Последние посты Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council (@eiasc1) в Telegram

Посты канала Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
9,085 подписчиков
952 фото
24 видео
Последнее обновление 12.03.2025 11:54

Похожие каналы

📚 ከሰለፎች ምክር 📚
4,929 подписчиков
مكتبة اللغة العربية
2,840 подписчиков

Последний контент, опубликованный в Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council на Telegram

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

06 Feb, 08:56

1,132

ጥር 29፣ 2017 ዓ.ል | ሻዕባን 7፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ            
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጠቅላይ ምክር ቤቱ በህዳሴው ግድብ አቅራቢያ ለሚገነባው ራህማ መስጂድ የፌሮ ብረት ድጋፍ አደረገ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ባምዛ ቀበሌ ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ በቅርብ እርቀት ለሚገነባው ራህማ መስጂድ አራት ሚሊዮን ብር  ወጪ ያደረገበትን 235 ኩንታል የፌሮ ብረት ድጋፍ አድርጓል።

በድጋፍ ርክክቡ ወቅት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ስራ አስፈፃሚ አባልና የተቋማት ዘርፍ ተጠሪ ሼይኽ አልመርዲ አብዱላሂ አሽዌይ እንደተናገሩት ከሆነ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከበወረት ድጋፍ በተጨማሪ የመስጂዱ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ህዝበ ሙስሊሙን የማስተባበር ሚና እየተጫወተ ነው።

በታላቁ የረመዷን የመጀመሪያ ጁምዓ  በቤንሸጉል ጉምዝ ክልል ከታላቁ ህዳሴ ግድብ በቅርብ እርቀት ለሚገነባው አል ራሕማን መስጂድ የገቢ ማሠባሰቢያ መርግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ስለሚካሄድ ህዝበ ሙስሊሙ ድጋፍ እንዲያደርግም ሸይህ አልመርዲ አብዱሏሂ ጥሪ አቅርበዋል።

የፌሮ ብረቱን ከጠቅላይ ምክር ቤቱ የተረከቡት የአል ራሕማን መስጂድ ተወካይ አቶ ኩራባቸው ዓለዊ በበኩላቸው  የመስጅዱ የመሰረት ደከንጋይ ህዳር /09/ 2017 በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም መቀመጡን አስታውሰው ከህዳር 24 2017 ጀምሮ መስጅዱ በግንባታ ላይ መሆኑን ገልፀዋል።

አቶ ኩራባቸው አክለውም ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለመስጅዱ ግንባታ የፌሮ ብረት ድጋፍ ማድረጉ የመስጅዱን ግንባታ በማፋጠን በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ያግዛል ብለዋል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለራህማ መስጅድ ግንባታ ላደረገው የብረት ድጋፍ በክልሉ ሙስሊምና በመስጂዱ ኮሚቴ ስም አመስግነው ከዚህ በፊትም ከተውፊቅ (ፍል ውሐ)፣ ከሰላም (ቄራ)፣ ከአቡ ሁረይራ (ወሎ ሰፈር) እና ከታላቁ ንጎስ ነጃሺ (አፍሪካ ህብረት) መስጂዶች ከህዝበ ሙስሊሙ ለመስጅዱ ማሰሪያ ገንዘብ መሰብሰቡን አስታውሰዋል።

በቀጣይም በታላቁ የረመዷን ወር የመጀመሪው ጁምዓ አዲስ አበባ ላይ በሚገኙ መሳጂዶች ድጋፍ ለማሰባሰብ ከወዲሁ የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

05 Feb, 12:49

1,468

ጥር 28፣ 2017 ዓ.ል | ሻዕባን 6፣ 1446 ዓ.ሒ

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የተከበሩ አቶ ሽመልስ አብዲሳ በጠቅላይ ምክር ቤቱ ተገኝተው ከፕሬዝደንቱንና ከከፍተኛ የመጅሊስ አመራሮች ጋር ተወያዩ።
••••••••••••••••••••••••••••••••

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር በመገኘት ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ከክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ እና ከከፍተኛ የመጅሊስ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳደሩ ከሸገር ሲቲ ምስረታ ጋር በተያያዘ ፈርሰው በነበሩ መስጅዶች ዙሪያ በመንግስት የተገባው ቃል ያለመረሳቱን አስታውሰው በቶሎ አግልግሎት አለመጀመሩ ሂደቱ ጊዜ በመውሰዱ ነው ብለዋል።

አያይዘውም በሸገር ሲቲ ምስረታ ምክንያት የፈረሱ መስጂዶች አገልግሎት መስጠት እንደሚጀመሩ ቃል በገባነው መሠረት በአጭር ጊዜ ውስጥ ውሳኔውን ተግባራዊ እናደርጋለን ብለዋል።

ርዕሰ መስተዳደሩ በክልሉ በሚኖሩ ሙስሊሞች ዙሪያ ከከፍተኛ የመጅሊስ አመራሮች ጠቃሚ የሆነ የጋራ ወይይት አድርገዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንትና ከከፍተኛ የመጅሊስ አመራሮች በክልሉ ነዋሪ ሙስሊሞች የሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ርዕሰ መስተዳደሩ የተከበሩ አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንትና ከከፍተኛ የመጅሊስ አመራሮች የተነሱ ጥያቄዎችን በመቀበል ጥያቄዎቹ በአጭር ጊዜ ምላሽ እንዲያገኙ መስተዳድራቸው በትኩረት እንደሚሰራ ቃል ገብተዋል።

ውይይቱ በጋራ ችግሮችን ለመፍታትና ተጨባጭ መፍትሄ ለመስጠት እንደሚያግዝም ተጠቅሷል።

•••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

05 Feb, 11:36

1,284

ጥር 28፣ 2017 ዓ.ል |  ሻዕባን 6፣ 1446 ዓ.ሒ。
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
"ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከሳውዲ አረቢያ ሀጅና ኡምራ ሚኒስቴር በተቀበለው የምዝገባ መመሪያ መሰረት ምዝገባው እስከ የካቲት 22 ብቻ ይከናወናል" ― ሀጅ ሪያድ ጀማል
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሀጅ ምዝገባ በይፋ ከተደረገበት ጥር 15/ 2017 ጀምሮ በመዝገባ ላይ እንደሚገኝ በዛሬው ዕለት በምዝገባ ሂደቱ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሐን በሰጠው ማብራሪያ አስታውቋል፡፡

ሀጅንእንደሌሎች ኢስላማዊ ግዴታዎች ባለንበት ቦታ ሆነን የምንፈፅመው አለመሆኑ ከሌሎች ግዴታዎች የተለየ እንዲሆን አድርጎታል ያሉት የከፍተኛ ምክር ቤቱ ዋና ፀሀፊ ሸይህ ሁሴን በሽር ሀጅ በአካል ካዕባ መገኘትን የሚጠይቅ በመሆኑ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ያስፈልገዋል ብለዋል፡፡

ዋና ፀሀፊው አያይዘውም ሀጅ የማድረግ አቅሙን አላህ የሰጣቸው ምዕመናን ከወዲሁ በመመዝገብ እራሳቸውን ከጌታቸው ግዴታ ነፃ ሊያደርጉ እንደሚገባም አስታውሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሀጅ ምዝገባ ሂደቱን ውጤማ ለማድረግ በየጊዜው ሰፊ የማሻሻያ ስራ እየሰራ ይገኛል ያሉት የአዲስ አበበባ ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ሀጅ ሪያድ ጀማል በበኩላቸው ከፍተኛ ምክር ቤቱ የምዝገባ ሂደቱን ለማቀላጠፍ ከፍተኛ በጅት በጅቶ በተደራጀ የሰው ኃይልና ቴክኖሎጂ ፈጣን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከሳውዲ አረቢያ ሀጅና ኡምራ ሚኒስቴር በተቀበለው የምዝገባ መመሪያ መሰረት ምዝገባው እስከ የካቲት 22 ብቻ ይከናወናል ያሉት ዋና ስራ አስኪያጁ የሀጅ ኒያ ያላቸው ሙስሊሞች ነገ ዛሬ ሳይሉ በቀሩት ጥቂት ቀናት ሊመዘገብ ይገባልም ብለዋል፡፡

አንድ ሐጃጅ የሚጠበቁበትን ሰነዶች አሟልቶ ከመጣ ምክር ቤቱ ባስቀመጠው የአሰራር ስታንዳርድ መሰረት ከ10 እስከ 15 ደቂቃ ምዝገባና ክፍያን ጨርሶ እንደሚመለስም ሀጅ ሪያድ ጀማል ጠቅሰዋል፡፡

ሁጃጆች ወደ ምዝገባ ጣቢያ ሲመጡ ከዘጠን ወር በላይ የአገልግሎት ዘመን ያለው ፓስፖርት፣ የመኖሪያ አካባቢን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያና አንድ ጉርድ ፎቶ ይዘው ሊመጡ ይገባል ያሉት ደግሞ በከፍተኛ ምክር ቤቱ የሀጅና ኡምራ መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ሀጅ ኢስሀቅ አብዱልዓዚዝ ናቸው፡፡

ሀጅ ኢስሀቅ አክለውም የአገልግሎት ዘመኑ የተጠናቀቀ ፓስፖርት ያላቸው ሁጃጆች ፓስፖርታቸው በፍጥነት እንዲታደስ ለማስቻል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና የአዲስ አበባ ከተማ መጅሊስ ከኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጋር በመነጋገር ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንደቻሉም አንስተዋል፡፡

ፈቃድ የተሰጣቸው ባንኮች በምዝገባ ጣቢያው የአገልግሎት መስጫ ጊዜያዊ ቢሮ እንዲከፍቱ በማድረግም ለሁጃጆች ከምን ጊዜውም የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ እንደተቻለም የሀጅና ኡምራ መምሪያ ኃላፊው አረጋግጠዋል፡፡
••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

29 Jan, 15:10

1,031

ጥር 21፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 29፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
"ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት ኃላፈነቱን በአግባቡ እየተወጣ ነው" ― ዶ/ር ኑረዲን ቃሲም።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ

በኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ እየተካሄደ ለሚገኘው 2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር ስኬታማነት ከመነሻው ጀምሮ ባሉት ሂደቶች የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተጣለበትን የበላይ ጠባቂነት ሚና በአግባቡ እየተወጣ እንደሚገኝ የውድድሩ አዘጋጁ ዘይድ ኢብን ሳቢት የቁርዓን ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ተናገሩ።

የቁርዓን ማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጁ ዶ/ር ኑረዲን ቃሲም በዛሬው ዕለት እንደገለፁት ውድድሩ ውጤታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከመጀመሪያው ጀምሮ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና ከኡለማዕ ጉባኤ ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ አስፈጻሚ አባልና የፈትዋና ምርምር ዘርፍ ተጠሪ ሼይኽ ኢድሪስ አሊ በበኩላቸው ውድድሩ በመንግስት ጭምር ትኩረት እንዲያገኝ ጠቅላይ ምከር ቤቱ በሃላፊነት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል።

ሸይኽ እድሪስ አክለውም ጠቅላይ ምክር ቤቱ ሃይማኖታዊ ኃላፊቱን ብቻ ሳይሆን እንደ ሀገርም ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር መሆኗን የሚያሳይ እና የቱሪዝም መነቃቃትን በሚፈጥር መልኩ እየሰራ መሆኑን ገልፀው ለዝግጅቱ ስኬታማነት ሁሉም ተባባሪ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

ፍፃሜውን እሁድ ጥር 25/2017 በአዲስ አበባ ስታዲየም በሚያደርገው ዓለም አቀፉ የቁርአንና የአዛን ውድድር ላይ እውቁ አልጀሪያዊ የቁርአን ውድድር ዳኛ የተከበሩ ዶክተር ተማም ዲዳን እንደሚዳኙና በፍጻሜ ውድድሩ ላይ ከ10,000 ሰው በላይ እንደሚታደም አዘጋጆች ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ገልፀዋል።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

29 Jan, 12:03

1,224

ጥር 21፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 29፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
"የ1446 ዓ.ሒ (የ2017) የሐጅ ጉዞ ምዝገባ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል።"
የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በቅጥር ግቢው በተዘጋጁት የምዝገባ ጣቢያዎች ከጥር 15/2017 ጀምሮ ሁጃጆችን በስፋት እየመዘገበ እንደሚገኝ በማህበራዊ የትስስር ገፁ ይፋ አድርጓል።

ከፍተኛ ምክር ቤቱ ዛሬ ይፋ ባደረገው መረጃው በዘንድሮ አመት ሐጅ ለማድረግ ንያ ያለቸው ሙስሊሞች በተዘጋጁት የምዝገባ ጣቢያዎች በአካል በመገኘት እየተመዘገቡ እንደሆነ ጠቅሷል።

በከፍተኛ ምክር ቤቱ የሐጅ እና ዑምራ መምሪያ ክፍል ኃላፊ ኢስሀቅ አብዱልአዚዝ የሀጅ ምዝገባው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ባስቀመጠላቸው አቅጣጫ መሰረት እየተከናወነ እንደሚገኝ መግለፃቸውንም መረጃው አክሏል።

ሐጅ ለማድረግ ንያ ያላቸውና መስፈርቱን የሚያሟሉ ሙስሊሞች የሀጅ ምዝገባ ቀነ ገደብ ከመገባደዱ በፊት በመመዝገብ በመጨረሻ ሰአታት ሊፈጥር ከሚችል መዋከብ እራሳቸውን እንዲከላከሉም ኃላፊው መልዕክት ስለማስተላለፋቸው በመረጃው ተመላክቷል።

የሳውዲ አረቢያ ሀጅና ዑምራ ሚኒስቴር ከቀደምት ዓመታት አንፃር በዘንድሮው የሀጅ ምዝገባ ሂደት ላይ የተጣበበ የጊዜ ገደብ ማስቀመጡ መዘገቡ አይዘነጋም።
••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

22 Jan, 06:47

840

ጥር 14፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 22፣ 1446 ዓ.ሒ

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት የፍልስጤምን አምባሳደር በጽህፈት ቤታቸው አነጋገሩ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ አምባሳደር ፋሬስ አልቁብን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

በኢትዮጵያ የፍልስጤም አምባሳደር ፋሬስ አልቁብ እና የአንባሳደሩ ዋና ጸሐፊ ዲያዲን አል-ናሙራህ በጠቅላይ ምክር ቤቱ ተገኝተው ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት እና ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ስራ አሰፈጻሚ አባላት ጋር በፍልስጤም ሰላም ዙሪያ ተዋይተዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም የሃይማኖታችን መለያ እና የተቋሙ ተልዕኮ ሰላም በመሆኑ የፍልስጤምን እና የኢስራኤልን የተኩስ አቁም ስምምነት አላህ የዘላቂ ሰላም ምክንያት እንዲያደርገው ዱዓችን ነው ብለዋል።

ፍልስጤማዊያን ጸንቶ የመታገል ተምሳሌት፣ በአላህ የመወከል ከፍታንና ትዕግስትን ለዓለም በተግባር ያሳዩ መሆናቸውንም ፕሬዝደንቱ በውይይቱ አንስተዋል።

የክብር ዶክተር ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም አያይዘውም በተኩስ አቁም ሰምምነቱ ጦርነት እንዲቆምና ሰላም እንዲሰፍንም ያለመታከት ያደራደሩት አካላትን አመስግነዋል።

የፍልስጤም በኢትዬጵያ አምባሳደር ፋሬስ አልቁብን በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት የፍልስጤም ታሪክ ከነፃነት ትግል ጋር የተያያዘ መሆኑ ለዓለም ሕዝብ ሁሉ ግልፅ ነው ብለዋል።

አምባሳደሩ አያይዘውም በጦርነቱ መቆም መደሰታቸውን ገልፀው አሁን ያለው ሰላም ዘላቂ እንዲሆን ሙስሊሞች ዱዓ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የስራ አሰፈጻሚ አባላትም ፍልስጤም በሁሉም ዘርፍ ተረጋግታ ማየት እንደሚመኙ ገልጸው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንም ዘወትር ዱዓ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

​•••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eias
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

21 Jan, 09:53

1,609

ጥር13፣ 2017 ዓ.ል |  ረጀብ 22፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ                  
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

ትምህርቷንም ትማራለች፣ ሂጃቧንም ትለብሳለች  በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ተጠናቋል
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

አዲስ አበባ


ትምህርቷንም ትማራለች፣ ሂጃቧንም ትለብሳለች
በሚል መሪ ቃል ከማለዳ ጀምሮ በክልሉ ዋና ከተማ መቐለ ሲደረግ የዋለው ሰላማዊ ሰልፍ በሮማናት አደባባይ  ተጠናቋል።

ከሰልፉ መጠናቀቅ በኋላ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ የህዝበ ሙስሊሙን ተወካዮች በጽ/ቤታቸው አነጋግረዋል።

በወይይታቸውም የሒጃብ ጉዳይ ፍጹም አጀንዳን መሆን የማይገባውና  ሆን ተብሎ አጀንዳ እንዲሆን የተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ችግሩ በፍጥነት እልባት እንደሚሰጠውም ፕረዚዳንቱለተወካዮች ስለማስረዳታቸው ከስፍራው የደረሰን  መረጃ ያመለክታል ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

16 Jan, 15:07

1,472

ጥር 8፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 16፣ 1446 ዓ.ሒ

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ለመልካም ስነ ምግባር ብሔራዊ ንቅናቄ ትግበራ መሰረት የሚሆን ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማሕበራዊ አገልግሎት ዳሬክቶሬት የሥነምግባር ጥናት ብድን ያዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ።

የስነ ምግባር ጥናት ቡድኑ ያዘጋጀው ረቀቅ ሰነድ በሀገር አቀፍ ደረጃ በመልካም ስነ ምግባር (አኽላቅ) ዙሪያ ብሔራዊ ንቅናቄ ለመፍጠር ጠንካራ መነሻ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።

በውይይት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በዳይሬክቶሬቱ የማኀበራዊው ዘርፉ ሀላፊ ዶክተር ተውፊቅ ቢራራ ጠቅላይ ምክር ቤቱ እንደ መሪ ሃይማኖታዊ ተቋምነቱ የስነ ምግባር ጉዳይ ቅድሚያ ትኩረቱ መሆኑን ገልፀው በኃላፊነት የሚመሩት ዘርፍ የስነ ምግባር እሴቶች የሚሻሻሉበትን ሁኔታ የሚያሳይ ረቂቅ ሰነድ እንዲዘጋጅ ማድረጉን ጠቅሰዋል።

በጥናት ረቂቅ ሰነዱ ላይ ማብራሪያ ያቀረቡት ዑስታዝ አህመድ ሙስጠፋ ጥናቱ ኢስላማዊ አስተምህሮዎችን መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል። ረቂቅ የጥናት ሰነዱ ዳብሮ ወደ ትግበራ ሲገባም ብልሹ ስነምግባርን በማስተካከል መልካም ስነምግባራዊ እሴት የተላበሰ ማኀበረሰብ ለመገንባት እንደሚያግዝም ኡስታዙ አክለዋል።

ጥናትና ምርምር እንዲሁም የስረዓተ ትምህርት (ካሪኩለም) ዝግጅት ከማስፈፀሚያ ስልቶች ዋናዎቹ እንደሆኑም ተነስቷል።

የስነ ምግባር ጥናት ቡድኑ የአኽላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሻለ መነቃቃት እንዲፈጥርና ተልዕኮው ከፍ ያለ ትውልድ ለማፍራት በጠቅላይ ምክር ቤቱ እውቅና የሚቋቋመው የአኽላቅ ግብረ ኃይል ከዑለማ ጉባኤ ጽፈት ቤት ጋር በመቀናጀት የሚሰራበት አቅጣጫ እንዳለም ተመላክቷል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ለጥናቱ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን እና ተጨማሪ ማብራሪያ የሚያስፈልጋቸውን ጥያቄዎች አንስተው ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።

በመጨረሻም የተሻለ ስነ ምግባር የተላበሰ ማኅበረሰብ ለመፍጠር ጥናቱ እንዲተገበር ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

****
የኢ.እ.ጉ.ጠ. ም/ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | twitter.com/eiasc
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

14 Jan, 17:24

1,676

https://youtu.be/XLU8HSIKoB8
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

14 Jan, 16:03

1,579

ጥር 6፣ 2017 ዓ.ል |  ረጀብ 14፣ 1446 ዓ.ሂ

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ                  
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
"በወንዶች ተጽእኖ ብቻ ከተመራ እንኳን ተቋም ቤትም አይስተካከልም"

         ሸይኽ ሙሐመድዘይን ዘህረዲን
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማእ ጉባኤ ጽሕፈት ቤት እና የሴቶችና ወጣቶች ዘርፍ በትብብር ያዘጋጁት የሴት ዳዒዎች ውይይት ተጠናቀቀ።

የምክር ቤቱን የለውጥ ጉዞ ለማሳካት በሁሉም አደረጃጀቶች ሴቶችን ማካተት ግዴታና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ነው በማለት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሐጂ ከማል ሐሩን ጥቃቅን ልዩነቶችን በመተው ለህዝቡ ዘላቂ ጥቅም በአንድነት መሥራት ይገባል ብለዋል።

ውይይቱን የመሩት የምክር ቤቱ የዑለማእ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሸይኽ ሙሐመድዘይን ዘህረዲን በበኩላቸው ሴቶች የነቢዩ ሙሐመድ ሶ.ዐ.ወ ወሳኝ የዳዕዋ አጋዦች እንደነበሩ አስታውሰው እነሱን ያላካተተ ተቋም ስኬታማ እንደማይሆን ገልጸዋል።

ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን አያይዘውም በሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ያሉ ችግሮች መፍትሔ የሚገኝላቸው ከሴቶች ጋር ተባብሮ በመሥራት መሆኑንና በወንዶች ተጽእኖ ብቻ ከተመራ እንኳን ተቋም ቤትም እንደማይስተካከል አስረድተዋል።

በጠቅላይ ምክር ቤቱ የሴቶችና ወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ኡስታዛ ፋጡማ ሑሴን ዘርፈ ብዙ የሕዝበ ሙስሊሙን ችግሮች ለመቅረፍ የቅድመና ድህረ ጋብቻ እንዲሁም በልጆች አስተዳደግ ዙሪያ ሰፋፊ ሥልጠናዎች መሰጠት እንዳለባቸው አንስተዋል።

በመሆኑም ሴት ዳዒዎች በጀት ተመድቦላቸው እንዲያስተምሩና የውጭ እስላማዊ ትምህርት ዕድል የሚያገኙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በጥረት ላይ እንደሆኑ ያነሱት ኡስታዛ ፋጡማ ሴት ዳዒዎች በየአካባቢያቸው በሚገኙ የመጅሊስ መዋቅሮች ውስጥ ገብተው እንዲሳተፉም መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሴት ዳዒዎች በመከሩበት በዛሬው መድረክ በሀገር ደረጃ በሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ያሉ ሥር የሰደዱ ችግሮች ተዳስሰው የመፍትሄ አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል።

••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13