የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት (@aasundayschool) Kanalının Son Gönderileri

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት Telegram Gönderileri

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
ይህ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ልሳን ነው።
10,161 Abone
3,317 Fotoğraf
37 Video
Son Güncelleme 05.03.2025 22:10

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት tarafından Telegram'da paylaşılan en son içerikler

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

04 Mar, 08:42

2,384

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የመጀመሪያውን መንፈቅ አመት የናሙና ምዘና ሰጠ።

እንደሚታወቀው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ወጥ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ማስተግበር ከጀመረ ዓመታት አስቆጥሯል ።

በዚህም መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ ያሉ ከ90% በላይ ሰንበት ት/ቤቶች እየተገበሩት ይገኛሉ ። በዚህም መሰረት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት 4 እርከኖች ያሉት ሲሆን ተማሪዎች ከአንዱ እርከን ወደሌላው እርከን ሲዘዋወሩ በሀገረ ስብከት ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነትም ይሔንን ምዘና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ እየሰጠ ይገኛል ።
በዚህ አመትም ሥርዓተ ትምህርቱን እየተገበሩ ከሚገኙ የ4ኛ ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል እያስተማሩ ለሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች የካቲት 22 እና 23 / 2017 ዓ.ም ከ130 በላይ በሚሆኑ ሰንበት ት/ቤቶች ላይ የመጀመሪያ መንፈቅ አመት ምዘና ሰጥቷል ።

በቀጣይም በዚህ አመት የማጠቃለያ ምዘናውን የሚዉስዱና ወደ ቀጣዩ እርከን (ክፍል ) መዛወር የሚችሉት እነዚህ ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን እንገልጻለን ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

03 Mar, 12:12

1,914

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲፪ኛ  ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል።

ምንጭ:- የኢ/ኦ/ተ/ቤ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

27 Feb, 06:25

3,103

ድርሳን ዘ ቅዱስ ኤፍሬም
ተግሣፅ

ሕይወትህን በአግባቡ መምራት ትፈልጋለህን? እንዲያውስ ትህትናን ተለማመድ፣ ያለትህትና ተገቢውን ህይወት መምራት አይቻልም። ስራህን ሁሉ በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጀምር። ያን ጊዜ ፍሬዎች ወደ መንግስተ ሰማያት ያደርሳሉ። ሰው ከትህትና ከራቀ ከትክክለኛው መንገድ ርቋል ማለት ነው። እግዚአብሔርን የተወ ሰው ርኩስ መንፈስ እንደ ሳኦል ያስጨንቀዋል። የጠላት ወጥመድ በማር የተቀባ ነው። በማር ጣዕም የሚማርክ ሰው ሀዘንን ሁሉ በያዘ ወጥመድ ይያዛል። ትህትናን ውደዱ፣ ያን ጊዜ ከሰይጣን ወጥመድ ውስጥ አትወድቁም። በትህትና ክንፍ በበረራችው ቁጥር ሁል ጊዜ ከጠላት ወጥመድ በላይ ትሆናላችሁ። ግልፍተኝነት እንደ በሰበሰ ረጅም ዛፍ ነው፣ ቅርጫፎቹ ሁሉ በቀላሉ የሚሰበሩ ናቸው። አንድ ሰው በወጣባቸው ጊዜ በወጣበት ከፍታ ወድያውኑ ይወድቃል። በመልካም ሀሳብ ልቦናው የበራ ሰው ግን ምስጉን ነው፣ ክብሩም ታላቅ እና ዘላለማዊ ነው ።
እንግዲ እራሳችንን ለመቆጣጠር እንጣር፣ ያን ጊዜ ኃጢያታችንን እንረዳለን።ያን ጊዜም ሁልጊዜ ራሳችንን ዝቅ እናደርጋለን፣ እንደ እባብ በእብሪት መወጠር እና ራሳችንን ከፍ ከፍ ከማድረግ እንቆጠባለን። እንግዲህ ራሳችንን ዝቅ ዝቅ ማድረግ እንውደድ፣ በንፁህ ልቦና ሆነን ምን አልባት የተሰጠንን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ከማቆሸሽ እንታደግ ይሆናል። መልካም ጸሎት በሳግ ና በእንባ የታጀበ ነው፣ በተለይ ደግሞ በምስጢር የሚፈስ እንባ። በልቦናው ከፍታ ሆኖ የሚፀልይ ጌታውን በፊቱ ያያል። እኛ የምንኖረው እና የምንሄደው በርሱ ፍቃድ ነውና። ልቦናችሁ ከጠነከረ በጌታችን ፊት አልቅሱ የእውቀትን ብርሀን ይገልጥላችዋል፣ ወደ እርሱ የሚወስዳችሁ አዲስ ልብን ይሰጣችኋል። ወንድምህን ብታስቀይም እግዚአብሔርን ታሳዝናለህ፣ ካንተ ጋር ካለው ከወንድምህ ጋር ሰላምን ከፈጠርክ ግን በሰማይ ካለው ከእግዚአብሔር ጋር ትታረቃለ። ወንድምህን በፍቅር ብትቀበለው፣ በደሉንም ይቅር ካልከው እግዚአብሔርን ተቀበለክ።
ስለዚህ በተናደዱ ሰዎች በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅ ፣ እንግዲ የተበሳጬትን በማስደሰት እግዚአብሔርን አስደስተው፣ በታሰሩት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን ጎብኘው፣ በተራቡት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አብላው፣ በታረዙ ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አልብሰው፣ መንገደኛን በመቀበል እግዚአብሔርን በአልጋ ላይ አስተኛ፣ እግሮቹንም እጠበው፣ በማዕድህም አስቀምጠው፣እንጀራህንም ከርሱ ጋር ተካፈል፣ ፅዋህንም ስጠው። እርሱ ታላቅ ፍቅሩን አሳይቶሀልና፣ እርሱ ስለ አንተ ብሎ ትበላው ዘንድ ሥጋውን ቆርሶልሀሰል፣ ትጠጣው ዘንድ ደሙን አፍስሷል።
ትርጉም እና ሐተታ
ዲ/ን መዝገቡ ከፍያለው
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

25 Feb, 03:41

4,743

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
#የፈተና_ማስታወቂያ
#የ2017_ዓ_ም #የ1ኛ ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ #የ4ኛ#የ8ኛ እና #የ10ኛ ክፍል የሙከራ(ሞዴል) ምዘና በሀገረ ስብከት ደረጃ እንደሚሰጥ ይታወቃል። በመሆኑም ምዘናው #የካቲት_22_ወይም_23_ሰንበት ት/ቤቱ ባለው መደበኛ መርሐ ግብር ላይ ስለሚሰጥ ከላይ የተጠቀሱትን ክፍሎች እያስተማራችሁ የምትገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ከወዲሁ ተማሪዎቻቹን እንድታዘጋጁ እናሳስባለን።

ምዘናው በአ/አ/ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል ተዘጋጅቶ በፒዲኤፍ በክ/ከተማቹ ትምህርት ክፍል በኩል የሚላክላቹ ሲሆን በየአጥቢያችሁ ፕሪንት በማድረግ በተጠቀሰው ቀን ምዘናውን የምታከናውኑ ይሆናል። ምዘናውን የወሰዱትን ተማሪዎች ውጤትና መረጃም ከምዘናው ጋር በሚላክላቹ ቅጽ መሠረት እንድትልኩልን ከወዲሁ እናሳስባለን።

#ምዘናው_የሚያካትታቸው_ትምህርቶች
~>4ኛ ክፍል/ከ1ኛ-4ኛ ክፍል/:- መሠረተ ሃይማኖት፣ ግእዝ እና ክርስቲያናዊ ሥነምግባር
~>8ኛ ክፍል/7ኛ እና 8ኛ ክፍል/:- መሠረተ ሃይማኖት፣ ግእዝ እና ክርስቲያናዊ ሥነምግባር
~>10ኛ ክፍል/9ኛ እና10ኛ ክፍል/:- ቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት (መጽሐፈ መነኮሳት)፣ ግእዝ፣ ጠቅላላ እውቀት (ጥናትና ምርምር ዘዴ)

#የሙከራ_ምዘናውን_ያልወሰደ_ተማሪ_የማጠቃለያ_ምዘና_መውሰድ_አይችልም!

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!!!

በአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል የምዘናና እውቅና ንዑስ ክፍል

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

24 Feb, 15:12

2,557

https://youtu.be/wWVzWMzdpM4?si=jl2dE1H1H8_cA32d
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

24 Feb, 15:09

2,214

https://youtu.be/wWVzWMzdpM4?si=zxK5ZEOMoXaMtFIp
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

21 Feb, 13:29

4,104

የግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት  የአገልጋይ እጦት እንደገጠመው ተገለጸ።

የመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የሚገኙ አባላት የልማት ተነሺዎች መሆናቸው አገልግሎቱን እንዳሰተጓጎለውም ተጠቁሟል። 

አቶ ዘውዱ ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሰብሳቢ ከማኀበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቆይታ በአካባቢው የሚኖር ሰውና ምእመን በመቀነሱ ሳምንታዊ ፕሮግራሞችን ወደ ወርሀዊ የመቀየር፣ሕጻናት ባሉበት ሆነው እንዲማሩ ዕድሉን እንዲያገኙ የማመቻቸት እና የኦላይን ትምህርቶችን ለመስጠት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ 

የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላቱ በኢኮኖሚያዊ፣በማኅበራዊ ጉዳዮች በተለይም በሃይማኖታዊ አንጻር ቃለ እግዚአብሔር እንዳይሰሙ ጫና እንደደረሰባቸው የሰንበት ትምህርት ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዘነበ ክፍሉ ተናግረዋል።

በአገልጋይ እጦት ምክንያት አንዳንድ ክፍሎች መታጣፋቸውን የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባል የሆኑት መቅደላዊት ተሾመ የተናገሩ ሲሆን ያሉትም ጥቂት አባላቶች ክፍሎችን ደርበው እንዲያገለግሉ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

በዚህም ችግሩን ለማቃለል በገዳሙ ውስጥ የሚገኙ አባቶችን በመጠቀም የሰንበት ትምህርት ቤት አባላቱ እንዲመጡ ቅስቀሳ የማካሄድ እና በወር አንድ ጊዜ ጉባኤ በማዘጋጀት እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን አባሏ አንስተዋል፡፡

ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ነው።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

16 Feb, 14:53

4,648

........"ይህ ታላቅ ምስጢር ነው ይህንን ስለ ቤተክርስቲያንና ስለ ክርስቶስ ነው እላለሁ" (2ቆሮ12:33) ስለምን" ታላቅ ምሥጢር አለው"? በዚህ ስፍራ ምሥጢሩን ግልፅ አድርጎ አቀረበልን። ይህን "ስለ ክርስቶስ እላለሁ" የሚለው ቃል "እግዚአብሄር ቃል" ከአባቱ በመውጣትና ወደዚህ ምድር በመምጣት ሙሽሪት ከተባለች ቤተክርስቲያን ጋር" ከጌታ ጋር የሚተባበር አንድ መንፈስቅዱስ ነው" 1ቆሮ6:16 እንዲህ አንድ አካል መሆኑን የሚያሳየን ነው።
ሆኖም ምሳሌያዊ አገላለፁ ባል ሚስቱን ሊወዳት ይገባል የሚለውን ትምህርቱን ከርዕሰ ጉዳዮ የሚወጣው አይደለም። ቢሆንም ቅዱስ ጳውሎስ :— ሆኖም ከእናንተ እያንዳዳችሁ የገዛ ሚስቱን እንዲ እንደራሱ አድርጎ ይውደዳት ሚስትም ባልዋን ትፍራ (ቁ 33)በማለት ወደ ተነሳበት ነጥብ ይመለሳል።
አዎን በእርግጥ ይህ ምስጢር ታላቅ ነው ያ ሰው በዚህ ምድር በመፈጠሩ ምክንያት የሆነውን የወለደውንና ያሳደገውን አባቱን በእርሱ ምክንያት ብዙ መከራ የተቀበለችሁን ስለ እርሱ ብላ የተጎሳቆለችውንና የተገላታችውን እናቱን እርሱን ለማሳደግ ብዙ ሀብታቸውን ያፈሰሱትን ወላጆቹን ትቶ አስቀድሞ ከማያውቃት አብረው ክፋ ና ደጉን ካልተካፈለችው ጋር አንድ ስጋና መንፈስ ይሆናል። በሁሉ ፊት ያከብራታል ፣ ያመሰግናታል ይህ በእርግጥ ታላቅ ምስጢር ነው።
ይህ ብቻ አይደለም ጋብቻው ሲፈፀም የእርሱ ወላጆች እና ዘመዶች ልጃቸው ከነርሱ ሲለይ አለማዘናቸው ነው። እንደውም እነርሱን ሊያሳዝን የሚችለው ልጃቸው ጋብቻን ባይፈፅም ነበር። እነርሱ ሀብታቸውን ለዚህ ታላቅ የደስታ ቀን ቢጠፋ እኳን ምንም ፀፀትአይሰማቸውም። በእርግጥ ይህ ምስጢር እጅግ ታላቅ የሆነ ምስጢር ነው።ይህ ምስጢር በውስጡ አንዳች የተደበቀ ጥበብን ይዞል......... ምንጭ :— የትዳር አንድምታ እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምሮ
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

01 Feb, 11:58

6,001

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  የግብጽ ኦርቶዶክስ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ልዑካንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸው ተገለጸ፡፡

ጥር ፳፬/፳፻፲፯ ዓ.ም

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበ ተክለ ሃይማኖት የግብጽ ኮፕቲክ ቤተርክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ታውድሮስ ሁለተኛ መልእክት ይዘው የመጡትን ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን የነጋዳን፣ ጉስ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሚካኤል ገዳም ሓላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ጥር ፳፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም አነጋግረዋል፡፡

ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን ኮፕቲክ ቤተርክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ታውድሮስ ሁለተኛ ያመጡትን መልእክት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ያቀረቡ ሲሆን በዚህም  ቅዱስነታቸው የግብጽ ኮፕቲክ ልዑካንን ተቀብለው በማነጋገራቸው መደሰታቸውን ገልጸው፤ ይህም የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናትን  አንድነት የሚያሳይ ነው ብለዋል ፡፡

በሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት መካከል ያለው ግንኙነት የጥንት መሆኑን ያስረዱት ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን “በግብጽ በርካታ ኢትዮጵያውያን ይኖራሉ፤ በዚያም ቤተክርስቲያን አላቸው ይጸልያሉ፡፡ የግብጽ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ለአማኞቿ አገልግሎት የምትሰጥበትን የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል  በጥሩ ሁኔታ ዕድሳት ተደርጎለት ተመርቆ ለአገልግሎት የሚጀምሩበትን ደብዳቤ ከቅዱስነታቸው መቀበላቸውን” አስረድተዋል፡፡

የሁለቱም አብያተ ክርስቲያንናት ግንኙነትም በጣም ጥሩ ነው ያሉት አቡነ ኤንገሎስ ኤልነጋዲ በኢትዮጵያ የግብጽ ቤተክርስቲያን ተወካይ እንደተናገሩት፤ በዚያም ቤተክርስቲያን አላቸው ይጸልያሉ፡፡ በኢትዮጵያም የግብጽ ቤተክርስቲያን አገልግሎቷን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳምና በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ታካሂዳለች፡፡
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

01 Feb, 11:58

6,008

ካቴድራሉም ተጠናቆ ተመርቆ ለአገልግሎት በመብቃቱ በጣም ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡ 

ልዑካኑ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ የግብጽ ኮፕቲክ ፓትርያርክ የተላከውን ስጦታ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስረከቡ ሲሆን ቅዱስነታቸውም ስለ ስጦታው አመስገነዋል። ልዑካኑም ስለተደረገላቸው መልካም አቀባበልና ይሁንታ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዕድሳቱ ተሠርቶ ማለቁ እጅግ ደስ እንዳሰኛቸው በመግለጽ የግብጽ ኮፕቲክ እንደተለመደው በካቴድራሉ መገልገል የሚችሉበት መንገድ ስለ ተመቻቸላቸው አመስገነዋል፡፡

ሜትሮፖሊታን በመጨረሻም ለኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ባስተላለፉት መልእክት “ኢትዮጵያውያን በእምነታችሁ ጠንካራ ክርስቲያኖች ናችሁ፡፡ የሰይጣን ፈተና በመላው ዓለም ለምንኖር ክርስቲያኖች ቢሆንም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፤ ፈተናውን ያሳልፍልናል፡፡ በቤተክርስቲያን ሁናችሁ ጸልዩ" ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ምንጭ :- የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት