ጥቅምት 12/2017 ዓ/ም
ሸዋ አማራ ኢትዮጵያ
በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና ጦር አዛዥ ፊትአውራሪ ኢ/ር ባዩ አለባቸው እና በናደው ክፍለጦር ዋና ጦር አዛዥ ቀኝ አዝማች ይታገስ በተመራ በዚህ ልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙ አሽከር የሆኑት የመርሃቤቴ ወረዳ የብልፅግና አመራሮች በባህርዳር ስብሰባ ሰንብተው እና በአገዛዙ ሰራዊት ታጅበው ከለሚ ወደ መርሃቤቴ አለም ከተማ ለመቀባበል እንዲሁም በዚህ ሳምንት ከአለም ከተማ ያገታቸውን ባለሃብቶች ፣ ታዋቂ ግለሰቦች ፣ወጣቶች እና የነቁ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች ወደ ሸዋሮቢት ለመውሰድ ጉዞ እያደረገ ባለበት ሁኔታ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር መቅደላ ብርጌድ ሶስተኛ ሻለቃ ዛሬ ከቀኑ 7:00 ሰዓት እስከ 8:20 ሰዓት ባደረጉት የደፈጣ ውጊያ በአናብስቶቹ የናደው ክፍለጦር አባላት ከጀማ ድልድዩ አቅራቢያ ልዩ ስሙ አጥበርበር በተባለ አካባቢ መብረቃዊ ጥቃት የተሰነዘረበት ሲሆን ሲሆን ጠላት የአማራን ህዝብ ለመፍጀት ሲጠቀምበት የነበረ አንድ ዙ23 ከጥቅም ውጪ ማድረግ ተችሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የወራሪው ብልፅግና ሰራዊት እስረኞቹን ተቀብሎ ወደ ለሚ እየወጣ ባለበት ሰአት ከ9:00 ጀምሮ እስከ 9:40 በቀጠለው ውጊያ በሮቃ መገንጠያ አካባቢ ላይ አይበገሬወቹ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር የራስ አበበ አራጋይ ብርጌድ አንድ ሻለቃ እና የናደው ክፍለጦር ተወርዋሪ ሰራዊት በጠላት ላይ በወሰዱት ፈጣን ምት ሀለት ሲኖትረክ እና ሁለት ኤፍኤሳር የጭነት አይሱዙ ላይ የነበረ ሰራዊት ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል።
በዚህ የተበሳጨው የአገዛዙ አራዊት ሰራዊት በየመንገዱ ላይ ያገኘውን የአርሶ የደረሰ ሰብል ሲያቃጥልና በከባድ መሳሪያ አካባቢውን ሲያሸብር ውሏል።
''ድላችን በክንዳችን''
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ተጠሪ ክፍል