Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community @alphasps Channel on Telegram

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

@alphasps


+251113498906

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community (English)

Welcome to Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community, a place where students, parents, and teachers come together to form a supportive and engaging learning environment. Our Telegram channel, @alphasps, serves as a hub for all members of our school community to connect, share resources, and stay updated on school events and announcements. Who is it? Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community is a vibrant and inclusive community made up of students, parents, and teachers who are dedicated to academic excellence and personal growth. What is it? Our Telegram channel, @alphasps, is a virtual space where members can engage in discussions, ask questions, and collaborate on projects. Whether you're a student looking for study buddies, a parent seeking information about school programs, or a teacher sharing educational resources, our channel is the place to be. Join us today to be part of the Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community and enhance your educational experience!

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

31 Jan, 12:24


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ

የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት (First semester) ትምህርት ተጠናቆ የማጠቃለያ ፈተና መሠጠቱ ይታወቃል።  በመሆኑም የፈተና ወረቀት (ውጤት) የሚመለሰው የፊታችን ሠኞ ማለትም በ26/05/17 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 - 5:30 እንደሆነ መልዕክት መተላለፉ የሚታወቅ ሲሆን በዕለቱም በመገኘት የፈተና ወረቀት (ውጤት) እንድትወስዱ እንዲሁም በሁሉም የትምህርት ዓይነት ከ100 ያላችሁን ውጤት እንድትመለከቱና እንድታረጋግጡ እናሳስባለን።

ማሳሰቢያ
በዕለቱ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ስትመጡ: -

የትምህርት ቤቱን ሙሉ የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) ብቻ አድርጋችሁ ብቻ ነው መምጣት የሚቻለው።

የትምህርት ቤቱን መታወቂያም መያዝ እንደሚኖርባችሁ እናሳስባለን።

የትምህርት ቤቱን የደንብ ልብስ  (ዩኒፎርም) ሳይለብስ እንዲሁም የትምህርት ቤቱን መታወቂያ ያልያዘ ተማሪ ወደ ትምህርት ቤቱ ግቢ እንደማይገባ እንገልፃለን።

ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

18 Jan, 09:05


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለመላው የት/ቤታችን የክርስትና እምነት ተከታይ

             መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣
        የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ

ለመላው የት/ቤታችን የክርስትና እምነት ተከታይ ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለከተራ እና ጥምቀት በዓል  አደረሳችሁ እያልን በዓሉ  የፍቅር፣ የሠላም፣ የጤና እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።


                       መልካም  በዓል!

                                                          ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

12 Jan, 16:12


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለ12ኛ ክፍል የተማሪ ወላጆች  እና ተማሪዎች በሙሉ

የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና እንደሚወስዱ ይታወቃል። ተማሪዎች ለዋናው የብሔራዊ ፈተና እንዲዘጋጁበት በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተዘጋጀ የሞዴል ፈተና ከማክሰኞ 06 - ሐሙስ 08/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ይታወቃል።

በመሆኑም ተማሪዎች ለፈተናው በቤታቸው ሆነው ዝግጅት እንዲያደርጉ ነገ ማለትም ሠኞ በቀን 05/05/2017 ዓ.ም ለ12ኛ ክፍሎች ብቻ ትምህርት የማይኖር መሆኑን እየገለፅን ተማሪዎች በፈተናው መርሀ ግብር መሠረት ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።



                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

09 Jan, 16:34


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

                  ለ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል 
           የተማሪ ወላጆች  እና ተማሪዎች በሙሉ

የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን  የ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ኦን ላይን (Online) ፎርም መሙላት መጀመሩ ይታወቃል። በመሆኑም ፎርም የሚሞላበት የመጨረሻ ቀን ጥር 4  ቀን 2017 ዓ. ሲሆን ጥር 5 እና 6  የተማሪዎች መረጃ ተጣርቶ ወደ ትምህርት ሚኒስተር የሚላክበት ቀናቶች መሆኑን አውቃችሁ እስካሁን  ፎርሙን ያልሞላችሁ ውስን  ተማሪዎች በሙሉ ነገ ማለትም በቀን በ02/05/2017 ዓ.ም በት/ቤቱ ግቢ በመገኘት እንድትሞሉ እያሳሰብን ሟሟላት የሚጠበቅባችሁን ክፍያ በማጠናቀቅ የከፈላችሁበትን  የባንክ ደረሰኝ ይዛችሁ በመምጣት እንድትሞሉ ስንል እናሳስባለን።

ማሳሰቢያ: -  በት/ቤት ባለመገኘት  ፎርሙን ባለመሙላት ለሚፈጠረው ክፍተት ት/ቤቱ ኃላፊነቱን  የማይወስድ መሆኑን እንገልፃለን።

                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

07 Jan, 07:18


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ከገና በዓል ተያይዞ ነገ ረቡዕ ማለትም በቀን 30/04/2017 ዓ.ም ትምህርት የማይኖር መሆኑን እንገልፃለን።

ከሐሙስ 01/05/2017 ዓ.ም ጀምሮ ግን መደበኛው የመማር ማስተማር የሚቀጥል መሆኑን እንገልፃለን።

                                                    ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

06 Jan, 12:16


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለመላው የት/ቤታችን የክርስትና እምነት ተከታይ

             መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣
        የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ

ለመላው የት/ቤታችን የክርስትና እምነት ተከታይ ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለገና  በዓል አደረሳችሁ እያልን በዓሉ  የሠላም፣ የጤና እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።


                       መልካም  በዓል!

                                                          ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

05 Jan, 11:18


#Update

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ጥር 6/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ስለሆነም ምዝገባ ያላጠናቀቃችሁ ተማሪዎች ከቀነ ገደቡ አስቀድማችሁ እንድታጠናቅቁ አገልግሎቱ አሳስቧል።

አገልግሎቱ የ2017 ዓ.ም ፈተናዎች ይዘትን በተመለከተ ባስተላለፈው መልዕክት፤ የሀገር አቀፍ 12ኛ ክፍል ፈተና በአጠቃላይ ከ 9-12ኛ ክፍሎች እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከ7-8ኛ ክፍሎች እንደሚሸፍን ገልጿል።

ተማሪዎች በተማሩበት የክፍል ደረጀ የተማሪ መጽሐፍን መሠረት አድርገው ሊዘጋጁ እንደሚገባ አገልግሎቱ ጠቁሟል።

@tikvahuniversity

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

22 Dec, 20:06


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለ12ኛ ክፍል የተማሪ ወላጆች  እና ተማሪዎች በሙሉ

የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና እንደሚወስዱ ይታወቃል። በመሆኑም ከመንግሥት በወረደው መመሪያ መሠረት የመፈተኛ ክፍያ በተማሪ 750 (ሰባት መቶ ሀምሳ ብር) ስለተጠየቅን ከሠኞ ታህሳስ 14 እስከ ረበዕ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም በተሰጠው የጊዜ ገደብ በልጅዎ በኩል ክፍያውን እንዲፈፀሙ በአክብሮት እንጠይቃለን።

                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

14 Dec, 09:06


"Names and Formulas of Chemical Elements!"

🔺 Common salt = NaCl
🔺Baking soda = NaHCO₃
🔺 Washing soda = Na₂CO₃ 10H₂O
🔺Caustic Soda = NaOH
🔺Suhaga = Na₂B₄O₇ 10H₂O
🔺 Alum = K₂SO₄ Al₂(SO₄)₃ 24H₂O
🔺Red medicine = KMnO₄
🔺 Caustic Potash = KOH
🔺Saltpeter = KNO₃
🔺Bleaching powder = Ca(OCl)Cl
🔺 lime water = Ca(OH)₂
🔺Gypsum = CaSO₄ 2H₂O
🔺 Plaster of Paris = CaSO₄ ½H₂O
🔺Chalk = CaCO₃
🔺Limestone = CaCO₃
🔺 Marble = CaCO₃
🔺Nausadar = NH4Cl
🔺Laughing gas = N₂O
🔺 Litharge = PbO
🔺 Galena = PbS
🔺Red vermilion = Pb₃O₄
🔺White lead = 2PbCO₃ Pb(OH)₂
🔺 Salt acid = HCl
🔺Shore's acid = HNO₃
🔺Amalraj = HNO₃ + HCl (1 : 3)
🔺Dry ice = CO₂
🔺Green Case = FeSO₄ 7H₂O
🔺 Horn Silver = AgCl
🔺 Heavy water = D₂O
🔺Producer gas = CO + N₂
🔺Marsh gas = CH₄
🔺Vinegar = CH₃COOH
🔺Gemaxine = C₆H₆Cl₆
🔺Blue Case = CuSO₄ 5H₂O
🔺alcohol = C₂H₅OH
🔺 Mand = C₆H₁₀O₅
🔺Grape juice = C₆H₁₂O₆
🔺sugar = C₁₂H₂₂O₁₁
🔺 Urea = NH₂CONH₂
🔺 Benzene = C₆H₆

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

22 Nov, 15:00


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለ11ኛ ክፍል የማህበሪዊ ሳይንስ
(Social Science) የተማሪ ወላጆች  እና ተማሪዎች በሙሉ


በባለፈው ቅዳሜ ሊሰጡ ከታሰቡት ፈተናዎች መካከል ኢኮኖሚክስ ፈተና እንዳልተሠጠ ይታወቃል። በመሆኑም የኢኮኖሚክስ ፈተና በነገው ዕለት ማለትም በቀን 14/03/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ እየገለፅን ተማሪዎችም ይህንን በመገንዘብ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ ለመግለፅ እንወዳለን።

                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

10 Nov, 12:12


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

                  ለሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
           የተማሪ ወላጆች  እና ተማሪዎች በሙሉ

የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ዙር ፈተና ከጥቅምት 28 - 30/2017 ዓ.ም ደረስ መሠጠቱ ይታወቃል። ሆኖም ግን ከ9ኛ -12ኛ ክፍል የተወሰኑ የትምህርት ዓይነቶችን በጊዜው እንዳልተፈተናችሁ ይታወቃል። በመሆኑም እነዚህን የትምህርት ዓይነቶች የፊታችን ቅዳሜ ማለትም በ07/03/2017 ዓ.ም የምትፈተኑ መሆኑን እየገለፅን ተማሪዎችም አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ ለመግለጽ እንወዳለን።

፨ ከነገ ሠኞ 02/03/2017 ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት የሚቀጥል ይሆናል። በመሆኑም ተማሪዎች ይህን አውቃችሁ ለትምህርት በሠዓታችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን።

፨ ከነገ ሠኞ 02/03/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ወደ ት/ቤት የመግቢያ በር የተቀየረ መሆኑን እየገለፅን አዲሱ መግቢያ በርም በሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ቤተ መፅሐፍት (Library) ፊት ለፊት ወይም መኪና በሚገባበት በኩል መሆኑን እንገልፃለን።

                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

08 Nov, 18:21


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

                  ለ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል
           የተማሪ ወላጆች  እና ተማሪዎች በሙሉ

የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ዙር የ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ፎርም መሙላት ዛሬ መጀመሩ ይታወቃል። በመሆኑም በዛሬው ዕለት ፎርሙን ያልሞላችሁ ተማሪዎች በሙሉ ነገ ማለትም በቀን በ30/02/2017 ዓ.ም የመጨረሻው ቀን መሆኑን አውቃችሁ ሟሟላት የሚጠበቅባችሁን ክፍያ በማጠናቀቅ የከፈላችሁበትን የባንክ ደረሰኝ ይዛችሁ በመምጣት እንድትሞሉ ስንል እናሳስባለን።

ማሳሰቢያ: -  በት/ቤት ባለመገኘት  ፎርሙን ባለመሙላት ለሚፈጠረው ክፍተት ት/ቤቱ ኃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን እንገልፃለን።

                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

08 Nov, 18:21


ቀን 29/2/2017 ዓ.ም

አስቸኳይ (ማስታወቂያ)
ለሁሉም የ12ኛ ክፍል አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች :-
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች የሚታስፈትኗቸውን ተፈታኞች ዝርዝር (school list) ወይም የተፈታኝ ተማሪዎች ዝርዝር እስከ ጥቅምት 30/2017ዓ.ም 4፡30 ሰዓት ድረስ ባለው ተዘጋጅቶ በዋና /ር/መምህር ተፈርሞ በሶፍት እና ሃርድ ኮፒ እንዲላክልን እያሳስብን በተቀመጠው ሰዓት እና ጊዜ ያልላከ ትምህርት ቤት ኃላፊነት ራሳች እንድምትወስዱ እናሳውቃለን ፡፡

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

08 Nov, 16:36


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

     ለ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ

የ2016 ዓ.ም የአገር አቀፉ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ እና የሪሚድያል መግቢያ ይፋ መደረጉ ይታወቃል። በመሆኑም የሪሚድያል ነጥብ የመጣላችሁ ተማሪዎች ትምህርታችሁን በአልፋ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ መከታተል የምትችሉበትን መንገድ ት/ቤቱ ስላዘጋጀ ተማሪዎች የዚህ እድል ተጠቀሚ መሆን የምትችሉ መሆኑን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው።
                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

03 Nov, 06:54


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

            ለሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ

የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መስከረም 6/2017 ዓ.ም መጀመሩ ይታወቃል። በመሆኑም የመጀመሪያው ዙር ፈተና ከፊታችን ሐሙስ ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም እስከ ቅዳሜ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ድረስ የሚሠጥ መሆኑን እየገለፅን ተማሪዎችም አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

03 Nov, 06:54


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ

የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መስከረም 6/2017 ዓ.ም መጀመሩ ይታወቃል። የመማር ማስተማር ሂደቱን በአግባቡ እንዲቀጥል ከሚያስችሉት ነገሮች መካከል አንዱ የተማሪዎች መማሪያ መፅሐፍ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም የአዲስአበባ ትምህርት ቢሮ ባመቻቸልን ዕድል አዲሱ የተማሪዎች የመማሪያ መፅሐፍ ትምህርት ቤታችን ያስመጣ ስለሆነ ወላጆች ለልጆቻችሁ መፅሐፍቶቹን መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

አጠቃላይ የመጽሐፍ ዋጋ ዝርዝር

9ኛ ክፍል 2999 ብር

10ኛ ክፍል 3461 ብር

11ኛ ክፍል (Natural Science) 2690 ብር

11ኛ ክፍል (Social Science) 2056 ብር

12 ክፍል (Natural Science) 2595 ብር

12 ክፍል (Social Science) 2131 ብር



                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

15 Oct, 04:44


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

     ለ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ

የ2016 ዓ.ም የአገር አቀፉ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ እና የሪሚድያል መግቢያ ይፋ መደረጉ ይታወቃል። በመሆኑም የሪሚድያል ነጥብ የመጣላችሁ ተማሪዎች ትምህርታችሁን በአልፋ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ መከታተል የምትችሉበትን መንገድ ት/ቤቱ ስላዘጋጀ ተማሪዎች የዚህ እድል ተጠቀሚ መሆን የምትችሉ መሆኑን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው።
                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

14 Oct, 17:33


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

     ለ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ

የ2016 ዓ.ም የአገር አቀፉ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ከተደረገ በኃላ የመቁረጫ ነጥብ አምጥታችሁ ነገር ግን የዩኒቨርስቲ እና የፊልድ ምርጫ ያልመረጣችሁ ተማሪዎች የመምረጫ የመጨረሻ ቀን ነገ ስለሆነ በነገው ዕለት ማለትም በቀን 05/02/2017 ዓ.ም በትምህርት ቤት ግቢ በመገኘት እንድትመርጡ እያሳሰብን ይህን ባለማድረጋችሁ ለሚፈጠረው ክፍተት ት/ቤቱ ኃላፊነት አይወስድም።

                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

09 Oct, 19:48


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለመላው የትምህርት ቤታችን
         የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ

ውድ ወላጆች እና ተማሪዎች ነገ ሀሙስ ማለትም በቀን 30/12/2017 ዓ.ም አጠቃላይ የመምህራን ስብሰባ ስላለ ትምህርት  የሚኖረው እስከ 6:00 መሆኑን በትህትና እንገልፃለን። በመሆኑ አፀደ ህፃናት እና የመጀመሪያ ደረጃ የሚማሩ ተማሪዎችን 6 ሠዓት ላይ በመገኘት በሠዓቱ ልጆቻችሁን እንድትወስዱ እናሳስባለን።

ማሳሰቢያ: - አርብ በቀን 01/02/2017 ዓ.ም መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደትም የሚቀጥል ሲሆን ትምህርትም ሙሉ ቀን መሆኑን እንገልፃለን።

                                                              ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

09 Oct, 03:00


የአቅም ማሻሻያ (ሬሜዲያል) ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችለው የመቁረጫ ነጥብ ስንት ነው ?

በመንግስት ተቋማት ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ የሪሚዲያል ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎችን የመቁረጫ ነጥብ ፦

➡️ በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ የወንድ ተማሪዎች የሬሜዲያል የመግቢያ ውጤት ከ600ው 204 ነው።

➡️ በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ የሴት ተማሪዎች የሬሜዲያል የመግቢያ ውጤት ከ600ው 192 ሆኖ ተቆርጧል።

(ተጨማሪ የመቁረጫ ነጥብ ከላይ ተያይዟል)

ከዚህ ባለፈ ግን እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 31% ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች በሁሉም አማራጮች (በግልና በመንግስት ተቋማት) በራሳቸው ክፍያ የሪሚዲያል ፕሮግራም መከታተል ይችላሉ።

ይህ ማለት ፦

➡️ ከ600ው የትምህርት ብዛት ፈተናቸውን ተፈትነው 31% እና ከዛ በላይ ውጤት ያመጡ (186 እና በላይ) ፤

ከ500 የትምህርት ብዛት የተፈተኑ (ዓይነስውራን ተማሪዎች) 31% እና በላይ ውጤት ያመጡ (155 እና በላይ) ፤

ከ700ው የትምህርት ብዛት የተፈተኑ 31% እና ከዛ በላይ ውጤት ያመጡ (217 እና በላይ) ... በፈለጉት አማራጭ ማለትም በግል ሆነ በመንግሥት ተቋማት ከፍለው የሬሜዲያል ፕሮግራም መከታተል ይችላሉ።

በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና #በቀጥታ የሚያሳልፈው ውጤት 50% እና በላይ መሆኑ ይታወቃል።

የሬሜዲያል ፕሮግራም መቁረጫ ነጥብ (በመንግሥት ስፖንሰርሺፕ / ተመድቦ ለመማር) ከላይ በምስሉ ላይ ተያይዟል።

በግል ከፍለው በመንግሥትም ይሁን በግል ተቋም ለመማር የሚፈልጉ ከተፈተኑት ፈተና ውጤት 31% እና በላይ ውጤት ማምጣት አለባቸው።

@tikvahethiopia

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

09 Oct, 02:59


1. ማስታወቂያ

         የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል

በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
                     የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
                           መስከረም 2017

2.  ማስታወቂያ

በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለምትሹ ተማሪዎች ማመልከቻችሁን በ https://student.ethernet.edu.et በኩል ብቻ እንድትልኩ እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።
                የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
                                 መስከረም 2017

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

26 Sep, 20:01


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለመላው የት/ቤታችን የክርስትና እምነት ተከታይ

             መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣
        የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ

ለመላው የት/ቤታችን የክርስትና እምነት ተከታይ ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለደመራ እና መስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን በዓሉ  የሠላም፣ የጤና እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።

                       መልካም  በዓል!

                                                          ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

14 Sep, 18:38


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለመላው የት/ቤታችን የእስልምና እምነት ተከታይ
             መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣
       የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ


ለመላው የት/ቤታችን የእስልምና እምነት  ተከታይ ማህበረሰብ በሙሉ  እንኳን ለመውሊድ በዓል አደረሳችሁ እያልን በዓሉ የሠላም፣ የጤና እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።

መልካም የመውሊድ በዓል!

ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

10 Sep, 17:49


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

ለመላው የት/ቤታችን
መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣
የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ

ለመላው የት/ቤታችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለ2017 ዓ.ም አደረሳችሁ/አደረሰን እያልን አዲሱ አመት የሠላም፣ የጤና፣ የመተሳሰብ እና የስኬት እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።

መልካም አዲስ አመት ይሁንላችሁ/ይሁንልን!!!
                   
                                                               ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

31 Jul, 05:07


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

 የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ


የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የነባርም ሆነ
የአዲስ ተማሪዎችን ምዝገባ ከሐምሌ 01/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ  23/2016 ዓ.ም ምዝገባ ስናካሂድ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን የነባር ተማሪዎች  የምዝገባ ግዜም   የተጠናቀቀ የነበረ ቢሆንም  በወላጆች ጥያቄ መሠረት ምዝገባውን ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ሐምሌ 30/2016 ዓ.ም ድረስ እንደተራዘመ በአክብሮት እንገልፃለን።

ይህ በእንዲህ እንዳለ: -

KG1 ምዝገባ የጨረስን ሲሆን

ከKG 2 - 12 ክፍሎች ባሉን ውስን ቦታዎች ወላጆች በፍጥነት ልጆቻችሁን እንድታስመዘግቡ ስንል ለመግለፅ እንወዳለን።



በመሆኑም ምዝገባው የሚቆየው እስከ ሐምሌ 30/2016 ዓ.ም  ብቻ ስለሆነ ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች የምዝገባው ጊዜ ሳያልፍባችሁ እንድታስመዘግቡ ስንል በአክብሮት እየገለፅን ከሐምሌ 30/2016 ዓ.ም በኃላ የተማሪዎች ምዝገባ የምንጨርስ ሲሆን ማንኛውንም ወላጆች ሆነ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን።


                                                               ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

23 Jul, 05:53


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

 የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ


የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የነባርም ሆነ
የአዲስ ተማሪዎችን ምዝገባ ከሐምሌ 01/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ትናንት ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም ምዝገባ ስናካሂድ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን የነባር ተማሪዎች የምዝገባ ግዜም የተጠናቀቀ የነበረ ቢሆንም በወላጆች ጥያቄ መሠረት ምዝገባ እስከ ቅዳሜ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም ድረስ እንደተራዘመ በአክብሮት እንገልፃለን።


በመሆኑም ምዝገባው የሚቆየው እስከ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም  ብቻ ስለሆነ ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች የምዝገባው ጊዜ ሳያልፍባችሁ እንድታስመዘግቡ ስንል በአክብሮት እንገልፃለን።


                                                               ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

18 Jul, 08:08


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

                ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural  Science) የተማሪዎች ወላጆች  በሙሉ

                               ማስታወቂያ

የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ሀገር አቀፍ ፈተና ዛሬ የሚጠናቀቅ ሲሆን ተማሪዎችም በዛሬው ዕለት ወደ ቤት የሚመለሱ ይሆናል። በመሆኑም ወላጆች ከምሽቱ 12:30 ጀምሮ  በትምህርት ቤታችን ግቢ በመገኘት ልጆቻችንን መውሰድ እንደምትችሉ በአክብሮት እንገልፃለን።
                                                               ት/ቤቱ

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

16 Jul, 06:05


አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት

     የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ


የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የነባር እና አዲስ ተማሪዎችን ምዝገባ ከሐምሌ 01/2016 ዓ.ም ጀምሮ እንደ ጀመርን ይታወቃል።

በመሆኑም ምዝገባው የሚቆየው እስከ ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም  ብቻ ስለሆነ ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች የምዝገባው ጊዜ ሳያልፍባችሁ እንድታስመዘግቡ ስንል በአክብሮት እንገልፃለን።

                                                         ት/ቤቱ