ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

@fionteabewzeorthodox


በዚኽ ቻናል ጽሑፍ የሃይማኖታዊና ሀገራዊ ጉዳዮችን የሚዳስስ ነው

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

22 Oct, 17:54


ማትረፍ ከፈለጋችሁ የምመክራችሁ አንዱ ይኽንን ዩቲዩብ ነው። ተከተሉት!!

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

22 Oct, 17:54


https://youtu.be/_5CmwUBrmnc?si=zLMbRlChzrQiHCM4

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

22 Oct, 16:23


ይስማችሁም አልስማችሁም!!

አብይ ይስማም አይስማም እናንተ ግን ሥራ ሥሩ። የትግራይ ጦርነት በመታለልም ይኹን በቸልታ አልያ በክፋት ብዙ ምእመናን በማለቅ ተባባሪ ኾነን አልፏል። አማራ ክልል እሳት እየዘነበ ነው።

አብይ አሰማም!! ቀጥታ ግን "ካላናገርከን ስብሰባ አንጀምርም" በሉት። ቆራጥ አጥቶ ነው እንጂ ፈሪ ነው። ፈሪ ግን ጨካኝ ነው። ቀጥ ብላችሁ "ጦርነት ዛሬውኑ አቁም አቁም፣ አንተን የምንለምንበት ጊዜ አብቅቷል። በቀጣይ ቀን እናወግዛለን፣ አልያ ከፈለክ ሰብስበህ እሰረን" በሉት። ኢትዮጵያ ያኔ ትፈወሳለች። ተስፋ ይለመልማል። ካልኾነ ግን በቃላት እየተክበሰበሳችሁ ምንም አታመጡም። ተያይዞ መፍረስ ብቻ ነው።

እኔኮ ነኝ በውስጤ የምለው።

https://youtu.be/T9i0k8-Wiyw?si=W48GRrHNbIwIUj2l
ንዋይ ካሳሁን

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

22 Oct, 13:45


ቅጽል

በጠቅላላ ሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ሊቃነ ጳጳሳቱ የተጠሩበት ቅጽል


የወንጌል ገበሬ
የጸሎት አባት
ትጉህና የዋህ
የልማት አርበኛ
የድሆች አባት
ደከመኝ ስለቸኝ የማይሉ
ቆራጥ አመራር ሰጪነት የሚሉ ናቸው!!

እውነቱ ግን በእጅጉ ከዚኽ የራቀ ነው የአደባባይ ኩሸት

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

22 Oct, 12:42


ኃጢአትንም ጽድቅንም የሠሩት በጋራ ነው ቅጣትም ሽልማትም የሚያገኙት በጋራ ነው።

ገማልያም ይኽንን ምሳሌ ተነግሯል:- ዐይነ ስውር እና እግረ ልምሾ ሰው መንገድ ሲሄዱ ይርባቸዋል። ፍራፍሬ ሰርቀው ሊበሉ ያስባሉ እና እንዴት ያድርጉ ዐይነ ስውሩ ፍሬውን አያይም ልምሾው ደግሞ ዛፉ ላይ አይደርስም። ተመካከሩና ዐይነ ስውሩ ልምሾውን ሰው እሽኮኮ ብሎት ወደ ተክሉ ገብተው ቆርጠው በሉ። ባለቤቱ ዳኛ ፊት አቅረባቸው። ዳኛው ማነው የሰረቀው ብሎ ይፍረድ? አንዱ በማየት አንዱ በመሄድ ተባብረዋል። ኹለቱንም ቀጣቸው። ዕውር ያለ ልምሾው ልምሾው ያለ  ዕውሩ ምንም ሊያደርጉ አይችሉም። ስለዚኽ ዳኛው ልምሾውን ሰው ዐይነ ስውሩ ትከሻ ላይ አስቀምጦ በጋራ ፈረደባቸው። ጽድቅን ባደረጉበት በጋራ ይሸለማሉ፣  ኃጢአትንም በሠሩበት መንገድ በጋራ ይፈረድባቸዋል። 

ነፍስ እንደገና ወደ አካሏ ትመለሳለች። አካልም እንደ ገና ሕያው ይኾናል። ይኽ ዳግም ትንሣኤ የምንለው ነው። ከትንሣኤ በኋላ ግን ፍጹም ምድራዊ እውቀቸው ይጠፋል ይቀየራል እንደ መላእክት ስለ ምስጋና ይኾናል። ቤተሰብ ሚስትና ባል እናትና ልጅ አይተዋወቁም። 

ንዋይ ካሳሁን

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

22 Oct, 12:41


መጸነስና መሞት በንጽጽር

በጽንስ ወቅት ነፍስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከግዙፉ ዓለም ጋር ትገናኛለች። ወሊድ በጣም ሕመም ያለው ክስተት ነው። ቅዱስ ዳዊት “አባቴና እናቴ ትተውኛልና፥ እግዚአብሔር ግን ተቀበለኝ።” ይላል መዝ.27:10


ቅዱስ ዳዊት “አባቴና እናቴ ተዉኝ” ሲል ይኽ በጽንስ ግዜ ስለነበረው ነገር ነው የተናገረው። ቅዱስ ዳዊት የእግዚአብሔር ነቢይ የተቀባ ነው። ወደ ኋላ ሄዶ በማኅጸን ስለ ኾነው ነገር አስታወሰ። 

ቅዱስ ዳዊት በእናትና በአባቱ በሩካቤ እንደተገኘ ያውቃል። ዳዊት በማኅጸን በተጸነሰ ጊዜ ተጸንሶ ሲያገኝ ከየት መጣሁ ብሎ እንደ መጠየቅ ነው። እናቱም ተኝታለች አባቱም ተኝቷል ዳዊት ግን ጽንስ ኾኗል። እኔን ለመፍጠር ኃላፊነቱ የማን ነው? ከየት መጣኹ እያለ ይጠይቃል። ብቻውን በማኅጸን ነበር። ጥያቄውን ይጠይቅና መልሱን መንፈስ ቅዱስ ይነግረዋል። “እግዚአብሔር ተቀበለኝ” ይላል። ኹሉም እንዲከናወን ያደረገው እርሱ ነው ይላል። 

እናትና አባቴ ደክሟቸው ተዉኝ ያለው ተኝተው ነበር ነው። እግዚአብሔር ግን ይንከባከበኝ ነበር። ይኽ ለመጀመሪያ ጊዜ ነፍስና ሥጋ ሲገናኙ ነው። ሰው የኾነበትን ቅጽበት። 

ከጽንሱ ከ40 ቀን በኋላ አካሉ ኹሉ ተሰርቶ ያልቃል። በሦስተኛው ወራት አካላት ተግባራቸውን ይጀምራሉ። አዕምሮ ወደ ጭንቅላት mind to brain ፣ መስማት ወደ ጄሮ hearing to ear ፣ ማየት ወደ ዐይን vision to eye ይሄዳሉ። መክሊታቸውን ያገኛሉ። ከአካል ጋር ይያያዛሉ። settling in ቀስ በቀስ ሙሉ ሰው ኾኖ ዘጠኝ ወር ያድጋል። 

ቅዱስ ዳዊት ይቀጥልና “በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ እንኳ አንተ ከእኔ ጋር ነኽና ክፉውን አልፈራም“ ይላል። መዝ.22:4 

የሞት ጥላ ያለው መወለድን (ልደትን ነው) ምክንያቱም በጣም ምቹ ከኾነው ሕይወት ከማኅጸን ውጭ ወደ ኑሮ ዓለም እየመጣ ነው። በነዚኽ መካከል በሸለቆ ውስጥ ያልፋል። አደገኛ መንገድ ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ ራሱን ችሎ ሊተነፍስ ነው። በጣም አስፈሪ መንገድ ነው። ይኽ ጠባቡ የማኅጸን በር ምጥ ነው። 

በዚኽ ሸለቆ ውስጥ ሲያልፍ እግዚአብሔር ብቻ ነው ማሳለፍ የሚችለው። ሞትን ሊያይ ይችላል በዚኽ ሸለቆ። 

ሞትን መጋፈጥ ከመወለድ ጋር ተመሳሳይ ነው birth and death. ልደትም ለሞት የቀረበ ተሞክሮ ወይም ልምምድ ነው። በዚያ መካከል እግዚአብሔር ብቻ ነው ሊጠብቅ የሚችለው። በመወለድም በሞትም ወቅት የሚያሳልፈው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ተመሳሳይ ናቸው። አስፈሪ ነገር ያልፋሉ። ከጽንስ 30 ቀን በኋላ ልጁ ፍጹም ነው። ነፍስ ከሥጋ ፍጹም ስምም ትኾናለች። 

በሞትም ጊዜ ተመሳሳይ ነው። ሞት በቅጽበት የሚኾን አይደለም። ደረጃ አለው። 

ብዙ ሰዎች ከሞታቸው 40 ቀን በፊት ሞት እየመጣ መኾኑን ያውቁታል። አስተውለው ስለማያውቁ ነው። ስሜት አላቸው። የሞትን ሽታ ይሸታቸዋል። ሞት በአስፈሪ ኹኔታ አይመጣም። ለዚኽ ነው ቅዱሳንም አንዳንድ ሰዎች ሞታቸውን አውቀው ኑዛዜ ያደርጋሉ፣ ይሰናበታሉ፣ ስለሞታቸው ይናገራሉ። እየመጣ መኾኑን ይታወቃቸዋል። 

ሞት በጣም አስደንጋጭ ነው። ለክርስቲያኖች ግን ሞት አስደንጋጭ አይደለም። ሂደቱ ግን ቀስ ብሎ ነው የሚከናወነው። መጀመርያ ስሜት ይፈጠራል። ነፍስ ከሥጋ እንደ ተለየች ወዲያው ሥጋን ጥላው አትሄድም። ሥጋዋ ባለበት ስፍራ ትቆያለች። ሰባት ቀን ድረስ ከሥጋው ውጭ አካሉ ላይ ትቀመጣለች። ቶሎ ትታው አትሄድም። ለዚኽ ነው ሰባት ቀን ኀዘን የመቀመጥ ባሕል የመጣው። በአይሁድ seven days of shivah ይሉታል። ቋሚ ሰዎች የሚሰማቸውን ኀዘን ነፍስም ይሰማታል። ነፍስ የሚሰማትን ነው እኛ የሚሰማን። 
ዮሴፍ ለአባቱ ያዕቆብ ሲሞት ሰባት ቀን አለቀሰ። “በዮርዳኖስ ማዶ ወዳለችው ወደ አጣድ አውድማ መጡ፥ እጅግ ታላቅ በሆነ በጽኑ ልቅሶም አለቀሱለት፤ ለአባቱም ሰባት ቀን ልቅሶ አደረገለት።" ዘፍ.50:10

ሦስት ቀን በጣም ከባድ ኀዘን ነው። ኀዘንተኛው ምግብ እሺ አይለውም፣ እንቅልፍ ያጣል፣ በጣም ግራ ይገባዋል። አስፈሪ ግን አይደለም ኀዘኑ ግን ጽኑዕ ነው። አራቱ ቀን ኀዘኑ እየቀነሰ ይሄዳል። በሰባተኛው ቀን ነፍስ ደግማ ከሥጋ ጋር እንደማትዋሐድ ታውቃለች። ሥጋን ለቃ ትሄዳለች። በዚኽ ምክንያት ኀዘንተኞች መቀመጥ ያቆማሉ። ነፍስ ተረጋግታለች። ለራስህ ግን ማዘንህ ይቀጥላል። 

30 ቀን በኋላ በሰማያት መኖር ትጀምራለች። ቢበዛ 12 ወር ነፍስ በምድር የነበራትን ትዝታ እየቀነሰች ትመጣለች። ይኽ ወቅት የሽግግር ወቅት ነው። ከምድራዊ ኑሮ ወደ ሰማያዊ ኑሮ ይቀየራል። ይኽ ኁኔታ ሲኦልም ገነትም ሊኾን ይችላል። እንደ ነፍስ ጽድቅ ኹኔታ። ወደ ደስታ አልያ ወደ ለቅሶ ይቀየራል። ገነት ከገባች ደስታን መደሰት ትጀምራለች። አይታው ሰምታው ወደ ማታውቀው ደስታ። ሲኦልም የገባችው አይታው ሰምታው ወደማታውቀው ስቃይ። የገነትም ደስታ ቀስ በቀስ እያደገ እያደገ ይመጣል። 

ሕጻን ልጅ በምጥ ወደ ዓለም እንደሚመጣ ወደ ሞትም በምጥ ነው የሚኬደው። ነፍስ ወደ ሰማይ የሚደረግ ጉዞ መኾኑን ታውቃለች። ነፍስ በምድር ላይ የኾነውን ነገር ሙሉውን ታውቀዋለች። ትውስታዋ አለ። የኖረችው ምድር ላይ ነው። የኾነውን ኹሉ ታውቃለች። እውቀቷ፣ የነፍስ ረቂቅ አካሏ አይጠፋም። በተለይ ቤተሰቧን አትረሳም፣አይጠፋም። 
በምድር ስላሉት ታስባለች። እንደውም ከሥጋ በኋላ ነፍስ ቀድሞ ከነበራት በላይ መስማት ማየት መገንዘብ ትችላለች።  ከሥጋ መለየት በኋላ ከፍ ትላለች። በሥጋ አካል አትገደብም። ስሜቷም ከምድር ይልቅ ከፍ ያለ ስሜት አላት። ለደስታም ይኹን ለስቃይ። ስለ እኛም ይጸልያሉ። 
ዛሬስ በመስተዋት በድንግዝግዝ እንደምናይ ነን በዚያን ጊዜ ግን ፊት ለፊት እናያለን፤ ዛሬስ ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ በዚያን ጊዜ ግን እኔ ደግሞ እንደ ታወቅሁ አውቃለሁ።” 1 ቆሮ.13:12

ባለጠጋው ነዌ ከሞተ በኋላ በሲኦል ሳለ ወንድሞቹን አስቧቸዋል። “እርሱም፦ እንኪያስ፥ አባት ሆይ፥ ወደ አባቴ ቤት እንድትሰደው እለምንሃለሁ፤ አምስት ወንድሞች አሉኝና” ሉቃ.16:27


ሙሉ በሙሉ ትውስታ memory የሚጠፋው ከዳግም ምጽዓት በኋላ ነው። ነፍስ አትሞትም። ሞት ማለት ሥጋ ነፍስን ሲለቃት ማለት ነው። የሚሞተው ሥጋ ነው። ነፍስ ሕያውነቷ ይቀጥላል። ሥጋና ነፍስ ሲለያዩ ነው ሞት የምንለው። 
በገነት ያለችም ነፍስ እንዲኹ ቤተሰቦቿን እያሰበች እርሷ ወዳለችበት እንዲመጡ ትመኛለች ትጸልያለች። “ሙታን ይስዕሉ ለሕያዋን” የሚለው ይኽንን ነው

በሞት የማናዝንበት ምክንያት ምድራዊ ሕይወት አጭር መኾኑን ማወቃችን ነው። ሞትም ጊዜያዊ ነው። ነፍስ ተመልሳ ሥጋን ለመዋሐድ ትጠብቃለች። የዛሬ ኹለት ሺኽ የሞተ ሰው ነፍስ ተመልሳ ወደ ሥጋዋ ለመመለስ ትጠቃለች። አካሏ ነው። The Resurrection of body. 
ይቀጥላል

ንዋይ ካሳሁን


👇

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

22 Oct, 12:41


ይኽንን ጽሑፍ በጥንቃቄ ያንብቡት ጊዜ ሲገኝ የማስረጃ ጥቅሶችን ማጣቀሻዎችን አቀርባለሁ። 👇

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

21 Oct, 23:41


ስንፍናችን ገደብ የለውም "መግለጫ አይጠቅምም፣ ሰልፍ አይጠቅምም" የምንል ነን። እነርሱ ግን መግለጫ ምንም አያመጣም ብለው አይንቁትም ። አቅሙን ያውቁታል።

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

21 Oct, 22:54


አሐቲ ድንግል

የሊቀ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን አዲሱ መጽሐፍ ነው። ለወትሮው መጽሐፍ ሲወጣ ሰው የሙያመጣልኝን ማፈላለግ እጀምር ነበር።

የልብን ፍላጎት የሚያውቅ ወዳጅ መቼስ ጥቂት ነው። እናም ለሥራ ወደ አሜሪካ ያቀናው ወንድሜ ፕ/ር እንግዳ አበበ ሰላም ሊለኝ ደውሎ መምጣቱን ነገረኝ። አሐቲ ድንግልን አምጥቼልሃለኹ ሲለኝ ደነቀኝ። ምን ይባላል የልብ ወዳጅ ማለት ይኽ አይደል። ድንግል ትስጥልኝ።

የመጽሐፉን ሽፋን፣ ምስጋናውን አበርክቶውን፣ አርዕስት ማውጫ ይዘቱን አነበብኩት።

የአባን መጽሐፉን ያዘጋጁበትን ምክንያት አመሻሹን አነበብኩት። እንቅልፍ አልመጣ ሲል አንድ ምዕራፍ ቀመስኩለት። መጽሐፍ ሳይነበብ ስለተደራረበብኝ አሁን አልጀምረውም።

ንባብ ጊዜ ይፈልጋል። ጊዜ ስል ሰዓት ሳይኾን የንባብ ፍላጎት መምጣት ማለት ነው። በጣም ከባዱ ነገር የንባብ ድባብ መፍጠር ነው። ያውም በአሜሪካ። ወቅቱ ንባብ እንቢ የሚልበት ወቅት ነው። ቀድሞ የጀመርኩትስ ስጨርስ ለማንበብ ነው። ንባብ ዲሲፒሊን ይፈልጋል።

መጽሐፉ ይደንቃል አባታችን የጻፉበትን መንፈስ ያሰቡበትንም ምክንያት ሳነብ መጽሐፉ ታላቅ ድካም የተደከመበት ነው።

መጽሐፉ ጥም ቆራጭ ተጠቃሽ መጽሐፍ ነው። አንብቤ ስጨርስ በዝርዝር እመለስበታለሁ።

ንዋይ ካሳሁን

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

21 Oct, 17:28


https://youtu.be/tbTBIgAmf1Q

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

21 Oct, 16:29


ኡኡኡኡኡኡ

ይሰሙ እንደኾን ብዬ ነው። ለምነን አባብለን ሥራቸው ተነጥፈን፣ ተመካክረን አልሰሙንም። ዛሬ ላይ ለአንድ አባት ብቻ ነው የልቤን ኀዘን የነገርኳቸው። "ትሰሙናላችሁ ብዬ አይደለም ነገር ግን ምን ያክል እንደምናዝን እንዲይልውቁ ብቻ ነው.... " ብዬ ነው የነገርኳቸው። አኩርፌም አዝኜም ከማናችሁም ርቄያለኹ ነው ያልኳቸው።

ለድሮው ቢኾን "ይኽ ቢኾንስ እንዲኽስ ብታደርጉ እያልኩ የማዋውየው ከግማሹ በላይ ነበሩ። አይሰሙም አልሰሙም። ዛሬም ስንጮኽ ከሰሙን ብዬ ነው።
ኦርቶዶክሳውያን እያለቁ ነው። ቢያንስ በአብይ ፍጅት 3 ሚሊየን ኦርቶዶክሳውያን አልቀዋል። ስደተኛው ረሃብተኛው 20 ሚሊየን ይበልጣል። ሰሜኑን እየሰበረው ነው። ግድ የላችሁም ስሙን።
አዲስ አበባ በወራት ውስጥ ሕንጻ ብቻ ታቅፋችሁ ትቀራላችሁ። መጨረሻ ቤተ ክህነቱም ሕንጻ አይቀርለትም። መንበረ ፓትርያርክ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በቅርቡ አጥሩና ቤተልሔሙ ይፈርሳል። ምልክት ተደርጎበታል።
አዲስ አበባ የሚተርፍ ክርስቲያን የለም። ነቅሎ ያባርረዋል። አብይን የማውገዝ ጉልበት ብታጡ እንኳ ለሕዝቡ ተጋድሎ አውጁለት መከራውን በጋራ እንካፈላለን በሉት። ስቃዩን በግልጽ ተናገሩና ተቀላቀሉለት። እያለቀሰ ቤተክርስቲያንን ጥሎ እየተሰደደ ነው። መንግሥት ይስማን ብላችሁ አትጨነቁ ከምእመናችሁ ጋር ኹኑ። ጦርነቱን በግልጽ አውግዙ አትለምኑ። ተደራደሩብ፣ ተነጋገሩ እያላችሁ አታውሩ። አብይን አቁም ብላችሁ አውግዙት። ቀጥታ ጦርነቱ መካከል ሂዱ።
ዘንድሮ ጥር ጥምቀት ጃንሜዳ ለጥምቀት የሚወጣ ታቦት አለ? ክርስቲያን አለ? ከምእመኑ ጎን ኹኑ። ተቃጠል ብሎኝ ነው እንጂ ምን በወጣችሁ ትሰማላችሁ። ካድሬ ቢደውል ዳንኤል ቢደውል ይሰማል።

እናንተ ስለ ቅያሬ፣ ስለ በጀት፣ ስለ መኪና መግዣ ፣ ስለ ኮሪደር መአት ተወያዩ።

ንዋይ ካሳሁን

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

21 Oct, 16:08


ከሞት በኋላ ያለ የነፍስ ግብግብ 

ሰው ሲሞት ነፍሱ ከሥጋው ትለያለች። መንፈሱ ከነፍስ ጋር ወደ ሰማይ ትሄዳለች። ሞት እንዲኽ ቀላል አይደለም። ይኽንን ለመረዳት በጥቂቱ የብሉይ ኪዳንን የነፍስ ኹኔታ እንመልከት። 

ሰው እንደ ተወለደ ሳጥናኤል ከጭፍሮቹ አንዱን ይልክና ይቆራኘዋል። በዚኽም ሰውየው ክፋት እንዲሠራ ያስጨክነዋል። ጣኦት እንዲያመልክ ወደ እግዚአብሔር ዞር እንዳይል ያደርገዋል። 

ሰውየው ሲሞት ደግሞ ሳጥናኤል እየተገለጸ ጽልመት ፊቱን እያሳየ ብዙ ያሰቃየዋል ያስፈራራዋል። በዚኽም ሰውየው ላብ አልቆ ደም እስኪወጣው ድረስ ይጨነቃል እያንፈራገጠ መሬቱን ይቆፍራል። በስተመጨረሻ ደሙ ይደርቃል ነፍሱ ትለያለች። ወደ ሲኦል እያዳፋ ይወስድና ወደ ስቃይ ይወስዳታል። 

በሐዲስ ኪዳን የተጠመቀ ክርስቲያንን ሰይጣን አይቆራኘውም። ለሰይጣን ተላልፎ እንዳይሰጥ የሥላሴ ልጅነት ይጠብቀዋል። ሰይጣን ያንን ሰው አጥብቆ ይጠላዋል። የተጠመቀ ቀን ለማሳሳት መድከም ይጀምራል። በሞተ ጊዜ ጭንቀት የለበትም። ጦርነቱ ነፍሱ ከወጣች በኋላ ይቀጥላል። ጠባቂ መላእክት መካከልና በሰይጣን መካከል ይኾናል። ሰይጣን ይኽች ነፍስ የእኔ ናት ይላል መዝገብ እየገለጠ ይከራከራል። አየሩን ላለማሳለፍ ከፍተኛ ውጊያ ያደርጋሉ። “በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው።” ኤፌ.2:1

መላእክት ደግሞ ደግ ሥራዋን እየጠቀሱ ሊያሳልፏት ይከራከራሉ። ሰይጣናት ወደ ሥጋዋ መልሰን እናሰቃያት እያሉ ይዋጋሉ። ነፍስ በመካከል ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ትወድቃለች። በዚኽ መልክ ከፍተኛ ውጊያ ተደርጎ ነው ነፍስ የምታልፈው። 
የኹሉም የብሉይ ኪዳን ነፍሳት በዚኽ መልክ ያለፈች ስትኾን የሙሴ ነፍስ ግን የተለየ ጥበቃ ተደርጎላታል። ሙሴን ቅዱስ ሚካኤል ሰይጣን ነፍሱን እንዳይወስዳት ተከራክሯል። ሰይጣን  ሰው ገድሏል የእኔ ነፍስ ናት ቢልም “እግዚአብሔር ይጣልኽ” እያለ ገሰጸው። 

ርቱዓ ሃይማኖት ስለ ሙሴ ሥጋ ሲናገር እንዲኽ ይላል:- ሙሴ በሚሞትበት ጊዜ ግን ሚካኤል ነፍሱን ያዛት፤ መልአከ ሞትም ፈጽሞ አልነካውም፡፡ ሰይጣን የሙሴን ነፍስ ሲያሳርጋት በተመለከተው ጊዜም እኔ መጥቼ የሞት ጽዋን ሳላጠጣት ለምን አወጣሃት አለው፡፡

ምንም ዓይነት የሞት ጻዕር አልነካውምና፡፡ አንተ በይውህና፣በሰላም ነፍሱን አውጥተሃልና፡፡ የአማፂው፤ የወንጀለኛው የአዳም ልጅ ነውና፡፡ ሚካኤል ግን የስድብን ቃል በሰይጣን ላይ ይሳደብ ዘንድ አልደፈረም፡፡ እግዚአብሔር ይገስጽህ አለው እንጂ። ያን ጊዜም ሰይጣን ሸሸ፡፡ ሚካኤልም የሙሴን ነፍስ ወደ እግዚአብሔር ዐሳረጋት፡፡ ስለዚህም ጌታችን "ሞትን የማይቀምሱ ከዚህ አሉ" አለ፡፡ ማቴ.17:28

ንዋይ ካሳሁን

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

21 Oct, 15:23


https://youtu.be/wwv5uMQtZP4?si=a6GyVYW37rN9ruE8

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

21 Oct, 12:11


ይረርም ይምረርም

ቤተ ክርስቲያን እንደ ተቋማዊ መዋቅር ቤተ ክህነት እንለዋለን። ይምረርም ይረርም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ ተቋሟ ይኽ ባሳለፍነው ሳምንት 43ኛ ዓመት ጉባኤውን ያካሄደው ጠቅላላ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ነው። ይኽ ጉባዔ ቤተ ክርስቲያን እንደ ተቋም ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ከዚያም ቅዱስ ሲኖዶስ ድረስ ያለ መዋቅራዊ ሰንሰለት የያዘ ነው።
በዚኽ መዋቅር ውስጥ የማይካተት ነገር ቤተ ክርስቲያን የላትም። ምእመኑም ካህኑም፣ አገልግሎቱም ቅርሱም ሕንጻውም፣ ይዞታውም፣ ገንዘቡም መዋቅሩ ይኽ ነው። 

ይኽንን ያነሣሁበት ምክንያት በሚገባውም በማይገባውም ቤተ ክህነት እያልን ስንወቅስና ስንተች ቀላል ነገር እንዳይመስለን ለማስገንዘብ ነው። የቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ ምሰሶ ወይም የጀርባ አጥነት ማለት ነው። የቤተ ክርስቲያን የጀርባ አጥንት ምሰሶዋ ይኽ ከአጥቢያ እስከ መንበረ ፓትርያርክ ያለው የዕዝ ሰንሰለት እንጂ ማኅበረ ቅዱሳን እንዳልኾነም ማወቅ ይጠቅማል። ሌላው ኹሉ ቢደረትና ቢደረብ እዚኽ ላይ የተለጠፈ ነው። 

ይኽ ተቋም ጠንካራ ከኾነ ቤተ ክርስቲያን ጠንካራ ትኾናለች። ይኽ መዋቅር ጠንካራ ካልኾነና ሥራውን በአግባብ ካልሠራ ቤተ ክርስቲያን ደካማ ትኾናለች። ቀደም ባሉት ጊዜያት ማለትም 1950ዎች በፊት ይኽ መዋቅር አይነት አይደለም የነበረው። ይኽንን ቅርጽ የያዘው በተለይ የደርግ መምጣት ጀምሮ ነው የዛሬውን ቅርጹን የያዘው። ከዚያ በፊት መዋቅራዊ ቅርጹ የተለየ ነው። 

ደርግ ሲመጣ የቤተ ክርስቲያን ርስት ጉልቷን ሐብቷን ኹሉ በመንጠቁ ምን ማድረግ ይሻላል በሚል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ዘመን መሠረት የጣለ ነው። ቤተ ክርስቲያን ምእመናኑን አስተባብራ ገንዘብ ከራሷ እየሰበሰበች አገልግሎቷን ታስቀጥል የሚል ነው። ያ ነው እስከ ዛሬ ቀጥሎ 43ኛ ዓመት ጉባዔውን ያካሄደው። 

በብዙ የውስጥም የውጭም ፈተና በተለይም የውስጥ አሰራርን ካለመጠንከር በመነሣት ይኽ መዋቅር በእጅጉ የተጎዳ መዋቅራችን ነው። አቅሙም አቋሙም የደከመ ስለኾነ ነው ወቀሳም ከሰሳም የምናበዛው እንጂ ስለማያስፈልገን ስለማይጠቅመን አይደለም። 

አሉበት የምንለው መዋቅራዊ ፈተና እንዲኽ በቀላሉ የምንዘልቀው አይደለም። ራሱን የቻለ ሰፊና ጥልቅ ጥናት ይፈልጋል። ይኽም ኾኖ ይኽ መዋቅር ባይኖር ቤተ ክርስቲያን በዛሬው ዘመን መምራት ጭርሱኑ አይታሰብም። የተበተነ ጨው በለው። ቤተ ክርስቲያን እንድትቀጥል ከፈለግንም የምናሻሽለው የምንለውጠው ይኽንን መዋቅር ይኽንን ተቋም ብቻ ነው። ምንም ላይ ብንንጠለጠል ይኽ ምሰሶ ሲያጎነብስ አብሮ ማጎንበስ ሲሰበር መዘርገፍ አይቀርም። ምክንያቱም የድሮው ሳይኾን ያለንበት መዋቅር ይኽ ስለኾነ ነው። 

ታላላቅ አድባራት፣ ገዳማት፣ አብነት ትምህርት ቤቶች፣ መንፈሳዊ ኮሌጆች የካህናት ማሰልጠኛዎች ኹሉም በዚኽ መዋቅር ሥር የሚመሩና የሚተዳደሩ ናቸው። ይኽ ጠቅላላ መዋቅር የሚመራበት ሕግ ደግሞ አንዱ "ቃለ አዋዲ" በመባል ይታወቃል። ሲኖዶስ የሚመራበት ደግሞ "ሕገ ቤተክርስቲያን" ይባላል።

የእኽል ክምር የሚበላሸው አንዴ ከአከማመሩ ብልሽት ከአናቱ ዝናብ ሲገባው ነው። አልያም እኽቱ ደርቆ ሳይወጣለት ታጭዶ ከተከመረ ነው። 

ቤተ ክህነት ከአናቱ ተበላሸ ማለት ከላይ ውኃ እንደ ገበበት ክምር ቁጠሩት። እስከ ታች አጥቢያ ድረስ ይበላሻል። የገጠመን ችግር ይኽ ነው። ከላይ የሚገባው ልፍስፍስነት ግዴለሽነት፣ ሙስና፣ ደካማ አሰራር መንፈሳዊነት መጉደል እስከ ታች ይዘልቃል። በጥቅሉ ቤተ ክርስቲያን ትደክማለች ብሎም ትጠፋለች። ነገም ከነገ ወዲያም ማዘመን፣ መፈተሽ ማሻሻል መለወጥ የሚገባው ይኽንን ነው። 

ንዋይ ካሳሁን

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

20 Oct, 20:16


የእኽታችን እህተ ማርያም (ሔርሜላ ጌታቸው) ሽኝት

"ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን፦ እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።"

ማቴ.22:31

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

20 Oct, 16:56


https://youtu.be/3KnRJTHWmpw?si=yN5yKBe7TUyN4mWp

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

19 Oct, 17:20


ተቃውሞ ማለት ባለጋራ ሜዳ ላይ ሄዶ መግጠም ማለት ብቻ ሳይኾን በራስህ ስፍራ ላይ ተገቢውን ዝግጅትና ሥራ መሥራት ማለት ነው። ትልቁ የማጥቂያ መንገድ ይኽ ነው። ከዚያ እንደ ባላጋራኽ አይነት ወደ እርሱ ትሄድበታለኽ።

13,124

subscribers

4,049

photos

1,126

videos