አንጾኪያ ሚድያ

@antsokia77


አንጾኪያ ሚድያ

23 Oct, 05:06


https://youtu.be/1nJs8LG-WAY?si=MFz72fJwvJndbRry

አንጾኪያ ሚድያ

22 Oct, 23:30


https://youtu.be/VgocIBeb9G8?si=_cMgweowibJu2Gti

አንጾኪያ ሚድያ

19 Oct, 15:59


https://youtu.be/JR0Lzrn66ms?si=OAZOXAjcoGwQHS7n

አንጾኪያ ሚድያ

19 Oct, 01:08


ህይወት አዙሪት ናት።ረጅም ርቀት የተጓዝክ ቢመስልህ የምትጨርሰው ከጀመርክበት ነው።ራቁትክን ትወለዳለህ እርቃንህን ወደ መቃብር ትወርዳለህ።በጥርስ ዐልባው ድድህ እየጋጥክ ትጀምራለህ ጥርሱን ባረገፈው ድድህ እያልጎጠጎጥክ ትጨርሳለህ።የህይወት ትግል እየዳህ ትጀምራለህ አጎንብሰህ ትጨርሳለህ።ዘመንም ተምኔታዊ ነው።መስከረም ጥቅምት ብሎ ያስጀምርህና መስከረም ብሎ ይመጣብሀል።ሰኞ ማክሰኞ ብለህ ተጉዘህ እንደገና ሰኞ ትላለህ።ሕይወት አዙሪት ናት!መጀመሪያህ መጨረሻህ ነው።የጀመርክበትን አትርሳ መጨረሻህ ነውና።የጀመርክበትን አትናቀው ትጨርስበታለህና።ተራ ሰው ሆነህ ትጀምራለህ ተምረህ እውቀት ብትጨምር ነግደህ ሀብት ብታገኝ ተሹመህ በህዝብ ላይ ብትሰለጥን ክቡረ ክቡራን ሆነህ የወርቅ ካባ ብትለብስ የምትጨርሰው እንደ ተራ ሰው አፈር ለብሰህ ነው።
ባለማወቅ ትጀምራለህ በመዘንጋት ትጨርሳለህ ዕውቀት አላመጣህምና ዕውቀትም ይዘህ አትሄድም።በለቅሶ ትጀምራለህ በጭንቅ ትጨርሳለህ።በሰው እቅፍ ትጀምራለህ በሰው ሸክም ትጨርሳለህ።
ገፅ 314_315
ከመርበብት
በዶ/ር አለማየሁ ዋሴ

አንጾኪያ ሚድያ

16 Oct, 15:11


https://youtu.be/ssO4YoTdCw0?si=PHqke7FsSAFZYx92

አንጾኪያ ሚድያ

14 Oct, 14:48


https://youtu.be/CmuG7NNGvvg?si=DlvD_rienJI779tW

አንጾኪያ ሚድያ

08 Oct, 11:56


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

“አሐቲ ድንግል”

በፈውስ መንፈሳዊ የዩቲዩብ ቻናል የህይወትን ቃል በሚመግቡን በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ ተጽፎ በ628 ገጾችና በ12 ምዕራፎች የተሰነደ
መጽሐፍ ነው፡፡

ከኅሊና አምላክ እስከ ዕርገቷ ድረስ ያለውን የእመቤታችንን ሙሉ የሕይወት ጉዞና በርካታ ምሥጢራት የያዘ ድንቅ መጽሐፍ ነው፡፡

እመቤታችን በነገረ ድኅነት ያላት ድርሻ ምን ይመስላል? ስለ እመቤታችን የሚነሡ ጥያቄዎች በመጽሐፍ ቅዱሳዊ የአበው ትምህርት እንዴት ተዳሰሰ? እንዴትስ በፍቅሯ ማደግና መጽናት ይቻላል? ሌሎችም መልሶችን የያዘው ይህ ግዙፍ መጽሐፍ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ጨምሮ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በተገኙበት የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 2/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7 ሰዓት ተኩል ጀምሮ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አዳራሽ ይመረቃል፡፡  ሁላችሁም እንድትገኙ በአክብሮት ተጠርታችኋል።

አንጾኪያ ሚድያ

07 Oct, 23:47


-ሲኖሩ በሰማዕትነት ሲሞቱ በታሪካዊነት፦
በምድር ላይ መኖር የምንችለው ባአጭር ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው።
ከሞት በኋላ ሁለተኛ ለብዙ ዘመናት መኖር የምንችለው ግን በመልካም ታሪካችን ነው።
ታሪክ የሠራ ሰው ዳግም በታሪክ ህልውና ውስጥ ሕያው ሁኖ ሲወሳ መኖር ይችላል።
ህያው አድራጊ ታሪክ ደግሞ ዝም ብሎ በስንፍና አይሠራም።
ራስን ሰጥቶ ሞትን ንቆ አጥቅቶ ነገን አልሞ በመሥራት ነው እንጂ።
ይልቁንም ትንሣኤ ሙታን ያለው ሰው ሁልጋዜም ታሪካዊ ሕያውነትን በህሊናው ማየት ግድ ይለዋል።
ስለሆነም ከሞት በኋላ በታሪክ ህልውና ውስጥ ለመኖር ምን እየሠራን ነው?
ወይስ አሁናዊ ብቻ ሁነን ለመቅረት ነው የምንፈልገው?
ክፉ ሰው ርኩስ መንፈስን አምኖ ምእመናንን ለማጥፋት ለክፉ ታሪክ ከተነሣ እኛ መንፈስ ቅዱስን አምነን ትናንትን ለትውልድ ለማስረከብ የነገ መልካም ታሪክን ለማንበር መነሣሣት ግድ ይለናል።
ምክንያቱም ዛሬ ባለችን በዓላማ በቁርጠኝነት ራሳችንን ሰጥተን ካልሠራን ለነገ ትውልድ ታሪክም ሃይማኖትም አይኖረንም።
በታሪክ ህልውና ውስጥ እንዳናይ የሚያደርገን ገርጋሪያችን ፍርሀት እና አስመሳይነት ነው።
ፈሪ ሰው ደግሞ የክርስቶስ መስቀሉን መሸከም አይችልም።
መስቀልን ያልተሸከመ ሰው ደግሞ መከራ አይንካኝ ሆዴ ይሙላ ደረቴ ይቅላ ሲል የሰማዕትነት ክብር ታመልጠዋለች።
ሲኖሩ በሰማዕትነት ሲሞቱ በታሪካዊነት ለመገለጽ ካሰቡ ፍርሀትን እና አድርባይነትን እንደ ሸረሪት ድር ገፎ መጣል ግድ ይላል።
መስሎ መኖር እና አድርባይነት ለስለላሳ ኑፋቄ ነው።
በምድር ላይ ማን ይፈራል? ሞትን እንዳንፈራው? ትንሣኤ ሙታን አለን።
አግባብስ ያለታሪክ ያለ ሃይማኖት እንዳይቀር የነገውን ትውልድ መፍራት ነው።
ለነገ አለማሰብ የነገውን ትውልድ በግልጽ መበደል ነውና።
ትናንትን እንደሚገባ ከአባቶቻችን እንደተቀበልነ ዛሬም በሰማዕትነት የተቀበልነውን አደራ እየጠበቅነ ለነገው ትውልድ የማስረከብ ሀላፊነት አለብን።
የነገ ታሪክ ሰነፎች ተቀምጠው ሳሉ እንደ ፈጣን ወፍ ማረፊያ አጥቶ በጊዜ ነፋስ ላይ በርሮ መሄዱ አይቀርም።
መሥራት ባይቻል እንኳን ለሚሠሩ ሰዎች እንቅፋት ላለመሆን መጣር ተገቢ ነው።
ከህሊናም ከታሪክም ጋራ መጣላት ትልቅ ድክመት ነው።
መሆን ያለብንን ሳንሆን መሆን ያለበት አይሆንም።

#መምህር ገብረ መድኅን እንየው

አንጾኪያ ሚድያ

07 Oct, 15:08


https://youtu.be/wyL-ztBQWdk?si=X--EvFfNt_O2b_D9

አንጾኪያ ሚድያ

06 Oct, 11:13


እግዚአብሔር ሁልጊዜ ወደ መከራ እንዳትገባ አያደርግም። አንዳንድ ጊዜ በወጀብ ውስጥ መንገድ ያዘጋጅልሃል። ግፊው በሚበዛበት ዐውሎ ነፋስ እያለፍህ ተፍገምግመህ እንዳትወድቅ ጉልበትህን ያጸናል፤ ኃይልን ያስታጥቅሃል። እንዲህ እያደረገ በመንፈስ ያጎለምስሃል።

እግዚአብሔር ዳንኤልን በአናባስት ጉድጓድ ከመጣል፣ ሠለስቱ ደቂቅን ወደ እቶን እሳት ከመግባት፣ ጳውሎስና ሲላስን ወደ ወኅኒ ከመውረድ ሊያድናቸው ይችል ነበር። ይሁን እንጂ እንዲህ አላደረገም። አምላካችን ፈተና ካለባቸው ቦታዎች ሁሉ ሊያወጣን ቃል አልገባምና። ነገር ግን በመከራ ጊዜያችን ሁሉ ከእኛ እንደማይለይና በእውነት ይዘነውም እንደ ሆነ በድል ነሺነት እናጠናቅቅ ዘንድ እንደሚረዳን ቃሉን ሰጥቶናል።

የጌታ እናት እመቤታችን የተወደደ ልጇን ይዛ በግብጽ በረሃ እንደ ወፍ ከተንከራተተች በኋላ ሕፃኑን የሚፈልገው ክፉ ሄሮድስ ሲሞት ተመልሳ ወደ ገሊላ ገብታለች። እንደ ድንግል ጌታን በመሐል እጅህ ብትታቀፍ እንኳን  ግብጽ መውረድ  አይቀርልህም። ይሁን እንጂ የመጣብህን መከራ ድል ነሥተህ ወደ ገሊላ መመለስህም እርግጥ ነው።

"ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል"
                              1ኛ ቆሮ 10፥13

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

አንጾኪያ ሚድያ

05 Oct, 14:46


http://youtube.com/post/UgkxHhgw15EG8XOI23K0s88rbak4acQDxu7N?si=vjptEVsyjQP3hvbW

አንጾኪያ ሚድያ

03 Oct, 15:20


https://youtu.be/oFnClBt3VXM?si=ugZ7YUor-yEm9CeI

አንጾኪያ ሚድያ

30 Sep, 15:45


https://youtu.be/FCSJGq47IC8?si=kk5c1R8pFIMsmmXZ

አንጾኪያ ሚድያ

30 Sep, 02:00


ድንግል ማርያም በድንጋይ ላይ ትገለጥልኝ ነበር እጅግ ግሩም ቆይታ #ከሰአሊ ቅዱስ ጋር


ዛሬ ምሽት 12:00 ላይ በአንጾኪያ ሚድያ ይጠብቁ


#አንጾኪያ ሚዲያ ሼር ሰብስክራይብ በማድረግ አገልግሎቱን ተደራሽ እናድርግ።

ወደ ቴሌግራም ግሩፓችን ሰዎችን አድ እናድርግ. https://t.me/antsokia77

https://youtube.com/@antiochmedia77?si=2VhwMdVZIA3ib1X3

አንጾኪያ ሚድያ

29 Sep, 14:51


የአማልክት ሌባ

በቅርብ ቀን ይጠብቁ


#አንጾኪያ ሚዲያ ሼር ሰብስክራይብ በማድረግ አገልግሎቱን ተደራሽ እናድርግ።

ወደ ቴሌግራም ግሩፓችን ሰዎችን አድ እናድርግ. https://t.me/antsokia77

https://youtube.com/@antiochmedia77?si=2VhwMdVZIA3ib1X3

አንጾኪያ ሚድያ

25 Sep, 14:15


ሲደርስ የገበሬዎቹ የነቢያት ጌታ ክርስቶስ ዘሩን እንዲሰበስቡና እንዲያከማቹ ሐዋርያቱን በእርሻ መካከል ይዟቸው ገብቷል /ማቴ.፲፪፥፩/፡፡ በአበው ፋንታ ውሉድን ለመተካት የመጣው መምህራችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢያትንና ሐዋርያትን በመስቀሉ አንድ ማኅበር አደረጋቸው፡፡ ሐዋርያው መስቀሉን ‹‹ገባሬ ሰላም›› በማለት ይጠራዋል /ኤፌ.፪፥፲፫/፡፡ ነቢያትንና ሐዋርያትን አንድ አድርጎ የእግዚአብሔርን መንግሥት ያወረሰ የክርስቶስ መስቀል ነውና፡፡

፪. ሙታንና ሕያዋን

አዳም በዕፀ በለስ ምክንያት የተሸከመው መስቀል ሞትን አምጥቶብናል፤ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ድኅነት ሲል የተሸከመው መስቀል ግን ሞትን ገድሎ ሕይወትን ሰጥቶናል፡፡ በዚህ ምክንያት የሞት መውጊያ ሲሰበር፣ የመቃብር ስቃይ ሲቋረጥ፣ የጨለማ ኀይል ሲሻር ከመስቀሉ ሥር ብዙ ሙታን እንደ አሸን ብቅ ብቅ አሉ፡፡ ምድር እስከዚያች ቀን ድረስ ሙታንን ትቀበል ነበር እንጂ ሕያዋንን ማስገኘት አትችልም ነበር፡፡ ሙታንና ሕያዋን የተፈላለጉበት መስቀል የመጀመሪያው ቀን ነው፡፡ በመስቀል ሙታን ሕያዋንን ፍለጋ ከመቃብር ወጥተው ወደ ከተማ ገቡ፡፡ ከታደለው የሕይወት ስጦታ የተነሣ ሞት አካባቢውን ለቆ ስለጠፋ በሩ እንደ ተከፈተለት እሥረኛ ሙታን ከመቃብር እየወጡ ከተማውን ሞልተውታል፡፡ ይህ ዕለት ሙታንን ከሕያዋን ጋር አፍ ለአፍ ያነጋገረ ዕለት ነው፡፡ ደመራው ሙታንን ከሕያዋን የሚለይ አይደለም፤ ታላቅነቱም እስከ ሲዖል ድረስ የሚታይ ነው፡፡

፫. ጻድቃንና ኀጥአን

የአዳም በደል በሕይወት የሚኖሩ ወንድማማቾችን በሁለት ሐሳብ ከፋፍሏቸው ነበር፡፡ የክርስቶስ የጽድቅ መስቀል ግን አንድ ሐሳብ ፈጠረላቸው፡፡ ጻድቁ አቤል ሳይበድል በደል የደረሰበት፣ ሳይገድል የተገደለ መኾኑ ከክርስቶስ ጋር ቢያመሳስለውም ሞቱ ግን ለሰው ልጆች ድኅነት አልጠቀመም፤ የፍጡር ደም ከእግዚአብሔር ጋር ሊያስታርቀን አይችልምና ኹላችንም በመከራ ውስጥ ለመቆየት ተገደናል፡፡ የክርስቶስ ሞት ግን የድኅነታችን መሠረት ኾነልን፡፡ በቤት ውስጥ የሚዘጋጅ መብራት ከፍ ብሎ ሲቀመጥ ኹሉን እንዲያሳይ ከምድር ከፍ ብሎ የተሰቀለው ክርስቶስም ጻድቃነ ብሊትንና ጻድቃነ ሐዲስን በዓይን እንዲተያዩ አድርጓቸዋል፡፡ በመስቀል ላይ የተፈጸመው ዕርቅ የኀጥአንን በደል ደምስሶላቸዋል፤ የጻድቃንን ጽድቅ አረጋግጦላቸዋል፡፡ ጻድቃንም ኀጥአንም አንድ ኾነው መንግሥቱን በጸጋው ወረሱ፡፡ ኢያሱ በኢያሪኮ እንዳደረገው አሞራውያን ወጥተው እስራኤል ብቻ ምድሪቱን የወረሷት አይደሉም፡፡ መስቀሉ ለኹሉም አንድ መንግሥትን አውርሷቸዋል፤ ጊዜው የደመራ ነውና፡፡ በምድር ደምቆ የታየው ይህ ደመራ እስከ መንግሥተ ሰማያት ድረስም ይቀጥላል፡፡

ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ

አንጾኪያ ሚድያ

25 Sep, 14:15


++ የደመራው ምሥጢር ++

እግዚአብሔር አምላካችን የሠራቸው ታላላቅ ሥራዎች በምልክት የተገለጡ ናቸው፤ ለምሳሌ የሙሴ መስፍንነት፣ የአሮን ሊቀ ካህንነት የተረጋገጠው በአሮን በትር ምልክትነት ነው፡፡ አብርሃም ልጁ ይስሐቅን ሊሠዋ በታዘዘ ጊዜ የሞርያን ተራራ የመረጠው እግዚአብሔር በተራራው ላይ ካሳየው ብርሃን የተነሣ ነው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምና ቅዱስ መስቀልም የድኅነታችን ምልክቶች ናቸው፡፡ የአሮንና የሙሴ በትሮች፣ የይስሐቅ ቤዛ የሚኾን በግ የተገኘባት ዕፀ ሳቤቅ ደግሞ የእመቤታችንና የመስቀል ምልክቶች ነበሩ፡፡ ወደ ፊት የምንወርሰው መንግሥተ ሰማያት ክርስቶስ ነው፤ እርሱን ደግሞ ያገኘነው ከመስቀል ላይ ነው፡፡

ጥንተ ጠላት ሰይጣን ይህንን ስለሚያውቅ ቅዱስ መስቀሉን አጥብቆ ይቃወመዋል፤ ስለዚህም አይሁድን አነሳሥቶ ከ፫፻ ዓመታት በላይ ተቀብሮ እንዲቆይ አድርጓል፡፡ በመሠረቱ ለሰይጣን ምሥጢሩ ስለማይገባው ነው እንጂ የመስቀሉ ትክክለኛ መቀበሪያ ሥፍራ የምእመናን ልቡና ነው፡፡ ቀራንዮ ለመስቀሉ መትከያነት የተመረጠችውም ቀዳሜ ፍጥረት አዳም የተቀበረው በዚያ ስለ ነበረ ነው፡፡ ቦታው ‹‹የራስ ቅል ሥፍራ›› /ማቴ.፳፯፥፴፪/ መባሉም የኹላችን ራስ አዳም ዓፅሙ በዚያ ስላረፈ ነው፡፡ መስቀሉ በአዳማውያን ፍጥረታት አእምሮ ውስጥ እንጂ ከዚያ ውጪ የሚኖር ባለመኾኑ ተቀብሮ በቆየባቸው ዓመታት ውስጥም ፍቅሩ ከሰው ልጆች ልቡና አልወጣም፡፡

ጠላት በሠራው ተንኮል ተቀብሮ እንዳይቀር መስቀሉን እንድታወጣ መንፈስ ቅዱስ ንግሥት ዕሌኒን አስነሣት፡፡ ይህች ሴት ቤቷ በሀብት፣ በንብረት ሞልቶ በነበረበት ጊዜና በገረድ፣ በደንገጡር በምትንቀሳቀስበት ወቅት ምን እንደ ሠራች አልተመዘገበላትም ነበር፤ ከክብሯ ወርዳ በተጣለችበት ጊዜ ግን እግዚአብሔር ለሚፈልገው ሥራ ምቹ ኾና ተገኘች፡፡ እርሷ በተጣለችበት ባዕድ አገር ውስጥ ኾና የመስቀሉን ነገር ታስብ፤ ብርሃነ መስቀሉም ዘወትር በልቧ ያንጸባርቅ ነበር፡፡ ሐሳቧን እንዲያሳካላት የለመነችው አምላክም ኪራኮስ የተባለውን አይሁዳዊ ሽማግሌ ልኮ አቅጣጫውን አመላከታት፤ ኪራኮስ የጀመረውን ምሥጢርም መልአኩ ‹‹ደመራ ደምረሽ፣ ሰንድሮስ የሚባል ነጭ ዕጣን ጨምረሽ አቃጥዪው›› ብሎ ተረጐመላት፡፡ እርሷም መልአኩ እንደ ነገራት ብታደርግ ጢሱ ሰማይ ደርሶ ወደ ምድር ተመልሶ መስቀሉ ወደሚገኝበት ተራራ ሰገደ፡፡ በጢሱ ምልክትነት መስከረም ፲፯ ቀን የተጀመረው ቍፋሮ መጋቢት ፲ ቀን አልቆ ዕሌኒ መስቀሉን ከልበ ምድር ለማውጣት ችላለች፡፡

መስቀልና ደመራ እንዲህ ነበር የተገናኙት፡፡ ደመራው ለመስቀሉ መገኘት፣ መስቀሉም ለደመራው መሠራት ምክንያት ናቸው፡፡ በዚህ አንጻር መለኮትና ትስብእት በአንድነት መደመራቸው መስቀሉ እንዲሠራ ምክንያት ኾነዋል፡፡ አምላካችን ሥጋ ለብሶ ‹ክርስቶስ› በሚል የተዋሕዶ ስም ሲጠራ ለመከራ መዘጋጀቱን እንረዳለን፡፡ መስቀሉ የሥጋ ብቻ ነበረ፤ አሁን ግን መለኮትም በሥጋ ባሕርይ የመስቀሉ ተካፋይ ኾነ፡፡ ይህም የደመራው ውጤት ነው፡፡ መለኮት አምስት ሺሕ ከአምስት መቶ ዘመን መስቀል የተሸከመ ሥጋን ሲዋሐድ መስቀሉን አስወግዶ አልነበረም፡፡ ይኸው በዕፀ በለስ ምክንያት የተሸከምነው መስቀል ነው፡፡ ሥጋ ዓቅም አጥቶ መስቀሉን ከትከሻው ላይ ሳያወርድ ለዘመናት የተጓዘውን ጕዞ መለኮት ኀይል ኾኖት ድካሙን ሳይለቅ ኀያል፤ ኀይሉን ሳይለቅ ደካማ ኾነ፡፡ መስቀል ትርጕሙ መከራ ቢኾነም ነገር ግን እግዚአብሔር ሲያመጣውና ሰው ሲያመጣው ግን ትርጕሙ ይለያያል፤ ሰው ያመጣው መስቀል ኹላችንን ለመከራ፣ ለሞት አሳልፎ ሰጥቶናል፡፡ የእግዚአብሔር መስቀል ግን መከራነቱ ለሰይጣን እንጂ ለእኛ ሕይወታችን ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድም ‹‹መስቀል ብሂል ዕፀ ሕይወት ብሂል፤ መስቀል ማለት የሕይወት ዛፍ ማለት ነው›› በማለት የመስቀልን ትርጕም ነግሮናል፡፡

አዳም ከገነት ሲወጣ በመላእክት እንዲጠበቅ የተደረገው የሕይወት ዛፍ የክርስቶስ መስቀል ነው፡፡ በዕፀ በለስ ምክንያት ኹላችንም እንደ ተጎዳን በዕፀ ሕይወቱም ተጠቃሚዎች ኾነናል፤ አስቀድመን በአዳም መከራ እንደ ተባበርን አሁን ደግሞ በደስታው እንተባበራለን፡፡ ሞትም ሕይወትም አንድ አድርጎናል፡፡ የክርስቶስ መስቀል ኹሉንም በሕይወት አስተባብሯልና፡፡ በአንጻሩ ሰውና ዲያብሎስን ለያይቷል፡፡ የኀጢአት ቁራኝነትን አጥፍቷል፡፡ ጌታችን በማኅፀን ሲፀነስ ጀምሮ የእኛን መስቀል መሸከም ሲጀምር የእርሱ የኾነውን ለእኛ ስለ ሰጠን ከሰይጣን ጋር መለያየታችን በመስቀሉ ተረጋግጧል፡፡ የአምላካችን መስቀል ምልክቱ ደመራ መኾኑ የእኛን ወደ እርሱ መሰብሰብና የጠላታችንን መበተን የሚያረግጥልን ነው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወብየ ካልዓትኒ አባግዕ እለ ኢኮና እምዝንቱ ዐፀድ ወኪያሆንሂ ሀለወኒ አምጽኦን ዝየ፤ ከዚህ በረት ያልኾኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱንም ላመጣቸው ይገባኛል›› በማለት ሊሰበስበን እንደ መጣ ነግሮናል /ዮሐ.፲፥፲፮/፡፡ መስቀሉ ፍጥረት አንድ ደመራ ኾኖ የተሠራበት ስለ ኾነ በደመራ እንዲገለጥ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ኾነ፡፡

መስቀሉ አንድ ደመራ ያደረጋቸው ፍጥረታት

፩. ነቢያትና ሐዋርያት

ነቢያት የሚባሉት ከአዳም እስከ ዮሐንስ መጥምቅ ያሉ አባቶች ሲኾኑ፣ ከክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ጀምሮ ለቤተ ክርስቲያን የወንጌልን የምሥራች እንዲነግሩ የተላኩ አባቶች ደግሞ ሐዋርያት ይባላሉ፡፡ በእርግጥ ሐዋርያ የኾነ ነቢይ የለም እንጂ ነቢይ የኾነ ሐዋርያ አለ፡፡ ነቢያትና ሐዋርያት በዘመን፣ በክብር እና በግብር የማይገናኙ ፍጥረታት ናቸው፡፡ መንፈሰ ረድኤት የተሰጣቸው ነቢያት ለሐዋርያት የተሰጠውን መንፈሰ ልደት ለማግኘት አልተቻላቸውም፡፡ ሐዋርያት ግን ኹሉንም አንድ አድርገው ይዘዋል፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው ስለዚህ ሲመሰክር ‹‹በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጠን›› በማለት አጕልቶ የተናገረው /ዮሐ.፲፥፲፰/፡፡ ነቢያት በዚህ ምድር የእግዚአብሔርን መንግሥት በመፈለግ ብዙ ደክመዋል፡፡

ሊቃውንቱ ነቢያትን በክረምት፣ ሐዋርያትን በበጋ ገበሬ ይመስሏቸዋል፡፡ የክረምት ገበሬ ላዩ ውሃ፣ ታቹ ውሃ ኾኖበት በጭቃ ወጥቶ በጭቃ ይመለሳል፡፡ ወደ ቤቱ ሲገባም ሚስቱ ጨምቃ ያቆየችለትን ጐመን በልቶ ደስ ሳይለው ይተኛል፡፡ ነቢያትም በዚህ ዓለም በጣዖት አምላኪ ነገሥታት፣ በነቢያተ ሐሰት ስብከት ሲንገላቱ ኖረው ሲሞቱም ሲዖል ይገባሉ እንጂ ገነትን አይወርሱም ነበር፡፡ የበጋ ገበሬ በደረቅ ወጥቶ፣ እሸት በልቶ፣ ተደስቶ ወደ ቤቱ ይመለሳል፤ ከቤቱ ሲገባም እንጀራው በሌማት፣ ጠላው በማቶት፣ ሲቀርብለት ደስ ብሎት ይበላል፤ ይጠጣል፡፡ ሐዋርያትም ልጅነትን አግኝተው ለማስተማር ተልከዋል፤ በሔዱበት ኹሉ ተአምራትን እንዲያደርጉ፣ ልጅነትንም እንዲሰጡ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል፡፡ ሞታቸው ሲደርስም መንግሥተ ሰማያት ተከፍቶ ይጠብቃቸዋል፡፡

ቅዱስ ያሬድም ‹‹ኖትያት ነቢያት ራግናት ሐዋርያት›› በማለት ነቢያትን በዋናተኛ፣ ሐዋርያትን በጀልባ ቀዛፊ መስሎ ይናገራል፡፡ ከቀዛፊዎች ይልቅ ዋናተኞች ይደክማሉ፡፡ ዋናተኞች ውሃው አጥልቋቸው፣ መተንፈስ ተስኗቸው አንዳንዶቹ ከዳር ይደርሳሉ፤ አንዳንዶቹም በድካም በውሃ ውስጥ ሰጥመው ይቀራሉ፡፡ ቀዛፊዎች ግን ምናልባት ሞገድና ማዕበል ካላሰጋቸው በስተቀር ይህ ኹሉ ውጣ ውረድ የለባቸውም፤ በጀልባዋ የተመሰለችው ቤተ ክርስቲያን ለነቢያት በተስፋ እንጂ በአካላ አልተሰጠችም፡፡ ነቢያት ከእርሷ ሳይደርሱ ሞት ቀድሟቸዋል፡፡ ሐዋርያትም በነቢያት ድካም ገብተው ነቢያት የዘሩትን የትንቢት ዘር አጭደዋል፡፡ ወንጌል የነቢያት ዘር ናት፤ ዳሩ ግን ፍሬውን ለመብላት የታደሉት ሐዋርያት ናቸው፡፡ እሸቱ

አንጾኪያ ሚድያ

22 Sep, 05:47


እንኳን ለሊቀ መላእኩ ቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ የመላእኩ ጥበቃ አይለየን።

         "የሰንበትን ቀን ትቀድሱ ዘንድ አስብ"
             ዘጸአት 20:8

" መልካም እለተ ሰንበት"

1,541

subscribers

11

photos

13

videos