✍️ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል፣
✍️ በአደጋው በ7 ሰዎች ቀላል፤ በ2 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፣
ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓም ምሽት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሸማ ተራ ነባር የገበያ ማዕከልና በአካባቢው በአጋጠመ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።የአደጋውን መንስኤ የሚያጣራ የፎረንሲክ ምርመራ ቡድን በማቀናጀት ምርመራ መጀመሩን ፖሊስ አስታውቋል።
አደጋውን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራና ከአደጋው ጋር በተያያዘ በ7 ሰዎች ቀላል በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታውቋል፡፡አደጋውን ለመከለከል የፀጥታ ተቋማትና የአካባቢው ህብረተሰብ ላደረገው ድጋፍ የአዲስ አበባ ፖሊስ አመስግኗል።
@Tikfahethiopia