እንኳን ለ1446ኛው ዓ.ሒ. የረመዷን ወር አደረሰን፤አደረሳችሁ።
ዛሬ እለተ ጁመዓ፣የካቲት 21/2017 ዓመታዊው የልግስና ሳምንት መቋጫውን አገኘ። በእለቱ ለተማሪዎች በመዝናናት ላይ የተመሠረተ ልዩ የልግስና መርሃ ግብር የተካሄደ ሲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተለይ የተማሪዎች ጀመዓ ኃላፊ መምህራንና የበጎ አድራጎት ክበብ ተጠሪ፣ እንዲሁም የቀድሞ ተማሪዎች በቅንጅት ባካሄዱት የነቃ ተሳትፎ መርሃ ግብሩ በደመቀና በተሳካ መልኩ ተጠናቅቋል።
በተለይ የዛሬውን ቀን ጨምሮ ለተከታታይ ቀናት በተማሪዎች ጀመዓ አመራር መምህራን በከፍተኛ ቁርጠኝነትና ዘመቻ በተካሄደ የልግስና ንቅናቄ በአጠቃላይ በገንዘብና በአይነት 323,000 (ሦስት መቶ ሃያ ሦስት ሺ)ብር ሊሰበሰብችሏል። በእቅድ ተይዞ ከነበረው የገንዘብ መጠንም የ73ሺ ብር ጭማሪ አሳይቷል።
ለእቅዱ መሳካት ላቅ ያለውን ሚና ለተጫወታችሁ ወላጆች (አሳዳጊዎች) ልባዊ ምስጋናችንን እያቀረብን ለሰደቃ ያዋላችሁት ገንዘብ በዱንያም በአኼራም ድርብርብ አጅር የምትመነዱበት ያደርግላችሁ ዘንድ ዱዓችን ነው።
አልቀለም የልግስና ዓለም!!!