጠቁ፡፡ እናታቸው በልጅነታቸው በማረፋቸው ምክንያትም ከእኅታቸው ጋራ መኖር ጀመሩ፡፡ የእኅታቸው ፍላጎት ከብት እንዲጠብቁ፣ ዕድሜያቸው ለአቅመ አዳም ሲደርስም በሕግ በትዳር ተወስነው እንዲኖሩና እያረሱ በግብርና ኑሮአቸውን እንዲገፉ ነበር፡፡

የካሣዬ ሐሳብ ደግሞ ከአድማስ ባሻገር ነበር፡፡ ይኸውም በአካባቢያቸው ባሉት አብያተ ክርስቲያናት እንደሚመለከቱት ሁሉ ከሊቃውንቱ እግር ሥር ቁጭ ብሎ መማር፣ ቤተክርስቲያንን ማገልገል፣ ጉባኤ አስፍቶ  ወንበር ዘርግቶ ማስተማር ነበር ::

ብፁዕነታቸው አባቴ <<በጣም መንፈሳዊ ሰው ነበሩ፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ አባታችን እያሉ ይጠሩኛል ስለእኔ ግን ትንቢት ተናግረዋል፡፡ አንዳንድ ሰዎችም ትልቅ አባት ይሆናል ብለው ይናገሩ እንደነበረ ነግረውኛል፡፡ በወቅቱ እኔ ልጅ ስለነበርኩ ይናገሩት የነበረውን አላስታውሰውም>> በማለት ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ፍላጎታቸውን ለመወጣት ወደ አለቃ መብራቴ ዘንድ በመሔድ በአቡነ አሳይ ቤተክርስቲያን ንባብና የቃል ትምህርት ጀመሩ፡፡ የኔታ ሰሎሞን የሚባሉ የአቋቋም መምህራቸው ያላቸውን የትምህርት ፍላጎት በመረዳት፤ ነገ ለቤተክርስቲያን የሚጠቅሙ ሆነው ስለታዩአቸው ወደ ሌላ ሔደው እንዳይሰናከሉ በማሰብ ከእርሳቸው ዘንድ እንዲማሩ ስለሚፈልጉ ርቀው ወደ ቆሎ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ሦስት ዋስ አስጠርተዋቸው በዚያው እንዲቆዩ አደረጓቸው፡፡

በልጅነታቸው አባትና እናታቸውን ያጡት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ግን ልባቸው ለትምህርት አድልቷልና ቤተክርስቲያንን እናት፣ እግዚአብሔርን አባት አድርገው ከተወለዱበትና ከአደጉበት ወላጆቻቸውንም ካጡበት ቀዬአቸው ትምህርትን ፍለጋ ለመኮብለል ወሰኑ፡፡ ስለዚህም ተጨማሪ ትምህርት ለመቅሰም ከመምህራንና ከቤተሰቦቻቸው ተደብቀው በጥንቱ ቆሎ ተማሪ ልማድ ስማቸውን ቀይረው ጎጃም (በጌምድር) ትምህርት ፍለጋ ተሰደዱ፡፡ በቆሎ ትምህርት ቤትም መዓዛ ቅዱሳን ተብለው ተጠሩ፡፡

ወደ ጎንደር እና ጎጃም ተሻግረው ከየኔታ ኃይሉ ስሜ በየላ ኢየሱስ፣ ከየኔታ መኰንን ላስታ አመራ ማርያም ከእነዚህ ከሁለቱም ጾመ ድጓና ምዕራፍ ከተማሩ በኋላ እንደገና ወደ ቅኔ ቤት ገቡ፡፡ ክህነት የተቀበሉትም ሁለት ጊዜ ምዕራፍና ጾመ ድጓ ዘልቀው ቅኔ እስከ ዘእይዜ ከቆጠሩ በኋላ ነበር፡፡ በደቡብ ጎንደር እና ወሎ ተዘዋውረውም በጉባኤ ቤቶች የዜማ፣ የአቋቋም ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ የሰሜን ጎንደር ደባርቅ ወረዳ ደረስጌ ማርያም አቅንተውም ከየኔታ መንበሩ ዘንድ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ የቅኔ ዕውቀታቸውን ለማስፋፋትም ከአዲስ አበባ ስማዳ ወረዳ ደብረ ዕንቁ በማምራት ከታላቁ ሊቅ ከየኔታ ጌጡ ዘንድ ተምረዋል፡፡ የብሉይ ኪዳንና ዐራቱን ብሔረ ኦሪትና ዳዊት ትርጓሜን ተምረዋል፡፡

ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመማር አዲስ አበባ በሚገኘው ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ገብተው ሐዲሳትን በመጀመሪያ ከመጋቤ ሐዲስ ወ/ሚካኤል፣ ከመ/ር ገብረ ማርያም ዓለሙ፣ ቅዳሴ ማርያምና ውዳሴ ማርያም ከመምህር ይኄይስ፣ ኪዳን ትምህርተ ኅቡዓት ከመምህር ከየኔታ ገብረ ማርያም፣ ከመምህርገብረ ሕይወት ፍትሐ ነገሥት ተምረዋል፡፡

ለራሳቸው እየተማሩ ከቤታቸው ያሉትን ተማሪዎች እያስተማሩ ቆይተዋል፡፡ የመጻሕፍት ተማሪ ሆነው መጻሕፍተ ሐዲሳትን እየተማሩ ሌሊት ከማቴዎስ ወንጌል ጀምሮ እስከ ራእየ ዮሐንስ መጨረሻ ድረስ እንዲሁም ትርጓሜ ፍትሐ ነገሥትን በእጃቸው ጽፈዋል፡፡ መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜን በቀዳማይ ኃይለ ሥላሴ ፊት እንዲተረጉሙ ተፈቅዶላቸው በሚገባ በመወጣታቸው ከንጉሠ ነገሥቱ እጅ ሽልማት ተቀብለዋል፡፡
ዓላማቸው በተመረቁበት በሐዲሱ ተማሪ አብዝተው ጉባኤ አስፍተው ማስተማር ነበር፡፡ ነገር ግን በቅድስት ሥላሴ መምህራን ማሠልጠኛ እድል አግኝተው ለሁለት ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡

ቅኔ ቤት ገብተው ከየኔታ መንበሩ ደረስጌ ስሜን ጃና አሞራ ገብተው ሲማሩ አንድ ዘመዳቸው “ምሰሶ ታቃፊ ሆነህ እንዳትቀር ዲቁና ተቀበል" ያላቸው ትዝ እያላቸው ዲቁና የተቀበሉት ካደጉና ከተማሩ በኋላ ነው፡፡ ይኸውም ከጎንደር ሸዋ (አዲስ አበባ) ድረስ በእግራቸው ተጉዘው በመምጣት በሚያዝያ ወር በ1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ከአቡነ ይስሐቅ ዲቁና ተቀብለዋል፡፡
አቡነ ባስልዮስ በጸመ ፍልሰታ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ይዘዋቸው በመሔድም ውዳሴ ማርያም እና ቅዳሴ ማርያም እየተረጎሙ እዚያው ከርመው ሦስቱን ታላላቅ መዓርጋት ቅስና፣ ምንኲስና ቁምስና በ1953 ዓ.ም ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ተቀብለዋል፡፡

ጵጵስና ጥር 13 ቀን 1971 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ለኤጲስ ቆጶስነት ከተመረጡት 13 አባቶች መካከል አንዱ ሲሆኑ፤ የትግራይ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሾሙ፡፡ በትግራይ ሀገረ ስብከትም እስከ 1975 ዓ.ም አገልግለዋል፡፡

ዘመናዊ ትምህርት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ወደፊት ጵጵስና የሚሾሙ ሰዎች ውጭ ሀገር ሔደው የውጭውን ትምህርትና ልምድ እንዲቀስሙ ያስፈልጋል በማለት ለአቡነ ባስልዮስ አሳሰቧቸው፡፡ ሊቃውንት ሲመረጡም በንጉሡ አማካይነት ተጠቁመው ውጪ ሀገር ከሚሔዱት መካከል አንዱ ሆኑ፡፡

ምን አይነት መዝሙሮችን ይፈልጋሉ?👇👇👇

ዐቢይ ጾም || የጾም መግቢያ
             
Size:-42MB
Length:-45:22

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery

EOTC ቤተ መጻሕፍት pinned ««ዝክረ ኒቅያ» ሀገር አቀፍ የሊቃውንት ጉባኤ ሊዘጋጅ ነው! የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ) <<የሊቃውንት ብዛት ለዓለም መድኃኒት ነው>> በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ ታሪካዊና በዓይነቱ ልዩ የሆነ <<ዝክረ ኒቂያ>> የተሰኘ ሀገር አቀፍ የሊቃውንት የምክክር ጉባኤ ከሚያዚያ 20 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለማካሔድ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ…»