👉 “ ያን ጊዜ ጌታ ኢየሱስ በዮሓንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ። (ማቴ ፫÷፲፫) እንደተባለው፦
ጌታችን ከተጸነሰባት ካደገባት ከናዝሬት ገሊላ ለመጠመቅ ወደ ዮርዳኖስ እንደሄ ታቦታትም ከማደሪያቸው ከመንበራቸው ተነስተው ወደባሕረ ጥምቀቱ ይሄዳሉ።
👉 “ ሕዝቡም ዅሉ ከተጠመቁ በዃላ ጌታ ኢየሱስ ደግሞ ተጠመቀ። (ሉቃ ፫÷፳፩) እንደተባለው፦
ጌታችን ከባሕረ ጥምቀቱ እንደደረሰ ኣልተጠመቀም ሕዝቡ ሁሉ ተጠምቀው ከጨረሱ በኋላ ነው የተጠመቀው ታቦታትም ወደ ባሕረ ጥምቀቱ እንደደረሱ ሳይሆን በተዘጋጀላቸው ቦታ ካረፉና ከቆይታ በኋላ ነው ሥርዓተ ጥመቀቱ ይፈጸማል።
👉 “ ባሕር ዓየች ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ ዃላው ተመለሰ። ” (መዝ ፻፲፫፥፫) እንደተባለው፦
ጌታችን ወደ ዮርዳኖስ ለመጠመቅ ሲገባ ባሕረ ዮርዳኖስ እንደሸሸች እና ለሁለትም ተከፍላ እንደ ግድግዳ እንደቆመች (እንደተከተረች) ዛሬም ምዕመናን ከመጠመቃቸው በፊት ውኃ በተዘጋጀው ገንዳ ውስጥ ይከተራል በመቀጠልም ጌታችንም እንደተጠመቀ ምዕመናንም የመታሰቢያ ጥምቀትን ይጠመቃሉ።
✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተስፋዬ
https://t.me/+Vd4rG3DjWHFlDGCo (ቴሌግራም ግሩፕ)
https://m.facebook.com/mekuria.tesfaye.71
https://www.youtube.com/channel/UC8v52_jNY156sxZtplafDtw/about (የዩቱብ አድራሻ)