Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

@ethiopianexporters


This Ethiopian Exporters page is created just to promot Ethiopian exporters, inform on updates, exchange information and contacts... Please add any ethiopian exporter here

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

16 Oct, 15:42


ኢትዮ ቴሌኮም “ለመጀመሪያ ዙር” 100 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ ማቅረቡን አስታወቀ

መንግስታዊ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢው ኢትዮ ቴሌኮም፤ “ለመጀመሪያ ዙር” እያንዳንዳቸው 300 ብር ዋጋ ያላቸውን 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ለሽያጭ አቀረበ። ተቋሙ ይህንን የገለጸው 10 በመቶ የባለቤትነት ድርሻውን በይፋ ለህዝብ መሸጥ መጀመሩን ዛሬ ረቡዕ ጥቅምት 6፤ 2017 ባስታወቀበት መርሃ ግብር ላይ ነው።

በካፒታል ገበያ በኩል ለሽያጭ የቀረበውን የኢትዮ ቴሌኮምን አክሲዮን መግዛት የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ፤ እስከ 3,333 አክስዮን ድረስ መግዛት እንደሚችል ተገልጿል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

[በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ይታከልበታል]

@EthiopiaInsiderNews

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

15 Oct, 12:08


መንግሥታዊው ባንክ የዶላር መሸጫ ዋጋ ቀነሰ።

በመንግሥታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዶላር ከብር አንጻር ያለው ምንዛሬ በመሸጫው ቅናሽ አስመዝግቧል። ባንኩ በመሸጫ ዋጋ ላይ ቅናሽ ሲያደርግ በመግዣው ላይ መጠነኛ ጭማሪ አድርጓል።
ባንኩ የባለፈውን ሳምንት ቀናት እንዲሁም ትናንት ጥቅምት 4/2017 ድረስ አንድ የአሜሪካን ዶላር በ112.39 ሲገዛ የነበረ ሲሆን፣ መሸጫው 123.63 ነበር።

ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 5/2017 ባወጣው አዲስ ዋጋ የመግዣ ዋጋው ላይ መጠነኛ ጭማሪ በማድረግ አንድ ዶላር 113.13 እንደሚገዛ አሳውቋል። በአንጻሩ ባንኩ በመሸጫ ዋጋ ላይ ቅናሽ በማድረግ ለአንድ ዶላር 115.39 ዋጋ አስቀምጧል። በመሸጫ ዋጋ ላይ የተመዘገበው ቅናሽ 8.24 ብር ነው።

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

10 Oct, 03:50


ባሳለፍነው ሳምንት እንዲሁ የቡና ዋጋ የመጨመር አዝማሚያ አላሳየም።
በኒውዮርክ ገበያ
NYCE Market Closing
Date: 10/10/2024
248.98 US cents lb.   
ዋጋ ላይ ይገኛል።

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

03 Oct, 06:30


ሰሞኑን የቡና ዋጋ የመቀነስ አዝማሚያ እያሳየ ነው።
በኒውዮርክ ገበያ
NYCE Market Closing
Date: 2/10/2024
Arabica = ባለፈው ሳምንት ሲሸጥ ከነበረበት 275.39 cents lb
ወደ 
256.2 US cents lb.   
ወርዷል።

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

21 Aug, 04:38


የአለም የቡና ዋጋ የመጨመር አዝማሚያ ላይ ነው። ካለፈው አመት የዚህ ወቅት ዋጋ ጋር ሲነፃፀር ከ $1.43/lb ወደ 2.53/lb ደርሷል። 66% በላይ ጨምሯል ማለት ነው።

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

24 May, 06:55


የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቡና ማጓጓዣ ዋጋን በግማሽ ቀነሰ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቡና ማጓጓዣ ዋጋን በኪሎግራም ከ3 ወደ 1.50 ዶላር ቀነሰ
አየር መንገዱ እንዳወጣው መግለጫ ለዋጋው መቀነስ ዋናኛ ምክንያት የሆነው በኤዥያ እና መከከላኛው ምስራቅ ወስጥ እየየ ያለውን የቡና መጠጣት መጨመር ለማበረታታ እና የኢትዮጵያን ቡና ለአለም አቀፈ ገበያ ለማስተዋወቅ እንደሆን ተናገሯል።

በኪሎግራም ከ3 ወደ 1.50 ዶላር ማጓጓዣ ዋጋ መቀነስ ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ቡና ላኪዎችም ሆነ ገዥዎች በተለይም ለመካከለኛው ምስራቅና እስያ ገበያ የሚውል የተቆላ ቡና እና አነስተኛ መጠን ያለው ቡና ኤክስፖርት አድራጊዎችን ማገዝ ላይ ያተኮረ ነው ሲሉ አብራርተዋል።
በተለይም ወደ ኤዥያ እና መከከላኛው ምስራቅ ትኩረት እየተደረገ ያለው የአውርፓ ህብረት ያወጣውን የደን መመሪያ ተከተሎ ሊከሰት የሚችልውን የገበያ እጥረት ከወዲሁ አማራጮችን ለማመቻቸት ነው። በቅርብ ጊዜያትም ቻይና ከፍተኛ የኢትዮጵያ ቡና መዳረሻ እየሆነች መምታቷ የሚታወቅ ነው።

ምንጭ፡ አዲስ ስታንዳርድ
@EthCoffeeCommunity
@EthCoffeeNetworkNews

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

06 May, 10:08


🔴 በ2016 በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ከቡና ምርት 835 ሚሊዮን 230 ሺህ ዶላር ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ በዘጠኝ ወራት ከ174 ሺህ 596 ቶን በላይ የቡና ምርት ወደ ውጭ ሀገራት መላኩም ተገልጿል፡፡

የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ኡመር ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በ2016 በጀት ዓመት ከ 174 ሺህ 596 ቶን በላይ ቡና ውደ ውጭ ተልኮ 835 ሚሊዮን 230 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡

በዘንድሮ ዓመት በዘጠኝ ወራት የተገኘው ገቢ ቀደም ባሉት ዓመታት ከተገኘው አንጻር የተሻለ መሆኑን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አመላክተው፤ የቡና ምርት ገቢን ለማሳደግ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የማሻሻያ ስራ ተሰርቷል ሲሉ አስረድተዋል፡፡

በተሰሩ የሪፎም ስራዎች የቡና ምርት ገቢ ወደ ቢሊዮን ዶላር ማደጉን ጠቁመው፤ ባለፈው ዓመት ከአንድ ነጥብ 33 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የተገኘ ሲሆን፤ በዘንድሮ ዓመት አንድ ነጥብ 75 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ በስፋት እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በዘንድሮ ዓመት በዓለም አቀፍ ደረጃ የቡና ዋጋ መውረድ እና ከወደብ ጋር ተያይዞ በቀይ ባህር አካባቢ የተፈጠረው ችግር በቡና ግብይት ላይ ማነቆ እንደነበር አንስተዋል፡፡

ከወደብ ጋር ተያይዞ ላጋጠመው ችግር የቡና ምርት ወደተለያዩ ሀገራት በመኪና እንዲጓግዝ ከማድረግ ጀምሮ የተለያዩ ጥረቶች መደረጋቸውን ተናግረዋል። የቡና ምርት በስፋት ሲገኝ የገበያ መውረድ ያጋጥማል፤ ስለዚህ ስፔሻሊቲ ቡና በስፋት ለመላክ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
🔴🔴🔴🔴🔴
አቶ ሻፊ እንዳስታወቁት፤ በዘጠኝ ወራት ከነባር የቡና ምርት መዳረሻዎች በተጨማሪ አዳዲስ ገበያዎችን የማፈላለግ ስራ ተከናውኗል። የኢትዮጵያ ቡና የመግዛት ድርሻቸው እስከ 10 ባለው ደረጃ ያልነበሩ ሀገራት፤ ከአንድ እስከ 10 ባለው ደረጃ መቀላቀል ችለዋል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የተባበሩት አረብ ኤምሬት፣ ሱዳን እና ቻይና ቀደም ብሎ የኢትዮጵያን ቡና በመግዛት ከአንድ እስከ 10 ባለው ደረጃ ያልነበሩ ሀገራት ሲሆኑ፤ በዘጠኝ ወራት ቻይና ሰባተኛ፣ ሱዳን ስምንተኛ እና አረብ ኤምሬት ዘጠነኛ ደረጃ በመያዝ የኢትዮጵያ ቡና መዳረሻ ሆነዋል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ እንደተናገሩት፤ ከዚህ በፊት የገበያ ሰንሰለት መርዘም፤ ቡና በእጅ ስለሚነካካ ገዚዎች በሚፈልጉት ደረጃ ጥራቱ የተጠበቀ ምርት ማግኘት አስቸጋሪ ነው፡፡

ችግሩን ለመቅረፍ በመሃል ያለውን ሰንሰለት በማሳጠር የቡና አቅራቢና ሻጭ በቀጥታ እንዲገናኙ ተደርጓል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም አርሶአደሮች በማህበር ተደራጅተው በቀጥታ ቡና ለውጭ ገበያ እንዲያቀርቡ የሪፎርም ስራ ተግባራዊ እየተደረገ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ (አዲስ ዘመን) የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት
ስልክ፡  +251115514005
ፋክስ፡  + 251115517699
P. O. Box 517,
ኢ.ሜይል: [email protected]
ድረ ገጽ: www.ethiopianchamber.com
ቴሌግራም      t.me/ethiopiachamber
ትዊተር         https://twitter.com/EthiopiaChamber
ፌስ ቡክ፡   https://www.facebook.com/EthiopianChamber
Youtube:https://www.youtube.com/channel/UCMEZ4TO8dQiIJvk2IQkTxhA
Linkedin(ሊንክዲን):https://www.linkedin.com/company/ethiopianchamber/in

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

02 May, 03:24


አፍሪካ እና አውሮፓ በባቡር ትራንስፖርት ሊገናኙ ነው ተባለ

የባቡር ትራንስፖርቱ ለ2030ው የዓለም ዋንጫ እንደሚደርስም ተገልጿል

የ2030ዋ ዓለም ዋንጫ በስፔን ፖርቹጋል እና ሞሮኮ አስተናጋጅነት እንደሚካሄድ ይጠበቃል

ተጨማሪ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://bit.ly/3QnLKkE

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

02 May, 03:24


የተሻለ ወርሀዊ ደመወዝ የሚከፈልባቸው የአፍሪካ ሀገራት የትኞቹ ናቸው?

ሲሸልስ ሊቢያ እና ሞሮኮ በአንጻራዊነት የተሻለ ደመወዝ የሚከፍልባቸው ሀገራት ናቸው

በኢትዮጵያ አማካኝ ወርሃዊ ደመወዝ 150 ዶላር ነው

ተጨማሪ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://bit.ly/3QpNGJB

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

26 Apr, 02:07


ሚንስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ በወጪ ንግድ ላይ የቀረጥ ማበረታቻ ሥርዓት የሚደነግግ ረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ አጽድቋል።

ምክር ቤቱ፣ የወጪ ንግድ ቀረጥ ላይ ማሻሻያ በማድረግ በዘርፉ ላይ ቀረጥ እንዲቀንስ የወሰነው፣ ለአገሪቱ ኢንደስትሪ ልማትና ኢንቨስትመንት የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ለማሳደግ፣ በወጪ ንግድ መስክ የተሠማሩ ባለሃብቶችና ኩባንያዎችን ለማበረታታት እንዲኹም የወጪ ንግዱን ዘርፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እንደኾነ ገልጧል።

መንግሥት በዘርፉ ላይ የቀረጥ ማሻሻያ ያደረገው፣ የውጭ ባለሃብቶችና ኩባንያዎች ከነዳጅ እና ማዳበሪያ ውጭ ባሉ ሸቀጦች በጅምላ እና ችርቻሮ የወጪና ገቢ ንግድ እንዲሠማሩ በፈቀደ ማግስት ነው።
                      የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት
ስልክ፡  +251115514005
ፋክስ፡  + 251115517699
P. O. Box 517,
ኢ.ሜይል: [email protected]
ድረ ገጽ: www.ethiopianchamber.com
ቴሌግራም      t.me/ethiopiachamber
ትዊተር         https://twitter.com/EthiopiaChamber
ፌስ ቡክ፡   https://www.facebook.com/EthiopianChamber
Youtube:https://www.youtube.com/channel/UCMEZ4TO8dQiIJvk2IQkTxhA
Linkedin(ሊንክዲን):https://www.linkedin.com/company/ethiopianchamber/in

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

18 Apr, 10:26


🔴 የውጭ ባለሀብቶች በጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቀደ

ከዚህ ቀደም ለአገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ተከልለው የቆዩ የወጪ፣ የገቢ፣ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ዘርፎች ለውጭ ባለሃብቶች ከፍት እንዲሆኑ ተደረገ፡፡

በዚህም መሰረት የውጭ ባለሀብቶች በጥሬ ቡና፣ በቅባት እህሎች፣ ጫት፣ ጥራጥሬ፣ ቆዳ እና ሌጦ፣ የደን ውጤቶች እና የቁም እንስሳት የመላከ የወጪ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቅዷል፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን እና የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጉዳዩ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ 🔴🔴🔴🔴

በመግለጫው ላይ እንደተገለፀው፤ የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሟሉ የውጭ ባለሃብቶች ከማዳበሪያ እና ነዳጅ በስተቀር በሁሉም የገቢ ንግድ ኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት ይችላሉ፡፡

የጅምላ ንግድን በተመለከተ ከማዳበሪያ ጅምላ ንግድ በስተቀር በሁሉም አይነት የጅምላ ንግድ መስኮች መሰማራት ይችላል ተብሏል፡፡ 🔴🔴🔴🔴

በተጨማሪም የውጭ ባለሀብቶች ቅድመ ሁኔታዎችን ሲያሟሉ ለአገር ውስጥ ባለሃብት በተከለሉ ሁሉም የችርቻሮ ንግድ ስራዎች መሳተፍ እንዲችሉ መፈቀዱም ተጠቅሷል።

በጉዳዩ ላይ በባለድርሻ አካላት የተካሄዱ ዝርዝር ጥናቶች ላይ በመመርኮዝ መሠረታዊ የፖሊሲ ለውጥ ያደረገው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድም አዲስ የአፈፃፀም መመሪያ አፅድቋል። EBC የአፈፃፀም መመሪያውን ከላይ አያይዘናል፡፡ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት
ስልክ፡  +251115514005
ፋክስ፡  + 251115517699
P. O. Box 517,
ኢ.ሜይል: [email protected]
ድረ ገጽ: www.ethiopianchamber.com
ቴሌግራም      t.me/ethiopiachamber
ትዊተር         https://twitter.com/EthiopiaChamber
ፌስ ቡክ፡   https://www.facebook.com/EthiopianChamber
Youtube:https://www.youtube.com/channel/UCMEZ4TO8dQiIJvk2IQkTxhA
Linkedin(ሊንክዲን):https://www.linkedin.com/company/ethiopianchamber/in

Ethiopian exporters page/የ ኢትዮጵያ ላኪዎች

11 Apr, 15:40


እንደምን አመሻችሁ
ብዙ ፋብሪካዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ስራ ማቆም፣ ሰራተኛ መበተን እና እስከ መሸጥ እየደረሱ እንደሆነ እንሰማለን።
ማህበራችን ይህንን ችግር ለባለስልጣናት በማሳወቅ መፍትሄ ለማፈላለግ ለ ገቢዎች፣ ለጉምሩክ፣ ለኢንዱስትሪ ሚኒስትር እና ለገንዘብ ሚኒስትር ጥያቄያችንን በአካል ለማቅረብ ዝግጅት እያደረገ ነው።
መረጃ ይዘን ለመግባት እንዲመቸን ከላይ እና ከታች ያቀረብናቸውን መጠይቆች በመሙላት ተባበሩን።
ከኮሚቴው ጋር ችግራችንን ለማስረዳት አብራችሁን ለመሄድ የምትፈልጉ ካላችሁ ደውሉልን።
መልካም ምሽት!

1,141

subscribers

1,118

photos

9

videos