✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

@maheberenesabho


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ;ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሳጽን ይንቃሉ " ምሳሌ 1:7
👉 የቻናሉ አላማ
✔️💠 የአባቶች ምክር
✔️💠መንፈሳዊ መዝሙሮች
✔️💠ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን መረጃ ያገኙበታል

ለማንኛውም ሀሳብ @hayelewa ✣✣

☞ ለመቀላቀል ይሕን @maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

20 Jul, 06:06


እግዚአብሔር ሲቀጣን

"አንድ ሐኪም አእምሯቸውን የሳቱ ሰዎች ቢሰድቡት፥ ስድባቸውን ከቁም ነገር አይቆጥረውም፡፡ እንዲህ አእምሯቸውን እንዲስቱ ያደረጋቸውን ምክንያት ያስወግድላቸው ዘንድ ይተጋል እንጂ፡፡ 'ሰድበውኛል' ብሎ የራሱን ጥቅም አያይም፤ የሕሙማኑን እንጂ፡፡ በጥቂቱም ቢኾን ሻል ካላቸውና ራሳቸውን መግዛት የሚችሉ ከኾነም እጅግ ደስ ይሰኝባቸዋል፡፡ ውስጡ በፍጹም ሐሴት ይሞላል፡፡ መድኃኒት መስጠቱን በፊት ከሚያደርግላቸው ይልቅ ተግቶ ይሰጣቸዋል፡፡ 'ከዚህ በፊት ሰድበውኛልና ልበቀላቸው' ብሎ በፍጹም አያስብም፡፡ ይበልጥ እንዲጠቀሙና ወደ ቀድሞ ጤናቸው ይመለሱ ዘንድ ተግቶ ይሠራል እንጂ፡፡

"እግዚአብሔርም እንደዚህ ነው፡፡ ምንም እንኳን እጅግ ጥልቅ በኾነ ኃጢአት ውስጥ ብንወድቅም፥ ኹሉንም ነገር የሚያደርገው እኛን ከመቅጣት አንጻር አይደለም፤ የሚቀጣን ስለ ሠራነው የኃጢአት ዓይነት አይደለም፡፡ ከዚህ ሕመማችን እንድንፈወስ ብሎ ነው እንጂ፤ በዚሁ መንገድ ሊመለሱ ይችላሉ ብሎ በማሰብ ነው እንጂ፡፡"

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፥ ወደ ቴዎድሮስ፥ ገጽ 36)
https://t.me/maheberenesabho



https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

20 Jul, 05:55


🕊

[  † እንኳን ለአባታችን ቅዱስ ብስንድዮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።  †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †


🕊  † ቅዱስ ብስንድዮስ ጻድቅ †  🕊

† ቅዱስ ብስንድዮስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ድንቅ ሥራ ከሠሩት እንደ አንዱ ሆኖ ይዘከራል:: ቅዱሱ ግብጻዊ ሲሆን በልጅነቱ ወደ ትምሕርት ቤት ገብቶ ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምሯል:: የሚገርመው የብሉይም ሆነ የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን በሙሉ ያጠናቸው በቃሉ ነበር::

በእርግጥ ይሕንን ማድረግ የቻሉ በርካታ የሃገራችን ሊቃውንት ዘንድሮም አሉ:: ልዩነቱ ግን ወዲህ ነው:: ቅዱስ ብስንድዮስ መጻሕፍቱን ያጠናቸው ለሕይወት እንጂ ለእውቀት አልነበረምና ሁሌም ነግቶ እስከ ሚመሽ እያንዳንዱን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እያጣጣመ ይጸልይ ነበር:: ይሕንን ሲያደርግ ደግሞ
ባጭር ታጥቆ ጫማውን አውልቆ: በባዶ ሆዱ ቁሞ ነው::

ታዲያ እያንዳንዱን የመጽሐፍ ክፍል ሲጸልይ ነቢይ ቢሆን ሐዋርያ ወደ እርሱ ይወርድለት ነበር:: ለምሳሌ ዘፍጥረትን ሲጸልይ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ይመጣና ከፊቱ ተቀምጦ ይሰማዋል:: ትንቢተ ኢሳይያስ ላይ ሲደርስ ኢሳይያስ: ወንጌለ ማቴዎስ ላይ ሲደርስ ቅዱስ ማቴዎስ ይመጡና ደስ እያላቸው ያደምጡት ነበር::

አንዱ ነቢይ: ወይ ሐዋርያ ሲወጣ ቅዱስ ብስንድዮስን ባርኮ ሌላኛውን ተክቶ ነው:: በዚህ ምክንያት የቅዱሱ ሕይወት በምድር እያለ ሰማያዊ ሆነ: ሰማንያ አንዱን አሥራው መጻሕፍት የጻፉ ቅዱሳንን ለማየት በቃ: በእጆቻቸውም ተባረከ::

የቅዱስ ብስንድዮስ ቀጣይ የሕይወቱ ተግባር ብሕትውና ሆነ:: ዓለምንና ግሳንግሷን ትቶም ወደ በርሃ መነነ:: በአጽንዖ በዓት: በጾምና በጸሎት: በትሕርምትም ተጋደለ:: በየደረሰበት ቦታ ሁሉ እግዚአብሔር በእጆቹ ድንቅ ተአምር ይሠራ ነበር:: ብዙ ድውያንን ፈወሰ: አጋንንትንም ከአካባቢው አሳደደ::

በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት ግን ስዕለት ስላለበት ሴቶችን ላለማየት ይጠነቀቅ ነበር:: በሆድ ሕመም ትሰቃይ የነበረችና ጥሪቷን በመድኃኒት የጨረሰች አንዲት ሴት ስለ ቅዱሱ ዝና ትሰማለች:: ችግሩ ግን እርሱ ከውዳሴ ከንቱና ከሴት የሚርቅ ነውና እንዴት ብላ ታግኘው? አንድ ቀን ከበዓቱ አካባቢ ተደብቃ ውላ ሲመጣ የልብሶቹን ዘርፍ ለመንካት በእምነት አሰበች::

ልክ ከበዓቱ ሲዘልቅ ስሉጥ [ፈጣን] ነበርና ገና እንዳያት ሩጦ አመለጣት:: እንዳትከተለው ድውይ ናትና አልቻለችም:: አዝና ዝቅ ስትል ግን የረገጠውን ኮቲ ተመለከተች:: በፍጹም ልቧ: በእምነት "የጻድቁ አምላክ ማረኝ" ብላ ከአፈሩ ቆንጥራ በላች:: ደቂቃ አልቆየችም:: ፈጥና ከደዌዋ ዳነች:: እንደ እንቦሳ እየዘለለች ወደ ከተማ ሔዳ ተአምሩን ተናገረች::

ከእነዚህ ዘመናት በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ቅፍጥ [Qift] በምትባል ሃገር ጵጵስናን [እረኝነትን] ተሹሟል:: ወደ ከተማ ሲገባ የቀደመ ተጋድሎውን ቸል አላለም:: ይልቁኑ ይተጋ ነበር እንጂ:: ከብቃት መዓርግ ደርሷልና ሲቀድስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገሃድ ያየው: ሠራዊተ መላእክትም ይከቡት ነበር::

ሕዝቡ ሊቆርቡ ሲመጡ የእያንዳንዱ ኃጢአት በግንባራቸው ተጽፎ ይታየው ነበር:: የበቁትን እያቀበለ: ያልበቁትን እየመከረና ንስሐ እየሰጠ ይመልሳቸዋል:: እንዲሕ በጽድቅ: በሐዋርያዊ አገልግሎትና በንጽሕና ተመላልሶ ቅዱስ ብስንድዮስ በዚህች ቀን ዐርፏል::

ቅዱስ ብስንድዮስ ካረፈ በኋላ ደቀ መዝሙሩ ከመግነዙ ጥቂት ቆርጦ አስቀርቶ ብዙ ድውያንን ፈውሶበታል::

† ቸር አምላክ ለአባቶቻችን የሰጠውን ጸጋ ለእኛ ለባሮቹም አይንሳን:: ከቅዱሱ በረከትም ያድለን::

🕊

[  † ሐምሌ ፲፫ [ 13 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅዱስ ብስንድዮስ ሊቅ ወጻድቅ
፪. ቅዱስ አሞን ሰማዕት [ዘሃገረ ጡህ]

[   † ወርኀዊ በዓላት    ]

፩. እግዚአብሔር አብ
፪. ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት
፫. ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት
፬. ቅዱስ አስከናፍር
፭. አሥራ ሦስቱ ግኁሳን አባቶች
፮. ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
፯. አቡነ ዘርዐ ቡሩክ


" አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር:: ከማን እንደተማርኸው ታውቃለህና:: ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳት መጻሕፍትን አውቀሃል:: የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጐ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምሕርትና ለተግሣጽ: ልብንም ለማቅናት: በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል:: " † [፪ጢሞ. ፫፥፲፬]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬


https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

16 Jul, 06:43


#ክፋትን_ከአንተ_አርቃት

"ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ ውስጥ ያለ መሆን አለመሆኑን ያውቃል፡፡ ይኸውም ስትቆጣ ወይም ስትጮህ ወይም የማይረቡ ከንቱ ነገሮችን ስትናገር ሲያይህ ጠላት በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል ያን ጊዜ በውስጥህም በውጭህም ያለውን ሳይቀር ይገዛል ፤ መዝጊያ እንደሌለው ቤት እንደ ክፉ ሌባ ይገባና ውስጥህን ይበረብረዋል፡፡"

#ቅዱስ_ባስልዮስ


https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

16 Jul, 05:35


🕊

✞  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

[  ✞ እንኩዋን ለጻድቅ  አባ ኅልያን ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]


🕊  ✞  አባ ኅልያን ገዳማዊ  ✞  🕊

ጻድቁ ተወልዶ ያደገው ዐይነ ፀሐይ በምትባል የቀድሞ የግብፅ ክፍለ ሃገር ሲሆን ወላጆቹ ዲስጣና ካልሞና ይባላሉ:: እነርሱ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩና ገና በልጅነት ይህንኑ አጥብቀው አስተምረውታል:: ቅዱሱ ኅልያን ጾምን: ጸሎትን ብቻ ያይደለ በሥጋዊ ሙያውም የተመሰገነ አንጥረኛ ነበር::

በወዙ በላቡ ሠርቶ ያገኘው ሃብት ነበረው:: በተለይ ወርቅና ብር እየሠራ ይተዳደር: ከገቢውም ነዳያንን ያስብ ነበር:: እንዲህ ባለ ግብር ሳለ አንድ ቀን ፈተና መጣበት:: አንዲት ዐረባዊት ሴት መጥታ የጀሮ ጌጥ [ጉትቻ] እንዲሠራላት ትጠይቀውና እርሱም ከወርቅ ይሠራላታል:: የጀሮ ጌጡን ከሰጣት በሁዋላ ግን "ዋጋውን አልሠጥህም" ትለዋለች::

እርሱም "ምነው እህቴ! የደከምኩበትን ለምን አትከፍይኝም?" ሲላት ገላዋን አጋልጣ "ሴትነቴን ልስጥህ" ብላ ለዝሙት ጠየቀችው:: ድንግሉ ኅልያን ከአነጋገሯና ከድርጊቷ የተነሳ በጣም ደነገጠ:: ከፊቷ ላይ አማትቦ: ገስጿት ወደ ቤቱ ሔደ:: ሙሉ ሌሊት ሲያዝን አደረ:: ሊነጋጋ ሲል በልቡ ወሰነ:: ይሕችን ዓለም ሊተዋትም ቆረጠ::

በወጣት ጉልበቱ ደክሞ ያፈራው ሃብቱ: ንብረቱ: ቤቱ: መሬቱ: ወርቁ: ብሩ አላሳሳውም:: ነዳያንን ሁሉ ወደ ቤቱ ጠርቶ ሙሉ ንብረቱን አካፈላቸው:: የተረፈችው የለበሳት ልብስ ብቻ ነበረችና ፈጽሞ ደስ እያለው ከተማውን ጥሎ ወደ በርሃ ተሰደደ:: ልቡናን የሚመረምር ጌታ ሊመራው ወዷልና ፫ [3] ቅዱሳን ስውራንን ሰደደለት::

ሦስቱም የብርሃን አክሊል ደፍተው: የብርሃን ካባ ላንቃ ለብሰው: የብርሃን ዘንግ ይዘው ተገለጡለት:: እየመሩም ወስደው በግራና በቀኝ ውሃ ከሚፈስባት: ደኗ ለዐይን ደስ ከምታሰኝ ዱር አደረሱት:: አካባቢው እንኩዋን ሰው እንስሳትም አልነበሩበትም:: ፫ [3] ቱ ቅዱሳን ከቦታዋ እንደ ገቡ በላዩዋ ላይ ዕንቁ ያለባት የብርሃን ዘንግ ሰጥተውት "ወደ ፈጣሪ እንስገድ" አሉት::

ሰግዶ ቀና ሲል ግን ፫ [3] ቱም በአካባቢው አልነበሩም:: ተሠውረዋልና:: አባ_ኅልያን ከቅዱሳኑ በመለየቱ ፈጽሞ አለቀሰ::

ተጋድሎውን ግን በጾምና በጸሎት: በስግደትም አጠነከረ:: ቅዱሱ የሚመገበው: የሚለብሰውም ቅጠል ነበር:: በእርሱ ዘንድ ሌሊት የሚባል አልነበረም:: ምክንያቱም ያቺ ዘንግ ሲመሽ ግሩም የሆነ ብርሃን ታወጣ ነበርና ነው::

መንገድ መሔድ በፈለገ ጊዜም ትመራው: ጐዳናውንም ታሳጥርለት ነበር:: እንዲህ ባለ ግብር ለበርካታ ዓመታት ከሰው ተለይቶ ኖረ:: አጋንንት በተለያየ መንገድ ፈተኑት:: ግን አልቻሉትም:: አቅም ሲያጥራቸው ወደ ከተማ ሔደው: በሰው አርአያ ሽፍቶችን አናግረው ሊያስገድሉት ሞከሩ:: ነገር ግን ከፊት ለፊት እያዩት ሽፍቶቹ ሲራመዱ ቢውሉም ሊደርሱበት አልቻሉም::

እግዚአብሔር በኪነ ጥበቡ መንገዱን ያረዝምባቸው ነበር:: በሁዋላ ግን ሽፍቶቹ በድካምና በውሃ ጥም ሊያልቁ ሆነ:: ጻድቁ ምንም እርሱን ለመግደል ቢመጡም አዘነላቸው:: ባሕሩን ያለ ታንኩዋ እየረገጠ ደረሰላቸው:: ከዱር ፍሬ አብልቶ: ንጹሕ ውሃም አጠጥቶ ሸኛቸው::

እድሜው እየገፋ ሲሔድ አንድ ቀን እነዛ በፊት የተሠወሩ ፫ [3] ቅዱሳን እንደ ገና ተገለጡለት:: በደስታ ሲጨዋወቱ አድረው ሲነጋ አባ ኅልያን ወደ ምሥራቅ ሰግዶ ዐረፈ:: ፫ [3] ቱ ቅዱሳንም ሥጋውን ገንዘው በበዓቱ ቀበሩት:: ዜና ሕይወቱንም ጽፈው አስቀመጡትና እንደ ገና ተሠወሩ::

የቅዱሳን አምላክ ለእኛም የአባቶችን ረድኤት ይላክልን:: ከጻድቁም በረከትን ይክፈለን::

🕊

[  †  ሐምሌ ፱ [ 9 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  †   ]

፩. አባ ኅልያን ገዳማዊ
፪. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሰማዕት [ዘሐምስቱ አሕጉር]
፫. ቅዱስ ታውድሮስ ሰማዕት
፬. ሰማዕታት ሉክዮስና ድግናንዮስ [በንስሃ ለክብር የበቁ የጦር አለቆች]

[   †  ወርሐዊ በዓላት  †   ]

፩. አባ በርሱማ ሶርያዊ [ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት]
፪. አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ [ኢትዮዽያዊ]
፫. ፫፻፲፰ ["318] ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት [ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ]
፬. የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
፭. አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ [ኢትዮዽያዊ]
፮. ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ [ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት]

" ጌታ ኢየሱስም "አትግደል: አታመንዝር: አትስረቅ: በሐሰት አትመስክር: አባትህንና እናትህን አክብር: ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ" አለው:: ጐበዙም "ይህንማ ሁሉ ከሕጻንነቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ:: ደግሞስ የሚጐድለኝ ምንድር ነው?" አለው:: ጌታ ኢየሱስም "ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሒድና ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ:: መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ:: መጥተህም ተከተለኝ" አለው::" [ማቴ.፲፱፥፲፰] (19:18)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

15 Jul, 16:36


                         †                        

  [      🕊  ፍኖተ ቅዱሳን   🕊      ]

[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  ተርእዮን [ መታየትን ] አለመውደድና ለታይታ ብሎ ምንም ነገር አለማድረግ !  ]

🕊

ራሱን የሚያዋርድ ከፍ ይላል .... !  "
........

አባ ዮሐንስ ሐፂር እንዲህ አለ ፦ "ብቻውን የሚኖር አንድ መንፈሳዊ ሽማግሌ ነበር፡፡ በከተማው ሕዝብ ዘንድ በከፍተኛ ደረጃ ይከበር ነበር፡፡

ሌላ አረጋዊ ሊያርፍ ሲል ከዚህ ዓለም ከመውጣቱ በፊት ወደ እርሱ እንዲመጣና ዓይን ለዓይን ተያይተው ይሰናበተው ዘንድ ወደዚህ ሽማግሌ ላከበት፡፡ በዚህ ጊዜ እንዲህ ሲል አሰበ ፦ "በቀን ብሄድ ሰዎች ከእኔ በኋላ ይመጡና ብዙ ክብር እናክብርህ ይሉኛል፣ ይህ ደግሞ ሰላም አይሰጠኝም። ስለዚህ ማንም ሰው እንዳያየኝ ሌሊት በጨለማው እሄዳለሁ፡፡"

ሌሊት ተነሥቶ በጨለማ ሊሄድ ሲልም ሁለት መላእክት ያበሩለት ዘንድ መብራቶችን ይዘው ከእግዚኣብሔር ዘንድ ተላኩ። መላእክት እያበሩለት ሲሄድ የከተማው ሰው በሙሉ ወጣና የዚህን አረጋዊ ክብር ተመለከተ፡፡

ከክብር ለመሸሽ አብዝቶ ባሰበ መጠን የበለጠ ከበረ "ራሱን የሚያዋርድ ከፍ ይላል" እንደ ተባለ። [ሉቃ.፲፬፥፲፩]

የአባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖



https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

14 Jul, 21:06


🕊

[  †  እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃን ወከዋክብተ ገዳም አቡነ ኪሮስ: አባ ብሶይ እና አባ ሚሳኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።  †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †


🕊  †   አቡነ ኪሮስ ጻድቅ   †   🕊

† የጻድቁን ስም የሚጠራ አፍ ንዑድ ነው: ክቡር ነው:: በእውነት የቅዱሱን አባት ክብር ለማግኘት መፋጠን ይበጃል::

አቡነ_ኪሮስ የተወለዱት በ፬ [4] ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ወላጆቻቸው ነገሥታት ናቸው:: ተወልደው ባደጉባት ሃገር ቁስጥንጥንያ ገና በልጅነት ምቾት ሳያሳሳቸው መጻሕፍትንና ትሕርምትን ተምረዋል:: ወንድማቸው [ታላቁ ቴዎዶስዮስ] በነገሠባቸው የመጀመሪያ ዓመታት በቤተ መንግስቱ ዙሪያ ግፍ በዝቶ ነበርና አቡነ ኪሮስ ከኃጢአት ለመራቅና ለጌታ ለመገዛት ከከተማው ጠፍተው: አሕጉር አቋርጠው ወደ ግብፅ [ገዳመ አስቄጥስ] መጡ::

እርሳቸውን ለመፈለግ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም:: ይባስ ብሎ የንጉሡ ልጅ ገብረ ክርስቶስ ሙሽርነቱን ጥሎ ወደ ሌላ ሃገር መነነ:: "የቅኖች ትውልድ ይባረካል" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት:: አቡነ ኪሮስ ለሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎቱ ናቸው:: አቡነ ኪሮስ በገዳም ውስጥ የታላቁ አቡነ በብኑዳ ደቀ መዝሙር ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል::

ቅዱስ በብኑዳን አንበሳ በበላው ጊዜ በጣም አዝነው "ለምን ጌታ ሆይ?" በሚል መሬት ላይ ወድቀው አለቀሱ:: "ምክንያቱ ካልተነገረኝ አልነሳም" ብለው ከወደቁበት መሬት ላይ ሳይነሱ ለ40 ዓመታት አልቅሰዋል:: በዚህ ምክንያት ግማሹ አካላቸው አፈር ሆኖ ሣር በቅሎበታል:: ጌታችን ተገልጦ ምክንያቱን ነግሯቸዋል:: አካላቸውንም እንደነበረ መልሶላቸዋል::

አንድ ቀን ጻድቁ ለቅዱስ በብኑዳ ሞት ምክንያት የሆነው መነኮስ ታንቆ መሞቱን ሰምተው በጣም አዘኑ:: ሱባዔ ገብተው: ፍጹም አልቅሰው: ከጌታም አማልደው: የዛን ኃጥእ ነፍስ ከሲዖል አውጥተዋል:: በሌላ ጊዜ ደግሞ ኃጥአን የሞሉበት አንድ ገዳም በግብጽ ነበርና መቅሰፍት ወርዶ ሁሉንም ባንድ ቀን ሲያጠፋቸው አዩ::

ጻድቁ በዚህም ምክንያት ለ፴ [30] ዓመታት አልቅሰው: ሙታኑን አስነስተው: ንስሃ ሰጥተው: ገዳሙን የጻድቃን: ሕይወታቸውንም የፍቅር አድርገውታል:: ጻድቁ እመቤታችንን ከመውደዳቸው የተነሳ በስዕሏ ፊት አብዝተው ይሰግዱና ያለቅሱ ነበር:: እመ አምላክም ተገልጣ ትባርካቸው ነበር::

ከዚህ በሁዋላ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሒደው ለ፶፯ [57] ዓመታት ማንንም ሳያዩ ተጋደሉ:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ [ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና] በየቀኑ ይጐበኛቸው: ቁጭ ብሎም ያወራቸው ነበር:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ጌታ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: ድንግል እመቤታችንና ቅዱስ ዳዊትን አስከትሎ ወረደ::

ቅዱስ ዳዊት ቀርቦ እያጫወታቸው: በበገናው እየደረደረላቸው: ከዝማሬው ጣዕም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ጌታችንም ታቅፎ: ስሞ ይዟቸው አረገ:: ሥጋቸውን #አባ_ባውማ ቀበሩት:: የአቡነ ኪሮስ ቁመታቸው ቀጥ ያለ: ጽሕማቸውም የተንዠረገገ ነበር:: እድሜአቸውን ግን መገመት የሚቻል አይመስለኝም::

🕊  † የበርሃው ኮከብ አባ ብሶይ  †  🕊

† ታላቁ አባ ብሶይ [ቢሾይ] :-

¤ በ፬ [4] ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ
¤ በመላእክት መሪነት የመነኑ
¤ የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ባልንጀራ
¤ የአባ ባይሞይ ደቀ መዝሙር የነበሩ
¤ በአጭር ጊዜ የብዙዎች አባት የሆኑ ሰው ናቸው::

† እንቅልፍን የማያውቁ

¤ በ፵ [40] ቀን ብቻ እህል የሚቀምሱ
¤ የጌታችንን እግር በየቀኑ እያጠቡ የሚመገቡ
¤ ፈጣሪያቸውን በጀርባቸው ያዘሉ [ነዳይ መስሎ አግኝተውት]
¤ በስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተጉ
¤ በርካታ ጻድቃንን የወለዱ ታላቅ የፍቅር ሰው ናቸው::

በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሰርተው: ቤተ ክርሰቲያንን በንጽሕናቸው አስደስተው: ሐምሌ ፰ [8] ቀን ዐርፈዋል:: ግብፅ ውስጥ የሚገኘው ገዳማቸው ዛሬም ቤተ አበው: ተአምራት የማይለዩትና ተወዳጅ ነው:: ቦታው መካነ ሱባዔ ወመንክራት ነውና::

🕊  †  አባ ሚሳኤል ነዳይ  †  🕊

† መቼም ያ ዘመን [፬ [4] ኛውና ፭ [5] ኛው ክ/ዘመን] እጅግ የተባረከ ነው:: ቅዱሳኑ በብዛት የባለጸጐችና የነገሥታት ልጆች ናቸው:: አባ ሚሳኤልም የኬልቄዶን ንጉሥ ልጅ ሳሉ መንነው በበርሃ ለ፷፭ [65] ዓመታት ተጋድለዋል:: በመጨረሻ ግን በደዌ ምክንያት ወደቁ:: ለ፭ [5] ዓመታት መነኮሳቱ ሲጠይቁዋቸው ቆይተው ሰለቹ::

ከዛም ለ፲፭ [15] ዓመታት ላበታቸው በግንባራቸው እየተቀዳ: ያለ ምንም ምግብ እያቃሰቱ በበዓታቸው ወድቀው ኑረዋል:: ቸሩ አምላክ ግን ፬ [4] ቱን ሊቃነ መላእክት [ሚካኤል: ገብርኤል: ሩፋኤልና ሳቁኤልን] አዞላቸው ሲጠብቁዋቸው ኑረዋል::

በዚህች ቀንም አቡነ_ኪሮስ መጥተው አጽናንተው: ጌታችንንም ጠርተው እንዲያርፉ አድርገዋል:: መላእክት እያጠኑና እየዘመሩ ጻድቁ ቀብረዋቸዋል:: በመቃብራቸውም ላይ ፈውስ የሆነ ጸበል ፈልቁዋል::

†   እግዚአብሔር የእኛን ያይደለ የጻድቃኑን ቅድስና አስቦ ይራራልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

🕊

[   † ሐምሌ ፰ [ 8 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. አቡነ ኪሮስ ጻድቅ [አረጋዊና ገዳማዊ]
፪. አባ ብሶይ ጻድቅ [ኮከበ ገዳም]
፫. አባ ሚሳኤል ነዳይ [ጻድቅ]
፬. አባ ቢማ ሰማዕት
፭. አባ በላኒ ሰማዕት
፮. ቅዱሳን አቤሮንና አቶም [ሰማዕታት]

[   †  ወርሐዊ በዓላት    ]

፩. ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
፪. ኪሩቤል [አርባዕቱ እንስሳ]
፫. አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
፬. ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ [ከ፲፪ [12] ቱ ሐዋርያት]

† " በረከት በጻድቅ ራስ ላይ ነው:: የኃጥአንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል:: የጻድቅ መታሠቢያ ለበረከት ነው:: " † [ምሳ.፲፥፯] (10:7)

† " እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና:: ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና:: ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል. . . ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: " † [መዝ.፴፮፥፳፰-፴፩] (36:28-31)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[
💖                   🕊                    💖

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

13 Jul, 10:44


#ወደ_ገዳማት_መሄድ_ላሰባችሁ_መልዕክት

ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና ምእመናን ሀገራዊ
✤ ሰላምን
✤ መረጋጋትን
✤ ፍቅርን
✤ አንድነትን ለማስፈን ጾም እና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
"የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ

https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

10 Jul, 01:44


✞ #የሐምሌ_ወር_የንግስ_በዓላት ✞

ረቡዕ ሐምሌ 3 - አባ ሊባኖስ - ልደታቸው - በጣፎ ሃያት ገብርኤል - በእንጦጦ ኪዳነምህረት

አርብ ሐምሌ 5 - የቅዱስ ጳውሎስ እና ጴጥሮስ - እረፍታቸው - በዌንጌት እና በሰዋሰው ቅዱስ ጳውሎስ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ

እሁድ ሐምሌ 7 - ቅድስት ሥላሴ - በአብርሃም ቤት የገቡበት

ሰኞ ሐምሌ 8 - አባ ኪሮስ - ዕረፍታቸው

ማክሰኞ ሐምሌ 9 - አቡነ እስትንፋስ ክርስቶስ -  - በቀበና መድኃኔዓለም

ረቡዕ ሐምሌ 10 - ሐዋርያው ናትናኤል - በቡራዩ ፀደንያ ማርያም

አርብ ሐምሌ 19 - ቅዱስ ገብርኤል

እሁድ ሐምሌ 21 - እመቤታችን በአባዶ

                        - ቅዱስ ዑራኤል በዓል - በካሳንችስ ዑራኤል

ሰኞ ሐምሌ 22 - ቅዱስ ዑራኤል

ማክሰኞ ሐምሌ 23 - ቅዱስ ጊዮርጊስ - ቅዳሴ ቤቱ(በገነተ ፅጌ ፒያሳ)

ሐሙስ ሐምሌ 25 - ቅዱስ መርቆሬዎስ - በደብረ አባይ አርሴማ - በጎፋ መብራት ሀይል
                          - ቃሊቲ ቁስቋም ማርያም - ቅዳሴ ቤቷ

አርብ ሐምሌ 26 - ቅዱስ ዮሴፍ - እረፍቱ

ቅዳሜ ሐምሌ 27 - ቸሩ መድኃኔዓለም - ቅዳሴ ቤቱ - በቦሌ በአራብሳi

ሰኞ ሐምሌ 29 - አቡነ እጨጌ ዮሐንስ - ዕረፍታቸው - በወይራ ሰፈር
https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

08 Jun, 05:47


✞ #የሰኔ_ወር_የንግስ_በዓላት ✞

ቅዳሜ ሰኔ 1 - ቅድስት ልደታ - ቅዳሴ ቤት - ፊጋ ከሲኤምሲ(አልታድ) ሚካኤል ፊት ለፊት ከጋስት ሞል ዝቅ ብሎ ከነዳጅ ማደያው አጠገብ ባለው ኮብል እስቶን ገባ ብሎ

ሰኞ ሰኔ 3 - አቡነ ዜና ማርቆስ - በድሬ ዳሌ ጣፎን አልፎ በአዲሱ መንገድ ድሬ ብሎ ትራንስፖርት መያዝ ከእዛ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ብሎ መጠየቅ

ሐሙስ ሰኔ 6 - የጌታችን በዐለ እርገት - በአርባ አንድ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን

ረቡዕ ሰኔ - 12  ቅዱስ ሚካኤል

እሁድ ሰኞ 16 - በዓለ ጵራቅሊጦስ - በጎላ ቅዱስ ሚካኤል - በቅዱስ ማርቆስ (6 ኪሎ) - በቦሌ አራብሳ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን 

ሰኞ ሰኔ 17 - አቡነ ገሪማ - በኮተቤ ካራ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን

ሐሙስ ሰኔ 20 - ነብዩ ኤልሳዕ - በእንጦጦ ራጉኤል ወ ኤልያስ ቤተክርስቲያን

አርብ ሰኔ 21 - እመቤታችን

ረቡዕ ሰኔ 26 - ቅዱስ ገብርኤል - በዓለም ባንክ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን

ሐሙስ ሰኔ 27 - መድኃኔዓለም - ሃያት ጨፌ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍል ጸበል  ከኃያት አደባባይ ወደ 49 ሲሄዱ መቄዶንያ ፊት ለፊት
እና ጨሪ መድኃኔዓለም - ሰፈራ ወረድ ብሎ

እሁድ ሰኔ 30 - መጥምቁ ዮሐንስ - በቦሌ መድኃኔዓለም በቤላ ዮሐንስ (መጥምቁ ባለበት ሁሉ)

✞ መምጣት የማትችሉ #Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ ✞

         ✥

https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

28 May, 21:11


#ግንቦት_21

#ደብረ_ምጥማቅ

ግንቦት ሃያ አንድ በዚች ዕለት አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ።

እርሷም በልጅዋ የመለኮት ብርሃን የተጐናጸፈች ናት በዙሪያዋም የመላእክት ሠራዊት የመላእክት አለቆችም በየማዕረጋቸው ክንፋቸውን ዘርግተው ይቆሙ ነበር ይጋርዷታልም። ሱራፌልም ማዕጠንታቸውን ይዘው ለንግሥዋ ገናናነት ይሰግዳሉ በየስግደታቸውም እንዲህ እያሉ ያመሰግኗታል። አብ በሰማይ ሁኖ ተመለከተ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም አንድ ልጁንም ልኮ ከአንቺ ሰው ሆነ።

ሁለተኛ ሰማዕታትም በየማዕርጋቸው ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው እየመጡ መጀመሪያ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአምባላይ ፈረሱ ወርዶ ይሰግድላታል እንዲሁም ባልንጀሮቹ ሰማዕታት መጥተው ይሰግዱላታል ።

ከእርሱ በኋላ የሚመጣው በዱሪ ፈረስ የሚቀመጥ ይህ መርቆሬዎስ ነው። ከዚህም በኋላ ሰማዕታት ሁሉ በመከታተል መጥተው ይሰግዱላታል ምስጋናም ያቀርቡላታል። ሁለተኛም ደግሞ የጻድቃን አንድነታቸው መጥተው በፊቷ ሰግደው ይመላለሳሉ።

ሄሮድስ የገደላቸው ሕፃናትም መጥተው ይሰግዱላታል በፊቷም እየዘለሉ አንዱ በአንዱ ላይ እየዘለለ በመተቃቀፍም ይጫወታሉ የተሰበሰቡትም በአዩ ጊዜ ደስታ ይመላባቸዋል በሰማይም ያሉ ይመስላቸው ነበር።

እናትና አባቱም የሞቱበት ቢኖር ወይም ከዘመዶቹ ወይም ባልንጀራዉ ቅድስት ድንግል እመቤቴ ሆይ ዕገሌን አሳዪኝ ብሎ በሚለምናት ጊዜ ቀድሞ በነበረበት መልኩ ያን ጊዜ ታመጣዋለች። ደግሞ መሀረባቸውን ወደላይ ይወረውሩላታል የወደደችውንም በእጇ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች ለበረከትም በየጥቂቱ ይካፈሉታል።

እንዲህም አምስት ቀን ሁሉ ክርስቲያንም እስላሞችም አረማውያንም ያይዋታል። ወደ ቤታቸውም ለመሔድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል እርሷም ትባርካቸውና ይመለሳሉ።


ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን ለአባት እናቶቻችን የተገለጠች እመቤታችን ለእኛም በረድኤት ትገለጽልን:: ጣዕመ ስሟ በአንደበታችን: ጣዕመ ፍቅሯ በልባችን ይደርብን አሜን::

(#ስንክሳር_ዘተዋሕዶ)

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

28 May, 05:41


✞ በድንግል አመረ ህይወቴ ✞

በድንግል አመረ ህይወቴ
በማርያም አማረ ህይወቴ
ስጠራት ገብታልኝ ከቤቴ

በድንግል አማረ ከሞት መሀል ነጥቀሽ
በድንግል አማረ ነፍስን ዘራሺብኝ
በድንግል አማረ ሀጢያተኛ ሳለሁ
በድንግል አማረ ሰው አድርገሽ አቆምሺኝ
በድንግል አማረ ሀዘን መከራዬ
በድንግል አማረ ታሪክ ሆኖ ቀረ
በድንግል አማረ ህይወቴም በአንቺ
በድንግል አማረ በድንግል አማረ
በማርያም አማረ

        /አዝ = = = = =

በድንግል አማረ ሀጢያትን አብዝቼ
በድንግል አማረ ለምፅ ቢያጠቃኝም
በድንግል አማረ አንቺ እያነፃሽኝ
በድንግል አማረ ዳግም ብጨቀይም
በድንግል አማረ እሩሩ ነሽና
በድንግል አማረ ምልጃሽ አይዘገይም
በድንግል አማረ ስምሽን ስጠራ
በድንግል አማረ አታሳፍሪኝም(×፪)

        /አዝ = = = = =

በድንግል አማረ ሀዘኔ በርትቶ
በድንግል አማረ እንባዬ ሲቀድመኝ
በድንግል አማረ ወዳጅ ያልኩት ሁሉ
በድንግል አማረ ሁሉ ፊቱን ሲያዞርብኝ
በድንግል አማረ አንቺ ደርሰሺልኝ
በድንግል አማረ ስሜ ተቀየረ
በድንግል አማረ ኑሮዬ በሙሉ
በድንግል አማረ በድንግል አማረ
በማርያም አማረ

        /አዝ = = = = =

በድንግል አማረ ሀዘኔ በርትቶ
በድንግል አማረ እንባዬ ሲቀድመኝ
በድንግል አማረ ወዳጅ ያልኩት ሁሉ
በድንግል አማረ ፊቱን ሲያዞርብኝ
በድንግል አማረ አንቺ ደርሰሺልኝ
በድንግል አማረ ስሜ ተቀየረ
በድንግል አማረ ኑሮዬ በሙሉ
በድንግል አማረ በቃጥላ አማረ
በግሸን አማረ

👉 ዘማሪ ያብስራ ሲሳይ                                                                                                                                                                
https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho

https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

18 May, 10:15


❤️ሲያምሩ❤️

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

26 Nov, 18:25


Channel photo updated

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

25 Oct, 17:54


✝️ጥቅምት✝️

የተዋህዶ ልጆች በያላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛ

እሁድ ጥቅምት 4 - አብርሃ ወአፅብሃ - በመሪ ሃያት ፋኑኤል  - በየካ ተራራ ዋሻ ሚካኤል እና ጋራው ተክለሃይማኖት - በዘነበ ወርቅ አቡነ አረጋዊ

ሰኞ ጥቅምት 5 - አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ

ረበዕ ጥቅምት 7 - ቅድስት ሥላሴ - በቦሌ አራብሳ ዋሻ ሥላሴ

ማክሰኞ ጥቅምት 13 - አቡነ ዘርዓ ብሩክ - በአስኮ ቃሉ ተራራ አቡነ ሃብተማርያም

ረቡዕ ጥቅምት 14 - አቡነ አረጋዊ

ቅዳሜ ጥቅምት 17 - ቅዱስ እስጢፋኖስ

ሰኞ ጥቅምት 19 - አቡነ ሐራድንግል - በሃያት ጣፎ  ዋሻ ሚካኤል

ማክሰኞ ጥቅምት 20 - ነብዩ ኤልሳዕ - በእንጦጦ ራጉኤል እና ኤልያስ ቤተክርስቲያን

ሀሙስ ጥቅምት 22 - ቅዱስ ዑራኤል - ኮተቤ

ማክሰኞ ጥቅምት 27 - ቸሩ መድኃኔዓለም

ረቡዕ ጥቅምት 28 - ቅዱስ አማኑኤል

አርብ ጥቅምት 30 - ቅዱስ ማርቆስ - 6 ኪሎ

ሁላችሁም በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ 🙏

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

13 Oct, 05:35


አንድ ፕሮፌሰርና አሳ አጥማጅ በአሳ አጥማጁ ጀልባ ላይ ሆነው ባህር እየሄዱ ነው።
ፕሮፌሰሩ አሳ አጥመጁን በንቀት እያየው እንዲህ ሲል ጠየቀው
<ስለባህር አሳዎች ብዛት... ወይም ስለአጠቃላይ እንስሳት ዓይነት ታውቂለህ?> ዓሳ አጥማጁም
<አላውቅም> አለ። በሁኔታው እንደማፈር እያለ
<አይ አንተ... አሁን አንተ ታዲያ ምኑን ኖርከው... ለማንኛውም የህይወትን ሩብ አጥተሃል።> አሳ አጥማጁ ዝምታን መረጠ። ፕሮፌሰሩ ቀጠሉ
<አይ እኔ የተማርኩት ትምህርት ለዚች ዓለም ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል... እነዚህ አሳዎች እንዴት የፍቅር ወዳጆቻቸውን እንደሚያገኙ ታውቃለህ>
<አላውቅም።>
<አሁን ሩበን የህይወት ክፍልን አጥተሃል... በአጠቃላይ በግማሽ ነው እየኖርክ ያለከው>
አሳ አጥማጁ በድንጋጤ ሲያያቸው።
<ግን ለማወቅ ያህል ስለእንሳስት ሳይንስ ምን ያህል ታውቃለህ?>
<አላውቅም...!>
<አንተ በቃ እየኖርክ አይደለም... በሩብ የህይወት ክፍል ነው የምትኖረው! > አሳ አጥማጁ በዝምታ ግራ ተጋብቶ ጀልባውን እየሰገረ ሲሄድ ከፊቱ ማዕበል እየመጣ እንደሆነ አየ። ማዕበሉ በጣም ኃይለኛ እንደሆነ ያስታውቃል። ጀልባዋ መናጥ ጀመረች። ፕሮፌሰሪም አሳ አስጋሪው ጭንቅ ውስጥ ሆኑ... አሳ አስጋሪው ለፕሮፌሰሩ
<መዋኘት ይችላሉ?!>
<ኧረ አልችልም> በፍርሃት ውስጥ እየተንቀጠቀጡ። ጀልባው በማዕበሉ የተነሳ እየተሰነጠቀ ነበር። አሳ አስጋሪው እያዘነ
<አሁን እርሶ 100በመቶ ህይወቶን አጥተዋል።> ብሎ ዘሎ ውሃ ስር ሲገባ። ጀልባው ፕሮፌሰሩን እንደያዘች ተገለበጠች።

ሁሉም ሰው ባለው ሙያ እና ችሎታ የሚያስፈልግበት ቦታ አለ። አንተ ወይም አንቺ ያላችሁ ሙያ የሚገባበት ቦታ አለ። የሰዎች ሙያ እና ህይወት ልናከብር ይገባል።
መልካም ቀን
https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

09 Oct, 18:39


Channel photo updated

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

09 Oct, 18:10


Channel photo removed

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

07 Oct, 06:31


አክሊለ ፅጌ

አክሊለ ፅጌ ማርያም አክሊለ ፅጌ
አክሊለ ፅጌ ማርያም አክሊለ ፅጌ

ስሟ ማርያም ነው አክሊለ ፅጌ
የጌታ እናት "
እናት አባቷ "
ያወጡላት "
ከምድር ማር "
ከሰማይ ያም "
ብለው ሰየሟት "
ድንግል ማርያምን "
አዝ......
የስሟ ጣህም አክሊለ ፅጌ
ከማር ይበልጣል "
እንደሷ ያለ "
ከየት ይገኛል "
የፍቅር መዝገብ "
ነቅህ የሌለባት "
ለክብሯ ወደር "
ማን አግኝቶላት "
አዝ......
የከበረ ዘውድ አክሊለ ፅጌ
የወርቅ ሙዳይ "
የሽቱ ብልቃጥ "
የነፍሴ ሲሳይ "
ከጥፋት ውሀ "
ኖህ የዳነብሽ "
የሰላም መርከብ "
ቤቱ አንቺ ነሽ "
አዝ......
በቤተ መቅደስ አክሊለ ፅጌ
ስትኖር ተመርጣ "
ምግቧን ይዞላት "
ፋኑኤል መጣ "
አስራ አምስት ዓመት "
ሲሆናት ድንግል "
በገብርኤል ብስራት "
ተፀነሰ ቃል "

https://t.me/maheberenesabho



https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

07 Oct, 06:29


#🌹ፆመ_ፅጌ / #የፅጌ_ፆም??
#የእመቤታችን_ስደት_በጾም_በጸሎት_የምታስቡ_ወይም #የምታሳልፉ_የእመቤታችን_የድንግል_ማርያም_የቃልኪዳን_ልጆች #ከወዲሁ_እንኳን_አደረሳችሁ🙏

🌹ለጽጌ ጾም ካላቸው ፍቅር የተነሳ አንዳንድ ምዕመናን ጽጌ ጾም መቼ ነው የሚገባው እያሉ የሚጠይቁ ስላሉ ከወዲሁ ለማስታወስ ጾመ ጽጌ ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ያለው አንድ ወር ከዐሥር ቀን ወይም 40 ቀን ወርኃ ጽጌ፣ ዘመነ ጸጌ፣ ተብሎ ይጠራል፡፡

በነዚህም ቀናት በየቤተክርስቲያኑ የሚነበቡ ምንባቦች፣ የሚዘመሩት መዝሙሮች፣ የሚሰበከው ስብከት፣ የሚቆመው ማኅሌት በጠቅላላው የሚነገረው ስብሐት እግዚአብሔር ሁሉ ሰማይ በከዋክብት ምድር በጽጌያት አሸብርቀው የሚታዩ መሆናቸውን የሚገልጽ ነው፡፡

ወርኃ ጽጌ ለሚከናወነው መንፈሰዊ አገልግሎት መነሻው "መልአኩ ሕፃኑንና እናቱን ወደ ግብፅ ይዘሃቸው ሽሽ፣ የሕፃኑን ነፍስ ሊገድሉት ይፈልጋሉና" ሲል ለዮሴፍ በሕልሙ በነገረው መሠረተ ዮሴፍም ሕፃኑንና እናቱን ድንግል ማርያምን ይዞ ወደ ግብፅ መሰደዱና እመቤታችንና ሕፃኑ ሦስት ዓመት ከመንፈቅ በስደት ከኖሩ በኋላ /ራእይ.12፣6/ ወደ አገራቸው ወደ ናዝሬት የመመለሳቸው መታሰቢያ ነው፡፡ /ማቴ 2፣13-23፣ ት.ኢሳ.19፣1፣ እንባቆም 3፣6-7፣ መዝ.83፣3/፡፡

ይህንንም በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሡ አባ ጽጌ ብርሃን ፍሬ ከአበባ አበባም ከፍሬ እንደሚገኝ ሁሉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንና ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስን በአበባና በፍሬ እየመለሰ በሚያስረዳው ድርሰታቸው እንዲህ በማለት ገልጸውለታል፡፡ "አፈወ ሮማን ማርያም ጽጌ ቀናንሞ ወአበሜ፣ እስከ ተጸምሐየየ በጾም ዘመልክዕኪ ጊዜ ድክታሜ፣ እምተመነይኩ ተሳትፎ ከመ አኅትኪ ሰሎሜ፣ ወፍሥሓኪ ዘአልቦ ፍጻሜ"፡፡ ሲተረጎምም የሮማን ሽቱ የቀናንሞ አበባ የምትሆኚ ማርያም ሆይ፣ በርሃብ በጾም አበባ የመሰለ የመልክሽ ደም ግባት እስኪጠወልግ ድረስ በስደትና በልቅሶ የደረሰብሽን ችግርና ድካም መከራሽንም ሁሉ እንደ እኅትሽ እንደ ሰሎሜ አብሬሽ ብቀበል ምኞቴ ነበር፤ በዚህ ፍጻሜ የሌለውን ደስታሽን እሳተፍ ነበር፡፡

እንዲሁም አባ አርክ ሥሉስ በስደቷ የደረሰባትን ኀዘን ፣ ልቅሶና ሰቆቃ አስመልክተው በደረሱት "ሰቆቃወ ድንግል" በሚለው ድርሰታቸው እንዲህ አሉ፣ ፀሐይን የምትለብሽ የብርሃን ልጅ ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ከሄሮድስ ዘንድ ልጅሽን ባሸሸሽ ጊዜ የደረሰብሽን ችግሮች ጨረቃን የሚጫሙ እግሮችሽ በመንገድ ብዛትና በአሸዋ ግለት እንደ ጎበጎቡ ሲሰማ ሰው ይቅርና ድንጋዩም ባለቀሰ ነበር”

የእመቤታችን የስደቷ መታሰቢያ ወር በቤተ ክርስቲያናችን የሚከበረው በማኅሌት፣ በቅዳሴና በዝክር ነው፡፡ በወርኃ ጽጌ ባሉት ሳምንታት ከቅዳሜ ማታ እስከ እሑድ ጠዋት አበው ካህናት የሚያቀርቡት ዝማሬ ከቅዱስ ያሬድ ድጓ፣ ከማኅሌት ጽጌና ከሰቆቃው ድንግል የተውጣጣና ሦስት ወገን ያለው ነው፡፡ ዝክሩም፣ በአሁኑ ወቅት በከተሞች አካባቢ እየተረሳ ቢመጣም፣ ዘወትር እሑድ የአንድ አካባቢ ሰዎች ማዕከላዊ በሆነ ቦታ ተሰባስበው በእመቤታችን ስም የሚዘክሩት ነው፡፡

ዐቅመ ደካሞች፣ ድሆችና መንገደኞች ተጠርተው በእመቤታችን ስም እንዲበሉና እንዲጠጡ ይደረጋል፡፡ ይህም ትውፊት እመቤታችን ወደ ኢትዮጵያ በመጣች ጊዜ ኢትዮጵያውያን አባቶችና እናቶች ያደረጉላትን መስተንግዶ ለማሰብ ነው፡፡
የእመቤታችን የቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም የአባታችን አረጋዊው ዮሴፍ ና የቅድስት ሰሎሜ እረዴት በረከት ይክፈለን

https://t.me/maheberenesabho



https://t.me/maheberenesabho




https://t.me/maheberenesabho

✞✞የንግስ መዝሙሮች👏👏👏

07 Oct, 06:26


🔴ግለ ወሲብ እንደሚያደርግህ ልንገርህ?
🔶
➜ከቤተክርስቲያን አስወጥቶህ እዛ ዳግም ልትወጣ የማትችለው ጨለማ ጉድጓድ ውስጥ ይጥልሃል።

➜እግዚአብሔር ይቅር ባይ አይደለም እንድትል ያደርግሃል።

➜የእንስሳነት ስሜት እንዲሰማህ ያደርግሃል።

➜ፈሪ እና ልፍስፍስ እንድትሆን ያደርግሃል።

➜ፈሪሃ እግዚአብሔር ከውስጥህ እንዲጠፋ ያደርግሃል።

➜እራስህን ሁል ጊዜ ሀጥያተኛ እና ቀደለኛ አድርገህ እንድታስበው እና ሁሉ ጊዜ ለፀፀት ይዳርገሃል።

➜ነፍሰ ገዳይ እንድትሆን ያደርግሃል (ካንተ የሚወጣው የወንድ ዘር ነገ እንዳንተ ትልቅ ሰው የሚሆን ሰው ስለሚሆን)

➜ለብቸኝነት አሳልፎ ይሰጥሃል።

➜ያለ ትዳር ኖረህ ትዳር ሲናፍቅህ እንንድትኖር ያደርግሃል።

➜መንፈሳዊነትን ፍፁም እንድትረሳው እና እንደ ልብስህ አውልቀህ እንድትጥለው ያደርግሃል።

🔴ስለዚህ ወዳጄ ምርጫህን አንተው ታውቃለህ!
የሚጠቅምህን መለየትም ትችላለህ ምክንያቱም ይህንን ፅሁፍ አንብበሃል።

🔶ምረጥ፦ እሳት
ወይ
ውሃ


🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
🔴የተዋሕዶ ጅጅ ወደ በመግባት እራስህን ፈትሽ!


https://t.me/maheberenesabho



https://t.me/maheberenesabho




https://t.me/maheberenesabho


https://t.me/maheberenesabho

20,154

subscribers

119

photos

22

videos