ማስታወቂያ!
ለመላዉ የተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ነባር ሰልጣኞች እና እንዲሁም በ 2017 ዓ.ም በኮሌጃችን በመደበኛ እና በአጫጭር ስልጠና ተመዝግባችሁ መሰልጠን ለምትፈልጉ ሁሉ በቅድሚያ እንኳን ለ2017 ዓ.ም የስልጠና ዘመን በሰላም አደረሳችሁ፡፡
እንደሚታወቀዉ የ2017 ስልጠና ዘመን የነባር የቀን ሰልጣኞች ምዝገባ የሚካሄደዉ ከ ሰኞ 13/01/2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 15/01/17፤ የማታ ከዚህ ቀደም ባሳወቅናችሁ ቀናት ሲሆን የአዲስ ሰልጣኞች ምዝገባ ደግሞ በቀጣይ በቅርብ ቀን የምናሳዉቅ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
በሌላ በኩል በስልጠና ዘመኑ በጣም ወሳኝ የሆኑ እናንተን ያሳድጋሉ ያልናቸውን ስልጠናዎች ማለትም ልል ክህሎት(Soft Skills; Innovation, Digital literacy, Entrepreneurial skill, problem solving skills and Communication skill) እና ሌሎች በርካታ ስልጠናዎችን በኮሌጃችን የምንሰጥ ይሆናል፤ እነዚህን ስልጠናዎች ደግሞ የምንሰጣችሁ ከዚህ በፊት በቴሌግራም ቻናል ላይ በተለቀቀላችሁ ACT Academy በሚለዉ ሊንክ ገብታችሁ አካዉንት ስትከፍቱ ብቻ ነዉ፡፡
ስለዚህ ሁላችሁም ሰልጣኞች ከላይ የተዘረዘሩትን ስልጠና ለመዉሰድ አካዉንት መክፈት ግዴታ መሆኑን አዉቃችሁ ወደ ምዝገባ ስትመጡ በስማችሁ የከፈታችሁት አካዉንት Screen Shoot አድርጋችሁ መምጣት ይኖርባችኋል፡፡
ማሳሰበያ፡ ሁሉም ሰልጣኝ አካዉንት ከፍቶ ወደ ምዝገባ መምጣት ይኖርበታል።