ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ፡ ጥዑመ፡ ስም
የጌታ፡ ኢየሱስ፡ ክርስቶስን፡ ስሙን ለሚጠራው ጣፋጭ ፡ ነው የጌታ ፡ ኢየሱስ፡ ክርስቶስን ሥጋ ውን ፡ ለሚቀበለው ረኀበ ነፍስን የሚያስወግድ የሕይወት ምግብ ፡ ነው ። የጌታ ኢየሱስ ፡ክርስቶስ፡ ደሙን ፡ ለሚጠጣው ጽምዓ ፡ ነፍስን ፡ የሚያረካ ፡ የሕይወት ፡ መጠጥ ፡ ነው ። አሁንም ፡ እኛን ፡ ለመባረክና፡ ጠላታችንን ፡ ድል ፡ ይነሣልን ፡ ዘንድ ጋሻ ፡ ጦሩን ፡ አሲዞ ፡ ልዩ ፡ መልክተኛውን ወደኛ ፡ ይላክልን።
ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ
ጌታ፡ ኢየሱስ፡ ክርስቶስ፡ ለሰው ልጅ ፡ ሲል ፡ የቆሰላቸው ቍስሎቹ ሕይወቱን አሳልፎ የስ ጠበት ፡ ቅዱስ ፡ መስቀሉ ፡ በፊት ለፊቱ፡ ተቀድሞ ፡ የወይን ምንጭ የሚሆን ፡ በጦር የተወጋው ፡ ጐኑ ፡ ቍርባነ አምልኮ ፡ የሚሆን ሥጋውና ፡ ደሙ ፡ በተዘጋጀበት ቅዱሳን ፡ አርበኞቹ፡ ተሸልመውና፡ ተጊጠው፡ ለግብዣ ፡ በተጠሩ፤ ጊዜ ፡ እኛንም ፡ ወደ ሙሽራው ፡ ሠርግ ፡ቤት፡ በአንድነት፡ ያግባን።
ለጥብሐ፡ ሥጋከ እሴስዮ
መድኃኒቴ ፡ ኢየሱስ ፡ ሆይ ፤ የሕይወት ፡ ምግብ፡የሆነ' ሥጋህን እመገበዋለሁ ፤የሕይወት ፡ መጠጥ የሆነ ፡ ደምህንም ፡ እጠጣዋለሁ ። ፈጣሪዬ ፡ ክርስቶስ ፡ ሆይ ፤ በቀራንዮ ፡ ለመሥዋዕት ፡ የቀረ ብክ ፡ ንጹሕ በግ ነህና ውበትህን አየው ፡ ዘንድ እመ ኛለሁ። ልመናዬን ፡ በሱራፊ'ጽዋ ሙላው ፡ ማኅየዊ ወይም አምላካዊ ፡ በሚሆን ፡ መከራህና፡ ሞት ህም ፡ ቍስለ ፡ ነፍሴን ፡ ፈውሰው።
ለጥብሐ ሥጋከ፡ እጸግቦ
ጌታዬ ፡ ኢየሱስ ሆይ፤ ቅዱስ፡ ሥጋህን፡ በልቼ፡ በልቼ፡ እጠግ በዋለሁ። ክቡር ፡ ደምህንም ፡ ጠጥቼ ጠጥቼ ፡ ከጥሜ ፡ እረካበታለሁ ። ፈጣሪዬ ፡ ክርስቶስ ፡ ሆይ ፤ ጐንህን ፡ በጦር ፡ የተወጋህ፡ የዋህ በግ ፡ እኮን፡ ነህ ። ምናልባት፡ ከማ ርያም ፡ ከሥጋዋ ፡ ሥጋ ፡ ከነፍሷ ፡ ነፍስ ፡ ነሥቶ ፡ ሰው ፡ ሆኖ ፡ አልተወለደም ፡ የሚልህ የቅድስት ፡ ሥላሴ እምነት የሌለው አይሁዳዊ ፡ ከሐዲ ቢኖር እንደተ ራበ ፡ ውሻ አገር ላገር ይዙር። ጐዳና ፡ ከጐዳና ይንከራተት።
አመ ፡ ትመጽእ ለኰንኖ
ጌታዬ፡ ኢየሱስ፡ ሆይ፤ ከእግሮችህና ፡ ከጐንህ ፡ ከፈሰሰው ፡ ደም ጋር ፡ ለፍርድ ፡ በመጣህ ፡ ጊዜ ነፍሴን ፡ ንዑድ ፡ ክቡር ለሚሆን እጅህ ፡ አደራ ፡ እሰጣለሁ ። የሰማይና፡ የምድር፡ ንጉሥ፡ ክር ስቶስ ፡ ሆይ ፤ አሁንም ፡ እራስህን በበትር ፡ የተደበደብከው ፡ መደብ ደብና ፡ እንደባሪያ ፡ ለሠላሳ ፡ ብር የተሸጥከው፡ መሸጥ፡ በዚያን ' በቍርጥ፡ ፍርድ ፡ ቀን ፡ ዋስ ጠበቃ ፡ ይሁኑኝ ።
ስብሐት ለከ
ጌታ፡ ኢየሱስ ሆይ፤ በፍጥረቱ 'ሁሉ፡ አንደበት ፡ ለአንተ፡ ምስ ጋና ፡ ይገባል ። ፈጣሪ ፡ ክርስቶስ ሆይ ፤ አፍኣዊ ፡ ሥጋን ፡ ውሳጣዊ ዛ ሰውነትን ፡ የምትቀድስ ፡ ለአንተ ምስጋና ፡ ይገባል ። ለተራቆቱት ፡ ልብሳቸው ፡ ለአንተ ፡ ለኢየሱስ ፡ ምስጋና ፡ ይገባል ። የማትሻር የማታልፍ፡ንጉሥ፡ ክርስቶስ፡ ሆይ፤ ለአንተ ፡ ምስጋና ፡ ይገባል ። የቅ ዱስ አብ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ሆይ ፤ ለአንተ ፡ ክብር ፡ ምስጋና ፡ ይገባል ለዘለዓለሙ ፡ አሜን