➕የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሣምንት ቅድስት ይባላል።
- የተለየች ፤ የተባረከች ፤ የከበረች፣ ንጽሕት ማለት ነው::
➕ ለምን ቅድስት ተባለ?
-> «ጾምን ቀድሰ ጉባኤውን አውጁ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤተ ሰብስቡ፡፡»
(ት.ኢዩኤል 1፥14) ብሎ በነቢዩ ኢዮኤል አፍ የተናገረ ቅዱስ እግዚአብሔር የጾማት ጾም ስለሆነች (የጌታችን ጾም ከቅድስት ጀምሮ በመሆኑ) ቅድስት ትባላለች።
-> እንዲሁም የዲያብሎስን ፈተና ድል ለመንሳት በቅድስት ከተማ በሰሎሞን ቤተ መቅደስ ጫፍ የቆመባት ዕለት በመሆኗ (ማቴ 4፥5/ ዮሐ 10፥22-23 ) ሰው ሁሉ ጾምን ጾሞ እንደ ፈጣሪው ፈተናን ድል ነሥቶ ቅድስና እና ክብርን ያገኛልና ቅድስት ተብላለች።
--> ቅድስት ዕለተ ሰንበት
«እግዚአብሔር ሰባተኛይቱን ቀን ባረካት ቀደሳት» (ዘፍ 2÷3፣ ዘጸ 20፥8) ሰዎች ፍጥረት ያልተፈጠረባት ዕለት ብለው እንዳይንቋት እንዳያቃልሏት እረፍተ ሥጋ እረፈተ ነፍስ የተገኘባት ዕለት ስለሆነች ቀደሳት አለ፡፡ ቅዱስ ያሬድም " ሰንበትየ ቅድስትየ ዕንተ አዕረፍኩ እምኩሉ ግብርየ ይቤ እግዚኣብሔር " ብሉአል:: በዚህ እሁድ (ሳምንት ) ቀደሳት፣ አከበራት፣ ከፍ ከፍ አደረጋት :- የተባለች ሰንበትን የምትታሰብበት የሰንበትንም ቅድስና የሚመለከቱ መዝሙሮች የሚቀርብበት ሳምንት በመሆኑ ቅድስት ተብሏል።
-> መዝሙር ዘቅድስት ፦
ግነዩ ለእግዚአብሔር
-> ምንባባተ ቅድስት ዘቅዳሌ ፦
- 1ኛተሰሎ.4፥1-13
- 1ኛ.ጴጥ.1÷13-ፍም
- የሐዋ.10፥17-30
- ማቴ 6፥16-25 (4፥1-11)
-> ምስባክ ዘቅድስት፦
" እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ አሚን ወሰናይት ቅድሜሁ ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ "
ትርጉም፦ " እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ፥ ምስጋና ውበት በፊቱ ፥ ቅድስትነትና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው ። " (መዝ 95፥5)
-> ቅዳሴ ዘቅደስት፦
- ኤጲፋንዮስ
✍️ አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተስፋዬ
https://t.me/+Vd4rG3DjWHFlDGCo (ቴሌግራም ግሩፕ)
https://m.facebook.com/mekuria.tesfaye.71
https://www.youtube.com/channel/UC8v52_jNY156sxZtplafDtw/about (የዩቱብ አድራሻ)