ይላታል፡፡ማርያምን እኮ ነው...እዚህ ምድር ላይ ማንን ትጠላለህ ቢባል ቀድሞ የሚጠራው የማርያምን ስም ነው.....ሲሰድባት ለአፉ ለከት የለውም።ደሞ እጁ ላይ የያዘውን ድንጋይ ብታዩት ሀገር ይጨርሳል።በየአመቱ "አንቺን ብሎ ማርያም" እያለ እየዛተ ነው ያረጀው.....
አንቺን ብሎ ማርያም!!!አንቺን ብሎ አዛኝ!!አንቺን ብሎ እናት!!ደግ ብቶኚ እኔን ትበድያለሽ??ሀቄን ትወስጃለሽ?? ብቻዬን ትጥዪኛለሽ??አንቺ ብሎ ማርያም!! በዚ ዲንጋይ ነበር ማለት...
ንግሷ ተጀምሮ እስኪያልቅ በሯ ላይ ሲጎፈላ አምሽቶ በረድ ሲልለት ወደ ከተማ ይመለሳል።በአመተ ክብሯ እግዚኦ እየተባለ ቢለመን፤በሽማግሌ ቢመከር፤በጎረምሶች
ቢታሰርም እሱ ግድ አይሰጠውም።በአመቱ ያው እራሱ ጉልላት ሆኖ ነው ሚመጣው..አይለወጥም።
ዛሬ ጉልላት የት ሄደ?? ምነው ጭር አለሳ??( አለ ጓደኛዬ ገና ቤተክርስትያን እንደደረስን
አረ ሰአቱን ጠብቆ ይመጣል....ደሞ የሱ ነገር...አሁን ታቦቷ ሲወጣ ብቅ ይል የለ?(ብዬ ወሬዬን ከአፌ ሳልጨርስ አረንጓዴዋ ታክሲ ስትበር መጥታ አጠገባችን ቆመችና
ብዙ ወጣቶች ከመኪና ወርደው አንዳች ነገር ከመኪናው
ለማውጣት ሲጣደፉ የሁለታችንም ቀልብ መኪናዋ ላይ አረፈ...
በስመአብ ወወልድ ጉልላት!! አለ ጓደኛዬ ቀደም ብሎ...
ምንድነው ምን ተፈጠረ?? ብዬ እኔም ከአንገቴ ስንጠራራ ጉልላትን በደም የተለወሰ ፊት አይቼ ደንዝዤ ቀረሁ...
ወጣቶቹ ለሬሳ የቀረበ የተዝለፈለ አካሉን ተሸክመው ለንግስ በተሰለፈው ምእመን መሀል ሰንጥቀው ወደ ማርያም ግቢ ሲዘልቁ ከጓደኛዬ ጋ ሳናወራ ተጣድፈን ተከተልናቸው....
ምንድነው??ምን ጉድ ተፈጠረ??ጉልላት ምን ሆነ?? (አሉ አባ መቋሚያና ፅናፅላቸውን እንደያዙ ባዶእግራቸውን እየተጣደፉ መጥተው።ከማህሌቱ ተጠርተው እንደመጡ ያስታውቃል..
በዋዜማው ጠጅ ቤት ነበር አሉ...ጠዋት ማዞሪያ ድልድይ ውስጥ ወድቆ ነው የተገኘው። ሆስፒቲል አድርሰነው ቤት አስገቡት ደክሟል አሉ...ጉልላት ደሞ ቤት የለው....(አለ አንዱ ጎረምሳ
ውይ የአደራ ልጄን.... እኔን እኔን..በሉ ቤት አግቡት
አባ ካባቸውን እየሰበሰቡ ቤታቸውን ከፍተው ሲገቡ ገልላትን ይዘን ተከተልናቸው ቀድሞም መድሐኒት አዋቂ ናቸው።ቁስል እጃቸው ላይ አይበረክትም፤ህመም ከፊታቸው አይቆምም፤ ፀሎታቸው ጠብ አትልም፤እቤታቸው ገብተን እንደቆምን
በሉ ሂዱ ውጡ እናንተ... አይዟችሁ አሉ ሲጣደፉ።እሺ ብለን ወጣን ....
ቆይ የጉልላት ፀባይ ምንድነ?? ለምንድነው በዚህ ልክ ማርያምን ሚጠላት??አለኝ ጓደኛዬ እጁን አገጩ ላይ አድርጎ እንደተከዘ
ማርያም እናቴን ቀማቺኝ ነው ሚለው....እርግጥ ጉልላት ከልጅነቱም የተበደለ ነው።እናቱን በሰፈሩ የማያውቃት የለም።እሱን አርግዛ እስከምጧ ቀን ድረስ አሻሮ እየቆላች ቀንስራ እየሰራች እቺ ቤተክርስትያን ስትሰራ በጉልበቷ እና በደሀ ገንዘቧ ትረዳ ነበር።በኋላ ጉልላት ተወለደ።ያኔ የማርያም ቤተክርስትያንም እየተሰራ ጉልላቱ ላይ ደርሶ ስለነበር ልጇን ጉልላቴ አለችው።የሚገርመው ግን እሱ አይደለም... ወልዳው በአራስነቷ ቁስሏ ሳይጠግ አቅሟ ሳይበረታ ጉልላቷ ሲሰራ አሸዋ እያቀበለች ድንገት ወድቃ እዚያው ሞተች።ጉልላትም ያለ አሳዳጊ በመንደሩ ሰው እርዳታ ሲያድግ ይህንን የእናቱን ታሪክ እየሰማ ነበር...በቃ ከዛ ወዲህ ይኸው እድሜ ልኩን ከማርያም ጋ ጥሉ
እንደከረረ ዛሬ ደረሰ...
ልጆች አላችሁ....?በሉ ኑ አንሱና አልጋ ላይ አድርጉልኝ አሉ አባ ከበራቸው ብቅ ብለው
ሁሉም ተበትኖ ስለነበር እኔና ጓደኛዬ ስንሮጥ ተከትለናቸው ገባን።የጉልላት ደሙ ተጠርጎ ቁስሉ ታክሞ ተሸፍኖ ሞት ከሚመስል እንቅልፉ ነቅቶ
ማሪኝ እመብርሀን ....ማሪኝ እናቴ....አትቀየሚኝ.... ትቼዋለሁ....ማርያም...ማርያም....ይቅር በዪኝ እያለ
ያቃስታል
በል ትንሽ እረፍ ጉልላቴ አሁን ደና ነክ....አየህ እናትህ ስምህን ስትሰይመው በዋዛ አደለም። የቤተክርስትያን ጉልላቷ በሰጎን እንቁላል ይመሰላል።ግዙፏ ሰጎን እንቁላል ከጣለች በኋላ እንቁሏሏን አቅፋ እስኪፈለፈል ድረስ አይኗን ከእንቁላሉ እንደማታነሳው አንተም ብትዝትባት ብትሰድባት አይኗን ካንተ አትነቅልም ዞሮ መግቢያክ ናት።እናትህ ይህችን ጉልላት ስትሰራ ወድቃ ብትሞትም ለህንፃዋ ግን ከገንዘቧ እስከ ደሟ ከፍላለች ማርያም እናትህን ቀምታህ ሳይሆን ወደ እቅፏ ወስዳት ነው።አንተ ምትጠላት ማርያም ለኛ ጉልላታችን ናት ሰገነታችን ናት መድሀኒታችን ናት።ይኸው አንተም ዘመንህን ስትዝትባት ኖረህ ሀኪም
ያቃተው በሽታህን ፈውሳ በእለተ ቀኗ በምህረት ጎበኘችህ
እንዳተ ዛቻና ስድብ ቢሆንማ.....አሁን ተው ጉልላቴ
ተመለስ ...ተው ግድየለም (አባ ቁስሉን በመስቀል
እየደባበሱ በስስት እያዩት ሲያወሩ ጉልለላት ሳል በቀላቀለ ድምፅ
አንቺን ብሎ ማርያም!!....ብሎ ፀጥ ሲል ደንግጠን
እያየነው
"ማን አፈረ' ብሎ ቀጠለ
እውነትም "አንቺን ብሎ ማርያም ማን
አፈረ ማንም!! አሉ አባ በፈገግታ ሁላችንንም
እያዩ።
✍️ ቻቻ