ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

@yeferayemeles


ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

22 Oct, 04:41


ሰበር

ጥቅምት 11/2017

በአዲስ አበባ ምሽቱን በግዙፉ የገበያ ቦታ መርካቶ ከባድ የእሳት አደጋ ተፈጥሮ በርካታ መደብሮች በመቃጠል ላይ ናቸው።

እሳቱ በመርካቶ ሸማ ተራ የተነሳ ሲሆን፤ በርካታ መደብሮችን ከማውደሙ ባሻገር ወደህፃዎች በመዛመት ላይ ይገኛል።

በመድኒዋ ግዙፉ የገበያ ቦታ እንደዚህ ዓይነት የእሳት አደጋ አጋጥሞ እንደማያውቅ 'ይህ በዓይነቱ የተለየ ነው' ያሉት የዐይን እማኞች፤ ከአደጋው ጀርባ አገዛዙ እጁ እንደሚኖርበት ጥርጣሬቸውን ገልፀዋል።

ኦሕዴድ ብልጽግና የአዲስ አበባ ነባር የኢኮኖሚ ይዞታዎች ላይ ማንነትን መሠረት ያደረገ ንቅለ ተከላ ለመስራት የኮሪደር ልማት የሚል የዳቦ ስም በመስጠት የዜጎችን ሀብትና ንብረት በማፍረስ ላይ እንዳለ ይታወቃል። 

ከዋናው መንገድ ገባ ያሉ ቦታዎችን በተለይም የገበያ ማዕከላትን ደግሞ በእሳት አደጋ ስም መሰል ውድመት ማድረስ የኢኮኖሚ ንቅለ ተከላውን ለማሳለጥ እንደሚጠቀምበት ከሥርዓቱ ፋሽስታዊ ባህሪው መረዳት ይቻላል።

የብልጽግና አፈቀላጤዎች እሳቱን ለማጥፋት ሂልኮፕተር ለመጠቀም እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ነው ቢሉም እሳቱ በፍጥነት በመዛመት ላይ ነው። አደጋው ታቅዶበት የደረሰ እንደሚሆን የዐይን እማኞች ለጣና ቴቪ የአዲስ አበባ ሪፖርተር ተናግረዋል።

በጉዳዪ ላይ ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን።

ጣና ሳተላይት ቴሌቪዥን

ከሀቅ ጋር …!

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

21 Oct, 16:39


https://youtu.be/DWXW3P8B9AE?feature=shared

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

25 Sep, 23:52


"እኔ ለስንታችሁ ዋ ብዬ ልሙት…?"

የጎንደር ቀጠና የአማራ ፋኖ ውጊያ እንደዶፍ ዝናብ መውረዱን ቀጥሏል፡፡ የትግል መዝገብ ማስታወሻችን እንደሚያረጋግጠው ያለፉት ሃምሳ አንድ ቀናት ያለማቋረጥ ውጊያ ተካሂዷል፡፡

ከሐምሌ 26/2016 እስከ ነሐሴ 25/2016 ድረስ ለአንድ ወር የቀጠለው ‹‹ዘመቻ አይሸሽም›› እጅግ ስኬታማ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ያ ዘመቻ የመተማውን ድል ያመጣ፣ የፋኖን ድል ዓለማቀፋዊ ሚዲያዎች ሳይቀር የዘገቡለት እንደነበር ይታወሳል፡፡

በመቀጠል የመጣው ዘመቻ ‹‹ዘመቻ ኖላዊት ዘገየ›› ነበር፡፡ ይህ ዘመቻ ለተከታታይ አምስት ቀናት ቀጠሎ ደምቢያ ሰቀልት ላይ የምዕራባዊያን ኢምባሲዎችና ዲፕሎማቶች በወታደራዊ አታሼዎቻቸው ትንታኔ ያሰሩበት ታላቅ ወታደራዊ ድል ተመዘገበ፡፡

አዲሱን የድል ዓመት ከተቀበልን ጀምሮ ከመናገሻ ጎንደር በመቶ ኪሎ ሜትር ራዲየስ 12 ቦታዎች ላይ መደበኛ የጦር አውደ ውጊያ ተካሂዶ የፋኖ የውጊያ ልኬት ስታንዳርድ የተቀመጠበት ድል ተመዘገበ፡፡
ይህ ድል፣ የዓለም ቀይ መስቀል ማኀበር Geneva, Switzerland,  በሚገኘው ዋና መቀመጫው ቢሮ ጠረጼዛው ላይ የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዓለማቀፍ የጦር ሕግን ያከበረ፡- የምርኮኛ ተረከቡኝ ጥያቄ አጀንዳን ያስቀመጠ፣ የአማራ ትግል የመጨረሻው ከፍታ የታየበት ሆነ፡፡

የጎንደር ፋኖ በአደረጃጀት መለያየት የትግል ዓላማ ልዩነት ሳይፈጠርባቸው የድሉን መለኪያ ከፍ አድርገው ሰቀሉት፡- ስሜናዊው የጎንደር ግዛት ደባርቅ፣ ዳባት፣ ገደብየ፣ አምባጊዩርጊስ፤ በምዕራባዊው የጎንደር ቀጠና ድፍን አርማጭሆ፣ መተማና ረዥሙ የሱዳን መዋሰኛ መስመር እስከ ቋራ ጥግ፤ ምስራቃዊው የጎንደር ቀጠና ኪንፋዝ በገላን ይዞ በለሳ መና መቀጣ ቆላ ሐሙሲት ተከዜ ጫፍ፤ ወደደቡባዊው የጎንደር ግዛት ጋይንት፣ ስማዳ፣ ሰዴ ሙጃ፣ ጉና፣ እስቴ ሁለቱም ወረዳዎች፣ ደራን አካልሎ፣ በማህደረማርያም እስከ ደብረታቦር ጫፍ የደረሰው ድል እጅን በአፍ ያስጫነ ነበር፡፡

ይህ ድል አሁን ድረስ መነጋገሪያ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ በየቀኑ የማስታወሻ መዝገቤ ላይ የማሰፍራቸው የፋኖ ድሎች የዘመናችን የጀግንነት ፊደል በሥም ይገለጽ ቢባል የማን ተፅፎ የማን ሊቀር ነው በሚል ጭንቀት ውስጥ እገባለሁ፡፡

ለካ ወድዶ አይደለም… ፋሲል ደመወዝ ‹‹እኔ ለስንታችሁ ዋ ብየ ልሙት…?›› ያለው… የደረሰበት ያውቀዋል!!

በድል ቁንጣን ስላጨናነቁን ፋኖዎቻችን የጦር ሜዳ ውሎና ጀብዷቸው፡- ለትውልዱ መማሪያ፤ ለእውነተኛ የአማራ ብሔረተኝነት ግንባታ መሠረት አድርገን እንጠቀምባቸዋለን!!

ለሁሉም በጎንደር ቀጠና ቢፃፍ በቴራ ባይት የሚለካ የድል ታሪክ መሰራቱ ቀጥሏል!!

ብዙዎች መረጃው ያላቸው አልመሰለኝም ሁሉም የጎንደር ቀጠና የገጠር ቀበሌዎች ነጻ ወጥተዋል፡፡ ይህ መረጃ መናገሻ ጎንደርን ጨምሮ ለከተሞች የሚቀርቡ የገጠር ሳተላይት ቀበሌዎችን ጨምሮ ነው፡፡ ቀዩን መስመር ሳይጨምር ጎንደር ቀጠና 19 ወረዳ ሙሉ በሙሉ፤ 21 ወረዳዎች ደግሞ በከፊል በፋኖ ቁጥጥር ስር ናቸው፡፡ የብልጽግና አራዊት ሰራዊት በዋና ዋና የዞን ከተሞች ተከማችቶ ይገኛል፡፡ በጠላት እጅ የሚገኙ የወረዳ ከተማ አስተዳደሮች በማንኛውም ጊዜ በፋኖ ቁጥጥር ስር ሊውሉ የሚችሉ እንደሆነ በተደጋጋሚ ውጊያዎች ታይቷል፡፡

እንደታች ጋይንት፣ ስማዳ፣ ሰዴ ሙጃ፣ እስቴ፣ ቋራ፣ ኪንፋዝ በገላ፣ በለላ ቆላው፣ …ባሉ ነጻ ወረዳዎች ለአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ፋኖ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ የማዘጋጃ ቤት፣ የፍርድ ቤትና ሌሎች ማኀበራዊ ተቋማት አገልግሎት መስጠት የተጀመረባቸው ወረዳዎችም አሉ፡፡

የፋኖ አስተዳደራዊ ተቋም ምሁራንን ጭምር የሚያቅፍ በመሆኑ ነጻ በወጡ ወረዳዎች የምሁራን ሚና ጨምሯል፡፡ አማራ አሁን ትክክለኛውን የፖለቲካ ቁመና የሚያገኝበትን መዋቅር ከታችኛው የቀበሌ መዋቅር ጀምሮ በመዘርጋት ላይ እንደሆነ በጎንደር ቀጠና እያየን ነው፡፡

በቀጣይ የሌሎች የአማራ ግዛት ቀጠናዎችን መረጃ አጠናቅሬ እመለሳለሁ…

ያየነውን እንመሰክራለን! የምናውቀውን እንናገራለን!

©የፈራ ይመለስ

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

20 Sep, 10:24


ሰበር!

አጣናው ብርጌድ ካራማራ ብርጌድና አርበኞች ክፍለጦር  በጥምረት ስምሪት በርካታ የጠላትን ሀይል ሙትና ቁስለኛ እያረጉት ነው።
ቀጠናውን ለመቆጣጠር እያረጉት ባለው ተጋድሎ እስከአሁን ድረስ ከዙ 23 ጀምሮ ያሉ ጠላት ሚጠቀምባቸውን ከባድ መሳሪያወች እያቃጠሉ እየገሰገሱ ነው ።

ዝርዝር መረጃ ምናደርሳችሁ ይሆናል
የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ

መስከረም 10/2017

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

18 Sep, 20:08


አሁን ይሄ የዘመናችን ከሀዲ ጎንደር ውስጥ ወጣት ይለቀም እያለ ነው። ትናንት ታስሮ እያለ ግን የጎንደር ወጣት አንገረብ ድረስ በእግሩ እየተጓዘ ነው የጠየቀው። ሲፈታም ፕሮግራም አዘጋጅቶ ነው የጠበቀው። ቢካድ ቢካድ የጎንደር ወጣት ይካዳል። ከእነዛ የዋህ ቤተሰቦችህ እውነት ተፈጥረሃል? መጨረሻህን ያሳየን።

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

18 Sep, 17:17


አርበኛ ሀብቴ ወልዴ (ትልቁ)

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዋና አዛዥ
ከተከታታይ ወታደራዊ ድሎች በኋላ ከ "አንከር ሚዲያ" ጋር ያደረገው ቆይታ በአጭሩ ሲቀርብ👇

❶. የድላችሁ ምስጥር ምንድ ነው…?

የድላችን ሚስጥር የምንታገልለት ዓላማ ፍትሐዊና እውነተኛ በመሆኑ፤ የአማራ ሕዝብ ድጋፍ ስላለን ነው፡፡

በጠላት በኩል ብንመለከት የብልጽግና አገዛዝ የከፈተው ጦርነት የዘር ማጥፋት ዓላማ ያለው፤ የብልጽግና ሰራዊት ደግሞ የሚዋጋለትን ዓላማ አያውቅም፡፡

ስለዚህ እኛ ለዓላማችን ለመሰዋት ቆርጠን ሕዝብን ደጀን አድርገን ነው የምንዋጋው፡፡ የብልጽና ሰራዊት ለምን እንደሚዋጋ እንኳ ሳያውቅ ወደሕዝብ የሚተኩስ፤ ከሕዝብ የተነጠለ አውሬ ነው፡፡

ውጊያው በሕዝብ ልጆች እና በሰይጣን ልጆች መካከል የሚደረግ ነው!

ሕዝብ ሁሌም አሸናፊ ነው!! ፋኖ ደግሞ የአማራ ሕዝብ ልጅ ነው፡፡ ከአማራ አልፎ በርካታ ኢትዮጵያዊያን በተስፋ የሚጠብቁት የነጻነት ታጋይ ነው!!

በአጭሩ የድላችን ሚስጥር እኛ የምንሞትለት ዓላማ አለን፤ ጠላት ደግሞ የሚሞትለት ዓላማ የለውም፡፡ እኛ የሕዝብ ድጋፍ አለን፤ ጠላት ደግሞ ከሕዝብ የተነጠለ ብቻ ሳይሆን የአማራ መሬት የከዳው በመሆኑ ድሉ የእኛ ሆኗል!!

❷. ምርኮኞችን በተመለከተ…

በቅድሚያ የምርኮኛ አያያዛች ሰበዓዊነት ያለው ዓለማቀፍ የጦርነት ሕጎችን ያከበረ እንደሆነ ዓለም እየታዘበ ነው፡፡ የዚህ መነሻ ግን የአማራ ባህል ነው፡፡

የአማራ ባህል በፋኖ ትግል ውስጥ ትልቅ ቦታ ይሰጠዋል፡፡ ለዚህም ነው ሁለት ሦስት ጊዜ የማረክናቸውን ምርኮኞች ሳይቀር በእንክብካቤ የያዝናቸው፡፡

በእኛ በኩል ለምርኮኞች ስለትግላችን መነሻ፣ ስለ አማራ ሕዝብ ትክክለኛ ገጽታ፣ እናስተምራቸዋለን፡፡ ፍላጎት ያለው ትግሉን ይቀላቀላል፤ ፍላጎት የሌለውን ደግሞ ወደየ ቤተሰቡ እንሸኛለን፡፡ አሁን ግን ይህን ማድረግ የሚያስችል አቅም የለንም፡፡
የምግብ፣ መድሐኒትና አልባሳት ወጭውን አልቻልነውም፡፡ በፊትም ሕዝቡ ነው የሚቀልባቸው፤ አልባሳትና መድሐኒት የሚያቀርብ፡፡ አሁን ግን ቁጥሩ ስለበዛ የዓለም ቀይ መስቀል ማኀበር ሰብዓዊ እርዳታ እንዲያደርግ በይፋ ጠይቀናል፡፡

ወታደራዊ መረጃ በመሆኑ የምርኮኛ ቁጥር አልነግርህም፤ ነገር ግን አሁን በዚህ ሰዓት ራሱ የፈረሰው የብልጽግና ሰራዊት መማረኩን ቀጥሏል፡፡ ይህን ሁሉ ምርኮኛ ለመቀለብ አንችልም፡፡

እጃችን ላይ ያለው ምርኮኛ ቁጥር በዐቢይ አሕመድ እጅ ካለው ሊበልጥ ነው፡፡

አሁን እንደአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ፡- የምርኮኞች አስተዳደር መምሪያ ልናደራጅ አስበናል፡፡

ከምርኮኛው ብዛት አኳያ ራሱን ችሎ በመምሪያ ደረጃ መታየት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ ሥራ አስፈጻሚው ወስኖ ወደሥራ እንገባለን፡፡

❸. በጎንደር ቀጠና ዕለቱም ዕዞች የጋራ ኦፕሬሽንን በተመለከተ…

ለአንድ ዓላማ በጋራ እየተሰዋን ያለነው፡፡
በዚህ ትግል ውስጥ እንኳንስ ፋኖ ነኝ ብሎ በአደረጃጀት የታቀፈ ቀርቶ ለረዥም ዓመታት በጥቁር ደም የሚፈላለጉ ወገኖቻችን ደም እያደረቅን ወደትግሉ እያስገባን ነው፡፡

የኔ አንዱ ሥራ የትግሉን ሕዝባዊ መሰረት ማስፋት በመሆኑ እንኳንስ በሌላ አደረጃጀት ያሉ ወንድሞቼን ከፋኖ ውጭ ያለው አርሶ አደር፣ ወጣት፣…ሁሉም የትግሉ አካል እንዲሆን አመራር መስጠትና መከታተል ነው፡፡

ጥቁር ደም አድርቀን፤ ለአንድ ዓላማ የምናሰልፍ መሪዎች ነን፡፡ እና ሁለቱም ዕዝ ለአንድ ዓላማ በጋራ መስዋዕትነት እየከፈልን ድል እያዋሃደን ይሄዳል፡፡ ድል ካለ ፍቅር አለ! ድል ካለ አንድነት አለ! ለዚህ ሁሉ መሰረቱ ግን ለትግል የወጡበትን ዓላማ አለመርሳት ነው፡፡

እኛ የምንታገለው ለአማራ ሕዝብ ነጻነት ነው! አማራነትን ማተቡ ያደረገ ወንድሙን አይከዳም! እኛ የአጼ ቴዎድሮስ ልጆች ነን! ቃል አለብን!!

ከአንድነት ውጭ ሌላ ቋንቋ አይገባንም!! ከቴዎድሮስ መንገድ አንወጣም!!


❹. ሕዝብ ከፋኖ ጎን መቆሙን አሳይቷል፡፡ ትግሉ በደረሰበት ምዕራፍ የሕዝብ ሚና ምንድነው…?

ሕዝባችን ከእኛ ጋር መሆኑን ደጋግሞ አሳይቶናል፡፡ የብልጽግናን ሴራ በሙሉ ተረድቷል፡፡

አሁን ዐቢይ አሕመድ እጁ ላይ የሴራ ካርዶቹን በሙሉ መዞ ጭርሷል፡፡ ርቃኑን ቀርቷል፡፡

ትግሉ አሁን በደረሰበት ምዕራፍ የሕዝብ ሚና፡-

አንደኛ፡- የትግሉ ባለቤት ሆኖ በፅናት እንዲቀጥል፣

ሁለተኛ፡- ሥርዓቱ የፈረሰ በመሆኑ በያለበት ተደራጅቶ ራሱን እንዲጠብቅ፣

ሦስተኛ፡- ትግሉ አድማሱን እያሰፋ በመሆኑ ወጣቶች አሁንም ፋኖን እንዲቀላቀሉ፣

አራተኛ፡- ምሁራን አሁን ሕዝባችሁን ለማገልገል ምትፈለጉበት ሰዓት ነው፤ ራሳችሁን አዘጋጁ
ነው የምለው፡፡

❺. ትግሉ የማይቀለበስ ደረጃ እንደደረሰ ተረጋግጧል፡፡ የብልጽግና ሰራዊት ተንዷል፡፡ በናንተ በኩል በፈረሰ ሥርዓት ውስጥ የእሳት ራት እንዳይሆን የምታስተላልፉት መልዕክት ካለ…?

ብአዴን ሞቷል፤ አሁን የቀረን መቅበር ብቻ ነው፡፡ ባህርዳር ያለው ካቢኔ የጨረቃ ካቢኔ ነው!
ለፖሊስ፣ ሚሊሻና አድማ ብተና የማስተላልፈው መልዕክት በፈረሰና በሞተ ሥርዓት ውስጥ አላስፈላጊ መስዋዕትነት አይከፈሉ፡፡ እጃቸውን ይስጡ!!

ከመቀበር ለማያድኑት ሙት ሥርዓት የውሻ ሞት አይሙቱ!!

በጊዜ እጅ ሰጥተው የምህረት አዋጃችን ተጠቃሚ ይሁኑ!!

❻.በመጨረሻም የቀረ መልዕክት…

አሁን ባለን የውጊያ ቁመና ጎንደር ከተማና ባህርዳር ለእኛ ኢምንት ናቸው!

የገነባነው ተዋጊ ኃይል ዐይኑ አራት ኪሎ ላይ ነው!!

ይሄ ኃይል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጦር የመሆን አቅም አለው!!

ዋናው የትግላችን ትኩረት የሞተውን ሥርዓት በመቅበር ላይ ነው፡፡ አፈር መመለስ ላይ ነን፡፡ አፈር መልሰን ከጨረሰን መንገዱ ክፍት ነው!!
በእርግጠኝነት የምናገረው የመጨረሻውን ሳቅ የሚስቀው አማራ ነው!

ስለዚህ ሕዝባችን የመጨረሻውን ሳቅ ለመሳቅ ከፋኖ ትግል ጋር በፅናት ይቀጥል!!

አመሰግናለሁ!!

ሻለቃ ሀብቴ ወልዴ (ትልቁ)

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዋና አዛዥ
ጎንደር፣ አማራ፣ ኢትዮጵያ

ሙለ ቃለ-መጠይቁ ከስር ተያይዟል
👇👇
https://youtu.be/dgDMNMBWK84?feature=shared

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

18 Sep, 10:41


ብዙዎቹ በተለየ መንገድ የጎንደርን ህዝብ ያዋረዱ መስሏቸው በነገ በጠባ በለፈለፉ ቁጥር የተራራቀውን አቀራርበውታል፣ ያልገባውን እንዲገባው አድርገውታል፣ ወዳጅና ጠላቱን እንዲያውቅ አድርገውታል። ጌታቸው ረዳ እና ሽመልስ አብዲሳ የአማራን ህዝብ ከጫፍጫፍ እንዲነሳ እንዳደረጉት ይሄም ተመሳሳይ ነው።

ሌላው ለእንደነዚህ ዓይነቶቹ መልስ መመለስ አያስፈልግም። የሚፈልጉት ስማቸው ተጠርቶ እንደ ተፅዕኖ ፈጣሪ መልስ እንዲመለስላቸው ነው። በጭራሽ ስማቸውን የሚጠራው የለም። ትልቁ ቁም ነገር ጎንደር ላይ በደንብ ጠላትን እየቀጠቀጡ ማን እያጎረሰ እንደሚያስለፈልፋቸው ማወቁ ላይ ነው። ዋናው ጠላት አጉራሻቸው ነው።

ድል ለፋኖ

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

18 Sep, 06:19


ጠላትን በቀይና በቢጫ ቀለም አቅልሞ መዝግቦ መያዝ ነው። ቀዩ ቀለም ወዳጅ ሊሆን የማይችል ጠላት ሲሆን በቢጫ ቀለም መዝግበህ የምትይዘው ደግሞ ወደ ወዳጅነት ሊቀየርም ላይቀየርም ይችላል። ወዳጅና ጠላቱን ለይቶ የሚጓዝ ሁሌም ውጤታማ ይሆናል። አማራ ሁሌም ማስታወሻና እና ቀይና ቢጫ እስክብሪቶ ከእጁ መለየት የለበትም።

ድል ለህዝባችን

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

18 Sep, 05:30


ይሄ አዲሱ የፌስቡክ አካውንቴ ነው።

https://www.facebook.com/profile.php?id=61565171657961

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

18 Sep, 05:05


ጎንደር ላይ ጠላት ሲቀጠቀጥ ገና ሰምተናቸው የማናውቅ ድምፆችን ሁሉ እንሰማለን። በይፋ ከብአዴን ጎን ሁነን ጎንደርን እናጠቃለን ሁሉ ሊባል ይችላል። አማራዎች አይግረማችሁ። የህውሃትም ሆነ የብልፅግናና እና የማደጎዎቿ ተስፋ ጎንደር ከተመታ ሌላው እዳው ገብስ ይሆናል ነው። ይሄ ደግሞ መሆን አልቻለም። ሊሆንም አይችልም። ገና የቀረ ጠላት ከጎንደር ምድር እየፀዳ ሲሄደድ አዳዲስ ክስተቶች ይከሰታሉ። መፍትሄው መልስ ሳትሰጥ ዝም ብለህ ምታ ነው።

ድል ለፋኖ

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

18 Sep, 05:01


ፌስቡኬ ተዘግቷል በአዲስ እስክመጣ በዚሁ መረጃዎችን አጋራለሁ።

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

16 Sep, 16:28


ጀማል ሲሳይ ይባላል። የደባርቅ ከተማ ትም/ጽ/ ቤት ምክትል ሃላፊ ነው። መሀል ደባርቅ ላይ ሁኖ የሀይማኖት ግጭት ለመፍጠርና የፋኖን የህልውና ትግል ፅንፈኛ እያለ ለአለቆቹ ተላላኪነቱን እያሳየ ይገኛል። እንዲህ ዓይነቱ ፅንፈኛ ነው አገር እየበጠበጠ ያለው። እንግዲህ ከኛ ጥርስ ገብተሃል ተወጣው።

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

16 Sep, 15:25


ይች ሰው ደባርቅ ትገኛለች። አብይ ሆይ ፋኖን በድሮን ጨፍጭፍልን እያለ ነው። በለፈለፉ ይጠፉ ነው ነገሩ።

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

16 Sep, 14:33


የደምቢያ አጠቃላይ ሁኔታ በተመለከተ
ጠላት የሱዳንን ኮሪደር አስከፍታለሁ በሚልና በባለፈው የደረሰበትን ምት ምክንያት በማድረግ በቀጠናው ያለውን ሁኔታ በአግባቡ በቁጥጥር ለማድረግ በአይነቱ ሰፋ ያለ ኃይል ከተለያዩ አካባቢዎች አጓጉዞ ነው ከባድ ትንቅንቅ እያደረገ ያለው ቢሆንም የጎንደር ዕዞቹ ከጯሂት በቅርብ ርቀት ላይ ቀድሞ እየተተራመሰ የመጣውን ኃይል አይቀጡ ቅጣት እየሰጡት ለእሱ ሽፋን ሊሰጥ የገባውን ኃይል ደረስጌ ላይ ቀድመው እየለበለቡት የሚገኙ ሲሆን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኃይል መግቢያ መውጫ አጥቶ ውሏል ከአዘዞ በቀጥታ የሚተኮስ ጀኔራል መድፍ በየአርሶ አደሩ ማሳ ላይ ከባድ ጉዳት እያደረሰ እንዳለ እስከአሁን በሰብአዊ ሰው ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት በተመለከተ መረጃዎችን ለማጠናቀር ይሞከራል

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

16 Sep, 13:32


ሰበር ዜና

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ሰሜን አንባራስ ክፍለጦር በሻለቃ ሻምበል የሚመራው የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ይታየው ማሬ ብርጌድ በሻለቃ ንጉስ ፈረደ የሚመራው የአማራ ፋኖ ጎንደር በናሁሰናይ አንዳርጌ ብርጌድ በሻለቃ ዋናው አሙሀይ የሚመራ የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ምስጋናው አጠኔ ብርጌድ በሻለቃ አገርነው ምስጋናው የሚመራ የዳባት ከተማን በጥምረት ተቆጣጥረውታል።በቀጣይ በዝርዝር ሙሉ መረጃ ይዘን እንመለሳለን።

ዛሬ በዳባት ፀሀይ አትጠልቅም 💪💚💛❤️

ክብር ለጀግኖቻችን
አማራ በልጆቹ ታሪኩን ያድሳል

መረጃው የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ነው።

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

16 Sep, 13:28


ፌስቡክ አስቸግሮኛል። ይሄን ቴሌግራም የምትከተሉ መልዕክቶችን አሠራጩልኝ።

ሙላት አድኖ(የፈራ ይመለስ)

15 Sep, 14:40


የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የቴሌግራም ገጽ
👇
👇
👇
https://t.me/AmharaFanoGonderCommand