Latest Posts from ማር ይስሐቅ (@mar_yisihak) on Telegram

ማር ይስሐቅ Telegram Posts

ማር ይስሐቅ
" መንፈስ ግን በግልጥ.....አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንትን ትምህርት እያደመጡ ሃይማኖትን ይክዳሉ ይላል'' 1ኛ ጢሞ 4÷1 ስለዚህ እንንቃ!!!
2,409 Subscribers
604 Photos
9 Videos
Last Updated 13.03.2025 06:41

Similar Channels

Esdros S.C
3,004 Subscribers
sewaseweth.com
2,220 Subscribers

The latest content shared by ማር ይስሐቅ on Telegram

ማር ይስሐቅ

10 Mar, 10:04

200

ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦

👉 “ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ።”
ማቴዎስ 9፥15

👉 “ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ወራትም ይጦማሉ።”
ማርቆስ 2፥20

👉 “ነገር ግን ወራት ይመጣል፥ ሙሽራውም ከእነርሱ ሲወሰድ ያንጊዜ፥ በዚያ ወራት ይጦማሉ አላቸው።”
ሉቃስ 5፥35

@Mar_Yisihak
ማር ይስሐቅ

03 Mar, 19:57

511

አሁን ጴንጤ ሆኛለሁ
   [ይህን ትምህርታዊ ጽሑፍ እባክዎ ሼር ያድርጉት]

አሁን መስቀል አልስምም!! ነው ምላቸው?? ወይስ ሳያሳልሙኝ ለመጨበጥ እጄን ልዘርጋ??

አመጣጣቸው አይተውኝ እንደሆን ያስታውቃል።የእናቴ ንሰሐ አባት ናቸው። ሁሌ ጠበል ሊረጩ ሲመጡ እኔ ጋ ና እያሉኝ ብዙ ጊዜ ጠፍቻለሁ።ዛሬ ደሞ ጭራሽ ጴንጤ ሆኜ ነው መንገድ ላይ የተገጣጠምነው። እንኳን ቄሱ እናቴም ካኮረፈችኝ ሰነበተች...

ልጅ ሀይለ ሚካኤል እንዴት ሰነበትክ ጎረምሳዬ..(ፎቅ የሚያህል ጥምጣማቸውን ጠምጥመው ወደ ቆምኩበት መስቀላቸውን ለማውጣት እየታገሉ መጡ

ጌታ ይመስገን አባ.. ስሙ ይክበር..አልኳቸው ድምፄን ጎርነን ፊቴን ኮስተር አድርጌ ምናልባት ሁኔታዬ ከገባቸው ብዬ ነበር...

ዛሬ ደሞ አትሳለምም እንዴ?? አሉ መስቀላቸውን አዘጋጅተው እንደቆሙ

አይ አባቴ ጴንጤ ሆንኩኝ እኮ...ጴንጤ....(ጭቅጭቃቸውን እያሰብኩት ተንተባተብኩ

ጎሽሽሽሽ የኔ ልጅ!!! ጎሽ.. ጎሽ... ጎሽ..ደግ አደረክ!! ተባረክየኔ አምበሳ ጎበዝ!!( ብለው ብቻ ፈገግ እያሉ መስቀላቸውን ወደ ካፖርታቸው መልሰው ጥለውኝ ሄዱ።የሠማሁት ነገር ግን ከአባ መሆኑ አጠራጠረኝ።እኔ ገና ለገና ተከራከሩኝ ለምን? እንዴት? እያሉ ዘበዘቡኝ ስል እሳቸው ጭራሽ ጎሽ???

ግራ ገባኝ። አባን ሳውቃቸው ትጉህ አገልጋይ የመንጋ ጠባቂ እንደሆኑ ነው፡፡ እንዲያውም እኔ ወደ ቤተክርስትያን እንድቀርብ.... (ተብከነከንኩ!!) ቆይ አታስፈልግም እያሉ ነው?? ብትኖርም አትጠቅምም ነው?? ንቀውኝ ነው?? በቆምኩበት መንገዱን ተሻግረው ወደ ቤተክርስትያን ሲሄዱ ንዴት እያጦዘኝ ተከተልኳቸው.....

ምን ማለትዎ ነው አባ?? ጴንጤ ሆንኩ እኮ ነው ያልኩት!! ወይስ መጀመርያም አላስፈልግም ነበር....(አባ በሩ ላይ እንደደረሱ አማትበው ሲያበቁ ዞር ብለው አይተውኝ ወደ ግቢው ዘለቁ። አረ....መናናቅ!!!ገነፈልኩኝ።

ያናግሩኝ እንጂ!!! ለምን መልስ አይሰጡኝም!! ወይስ እርሶም ሊሆኑ አስበዋል?? ነገሩ...(የጀማሪ ነገር እንዳይሆንብኝ ወሬዬን ገታ አድርጌ አየኋቸው፡፡እሳቸው ግን ጭራሽ ችግኝ እና ዶማ ይዘው መጥተው

ይልቅ ከመጣህ አይቀር እቺን ትከልልኝ አሉ በልምምጥ ድምፅ(ሳላንገራግር ቆፈር ቆፈር አድርጌ የሰጡኝን ችግኝ ተክዬ ሳበቃ አባ በተራቸው መጥተው የተከልኩትን መልሰው ይነቅሉት ጀመር....

እንዴዴ ምነው እርሶ!? በማስተማር ፈንታ ፀብ ፀብ አልዎትሳ???

አይ እንግዴ!! ታድያ ተክለከው መች በቀለ???

መች ስር ሰደደና???አሁን ተክሎ አሁን ይበቅላል????

ጎሽ ጎበዝ...እንግዲህ መልሴ ይሄ ነው፡፡ተተክሎ ያልቆየ ያልተኮተኮተ ወይ ስር ያልሰደደ ተክል አይፀድቅም!!ይህ ችግኝ ማለት ደሞ አንተ ነህ።ተምረህ እንድታውቅ አውቀህ እንድትኖር ብዙ ብለምነህ እምቢ ብለህ የቆየከው አንተ!!ዛሬ ደሞ ወጣሁ ሄድኩ ከቤተክርስትያን ልጅነት አፀድነት ተነቀልኩ ትላለህ....አብ የተከለውማ አይነቀልም....

አየህ ሀይማኖት መቀየርህን ሳይውል ሳያድር ነበር ከናትህ የሠማሁት። ለዚህ ነው አንተ ስትነግረኝ እንግዳ ያልሆንኩት፡፡ ነገር ግን ፍፁም አዝኛለሁ፡፡ በሰአቱ መንገድ ዳር "እንዴት ሀይማኖት ቀየርክ" ብዬ ብሰድብህ ከመቅረብ ይልቅ ትሸሸኛለህ። በተቃራኒው ግን ደግ አደረክ ብልህ ከኔ የማትጠብቀው አነጋገር በመሆኑ አጥብቀህ ትጠይቃለህ። ባትመጣ እንኳ እኔ መመለሴ አይቀርም ነበር።ብዙ ምእመናንኮ የጠፉብን አቅርበን ከማስተማር ገፍተን ሰድበን በማስወጣታችን ጭምር ነው...

ይልቅ እንደዚህ ችግኝ አትሁን። አለባብሰው ቢተክሉህ ያፀደቁህ እየመሠለህ ሽው ባለ ነፋስ አትንገዳገድ፡፡ ስር ያልሰደደ እውቀት የመሀይም መጫወቻ ያደርጋልና ተጠንቀቅ። ተዋህዶን እንኳ አውቀሀት አይተሀት አትጨርሳትም "ሮጦ መውጣት ለእንቅፋት" እንዲሉ ሰክኖ መርጋት ከድንገተኛ ሞት ያድናል። ቤት ውስጥ ያሉትን መ**** ቅ በማለት ውጪ ያሉትን በማቃለል ሀይማኖታቸውን በማንቋሸሽ ሀይማኖት አትፀናም.. እንዲያውም ቤተክርስትያን አክብሮ መጥራት እንጂ ሰድቦ ማባረርን አታስተምርም ።አንተም ያልተማርክበት ቦታ ብትሔድ በጥባጭ እንጂ አማኝ አትሆንም።

እንግዲህ ያላወቅከው እንዲገባህ ያወቅከው እንዲያፀናህ እኔም ለመጠየቅ ዝግጁ ነኝና ጠዋት እዚሁ ና...ጠፍቶ ከመቅረት ወጥቶ መመለስ ይሻላል። አሁን ግን ግባና እረፍት አድርግ ከቅድሙ ይልቅ አሁን ኮርቼብሀለው... (ብለው ዶማቸውን ሰብስበው ወደቤታቸው ተመለሱ....
መች ነው ነግቶ እንደገና ማወራቸው??? እያልኩ ወደቤቴ ገባሁ።

ጸሐፊው ቻቻ ነው።

© አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

@Mar_Yisihak
ማር ይስሐቅ

27 Feb, 06:43

659

በጾማችን የነፍሳችንን ክፉ ልማዶች ካላስወገድን ከሥጋ መከልከላችን ብቻውን ምን ይጠቅመናል?

ስንጾም ውለን ጾም ከመግባቱ በፊት እንመገበው የነበረውን ምግብ ለውጠን መናኛ የሆነ የጾም ምግብ በማዕዳችን አቀረብን፡ ሆኖም ግን በጾም የምንመገበውን ምግብ እንደ ለወጥን ሁሉ ክፉ ሥራችንን እና ሕይወታችንንስ አብረን ለውጠናል ይሆን?

በእውነት እኔ ግን እንዲህ ያደረጋችሁ አልመሰለኝም፡፡
እንዲህ ከሆነ መጾማችሁ ጥቅሙ ምንድን ነው?

ስለዚህ ከጾማችሁ ጋር ልማዳችሁንና ሕይወታችሁን ወደ መልካምነት ትቀይሩ ዘንድ በተከታታይ እንድታስቡበት አደርጋችሁ ዘንድ ስለዚህ ነገር እናንተን ማስተማርንና መገሠጽን አላቋርጥም፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት 4 ቁ 12

@Mar_Yisihak
ማር ይስሐቅ

24 Feb, 06:01

654

✍️ ጉዞ ወደ ምሁር ኢየሱስ ገዳም ✍️

🗓 መነሻ ቀን :- መጋቢት 13 2017 ዓ.ም (ቅዳሜ)

🕰 መነሻ ሰዓት:- ከንጋቱ 11:30

📍 መነሻ ቦታ:- ብሥራተ ገብርኤል ቤተክርስቲያን

🗓 መመለሻ ቀን  :- መጋቢት 14 2017 ዓ.ም

🏦 ዋጋ መስተንግዶን ጨምሮ : - 1,500 ብር ብቻ

⚡️ ሰዓት ይከበር!
ማር ይስሐቅ

12 Feb, 06:23

1,036

እኔ ከሌለው አገልግሎቱ አይደምቅም ለሚል አገልጋይ እነሆ.......

ይተካል እግዚአብሔር አገልጋይ ለቤቱ
ከዛሬው የሚልቅ የማይዝል ጉልበቱ
አይሰስትምና ጸጋን በማካፈል
ብርቱውን ያስነሳል ከትውልዱ መሃል

የሙሴ በረከት ደርሶዋል ለኢያሱ
አምላክ በቃ ብሎ ሊጠራው ወደርሱ
ኢያሱን አቆመው በበረታ ጸጋ
የነገሥታት ንጉሥ አልፋና ኦሜጋ

መጎናጸፊያውን ለኤልሳ ትቶለት
ኤሊያስ ቢሄድም ቢነጠቅ በእሳት
እጥፍ ድርብ ጸጋ ከሁሉ የሚልቅ
አምላክ ስለሰጠው ፈጽሟል ድንቃድንቅ

ከእኔ ብቻ በቀር ማነው ያለው ሌላ?
ትጉን ለአገልግሎት ዝናሩ ያልላላ?
እንዲህ አትበሉ እግዚአብሔር ዘገየ
ይሾማል ለቤቱ ጠላት ዓይኑ እያየ

ቀድሰን ዘምረን ወንጌሉን መስክረን
ወደ ሰማዩ ቤት ደሞ እንሄዳለን
እግዚአብሔር ያስነሣል ዳግም እንደገና
ዘመኑ የዋጀ እጅጉን የጸና

@Mar_Yisihak
ማር ይስሐቅ

30 Jan, 05:17

737

✞ የጋለ ብረትን ለመቀጥቀጥ የሚነሣ ሰው አስቀድሞ
በብረቱ ምን ለመሥራት እንዳሰበ መወሰን አለበት
መጥረቢያ
ሰይፍ
ወይስ ማጭድ?

እኛም በምን ዓይነት የሕይወት መስመር ፍሬ ለማፍራት እንዳሰብን አስቀድመን ልቡናችንን ማዘጋጀት አለብን፡፡

@Mar_Yisihak
ማር ይስሐቅ

17 Jan, 20:10

1,016

#ከተራ

#ከተራ ምን ማለት ነው?

ከተራ 'ከበበ' ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡
ትርጓሜውም ውኃ መገደብ ማለት ነው፡፡

በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር በየአጥቢያው የሚገኙ ሰዎች ተሰብስበው በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ይጥላሉ፡፡

በጥር 11 ለሚኖረውም የጥምቀት ሥነ-ስርዓት ጉድጓድ እየቆፈሩ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡

በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማኅሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።

በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በዋዜማው የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡

ታቦቱ የጌታችን ምሳሌ ናቸው።

ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡

መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡

መልካም በዓል!
@Mar_Yisihak
ማር ይስሐቅ

04 Jan, 11:48

1,013

🎁 🎁 🎁  የገና አባት 🎁 🎁 🎁

ለኦርቶዶክሳዊ ሰው ቅዱሳንን መምሰል ክርስቶስ ጋር ለመድረስ መንገዱ ነው።

እንግዲያውስ በዚህ የልደት በዓል የመስጠት አባት የሆነ የገና አባትን (ቅዱስ ኒቆላዎስን) በተግባር እንምሰለው፡፡

ቅዱሱ በድሆች መንደር ምጽዋትን እንደሰጠ እኛም ለበዓለ ልደት የተቸገሩትን በመርዳት፣ ለወዳድ ዘመዶቻችን የምሥራችን በማሰማት..... እናክብር።

በቃል የገና አባት ከማለት ባለፈ እንደ የገና አባት (ቅዱስ ኒቆላዎስ) በስጦታ የገና አባትን እንምሰል፡፡

@Mar_Yisihak
ማር ይስሐቅ

28 Dec, 07:20

1,109

እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሰን!

አናንያን፣ አዛርያን፣ ሚሳኤልን እንዲሁም ዳንኤልን የረዳ መልአክ እኛንም ይርዳን፣ ይባርከን፣ ከኃጢአት በቀር የልቦናችንን ፍላጎት ይፈጽምልን!

“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።”

መዝሙር 34፥7

@Mar_Yisihak
ማር ይስሐቅ

25 Nov, 03:13

1,297

ቅዱስ ሚናስ (ማር ሚና) በምድረ ግብጽ ተወዳጅ ከሆኑ ሰማዕታት ዋነኛው ነው። በግብጻውያን ልዩ ቦታ አለው ማር ሚናስን ጠርተው አይጠግቡትም። ምክንያቱም ከታላላቅ ሰማዕታት አንዱ በመሆኑና ዛሬም ድረስ ለጆሮና ለዐይን ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ስለሚሠራ ነው። በተለይ ለታመመ ለደከመና ለተጨነቀ ፈጥኖ ደራሽ ባለ በጎ መድኃኒት ፈዋሽና አማላጅ ነው።

ቅዱስ ሚናስ ትርጉሙ ታማኝና ቡሩክ ማለት ነው። በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ የደጋግ ክርስቲያኖች ልጅ፣ በልጅነቱ የቅድስና ሕይወትን ያጣጣመ፣ በዘመኑ ሰው እጅግ ተወዳጅ የነበረ፣ ሃብትን ክብርን ሥልጣንን ንቆ በጾምና በጸሎት የተወሰነ፣ በመጨረሻም በክርስቶስ ስላመነ በአላውያን ከብዙ መከራና ስቃይ በኋላ ኅዳር 15 በሰማዕትነት ያረፈበት ሲሆን ሰኔ 15 ደግሞ ቤተ ክርስቲያኑ መርዩጥ በተባለ አገር የከበረችበት ነው።

#በአንድ_ወቅት፦
ዐሥራ ስምንት ቀሳውስት በሥራ ጉዳይ አቡነ ቄርሎስ ፮ኛን ለማነጋገር መርዩጥ ወደ ሚገኘው የቅዱስ ሚናስ ገዳም ጉዞ ጀመሩ። ቀሳውስቱ በጉዞአቸው መንገድ ስተው ሲባዝኑ ከአንድ የበረሓ ሰው ጋር ተገናኙ።

የበረሓው ሰው መርዩጥ የሚገኘው የቅዱስ ሚናስ ገዳም ለመሄድ መንገድ እንደሳቱ ቀድሞ ተረድቶ ነበርና "የማር ሚናስን ገዳም ነው የምትፈልጉት? በማለት ይጠይቃቸዋል። እነርሱም ችግራቸውን እንዴት እንዳወቀ በልባቸው እያደነቁ "አዎን" አሉት። የበረሓው ሰውም እየመራ ከገዳሙ አደረሳቸው አቡነ ቄርሎስ ፮ኛም ወደ በር ወጥተው ተቀበሏቸው።

ከዚያም "ምነው ዘገያችሁ? መንገድ ሳታችሁ እንዴ?" ብለው እንደ ቀልድ ጠየቋቸው። እነርሱም "አዎን! በጣም ተቸግረን ሳለን ይህ የበረሓ ሰው ደርሶልን መንገዱን አሳየን" ብለው ወደ ሰውየው ለማመልከት ዘወር ሲሉ እርሱ በአካባቢው የለም። አቡነ ቄርሎስም "መንገድ እንደጠፋችሁ ስለተረዳሁ ሚናስን ልኬላችሁ ይዟችሁ የመጣው እርሱ ነው" አሏቸው።

አምላካችን ከቅዱሱ ሰማዕት በረከትን ይክፈለን!!

@Mar_Yisihak