Dernières publications de ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (@maedotzeorthodox) sur Telegram

Publications du canal ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ይህ ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የተሰኘ የቴሌግራም ስብስባችን ነው::
• በእርጅናና በተለያየ ምክንያት ጤናቸው የተጓደለና በየመቃብር ቤቱ የወደቁ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ለመንከባከብ
• የአብነት ትምህርት መምህራንን: ተማሪዎችን ለመርዳት እንዲሁም የትናንቱን ለነገ ለማስቀጠል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ልጆች የሚመክሩበት የቻናል ገፅ ነው::
31,001 abonnés
493 photos
5 vidéos
Dernière mise à jour 27.02.2025 22:38

Canaux similaires

Faking Space
15,322 abonnés

Le dernier contenu partagé par ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ sur Telegram


✍️✍️✍️

❝አትገረምም!❞
*********

አየህ አገልግሎት ገደብ የለውም! ዕድሜ፣ ቦታ፣ ስራ፣ ትዳር፣ ሁኔታ፣ ሌላውም ምክንያት አይገድበውም። ይህን መልዕክት የምትመለከተው ወንድሜ ሆይ ያኔ በልጅነት ሰንበት ትምህርት ቤት ያሳለፍከውን ጊዜ አስብ፤ መልዕክቱን የምታነቢውም እህቴ፣ ያን የማይረሳ የአገልግሎት ዘመን አስቢው! ዝማሬ ለመቆም፣ መዝሙር ለማጥናት፣ ያሬዳዊ ዝማሬን አጥንቶ ለማቅረብ፣ ድራማ እና ጭውውት ለመስራት፣ አልባሳት ለብሶ ለመዘመር፣ በየበዓላቱ በአልባሳት ደምቆ ቄጤማ እና ዘንባባ ይዞ በየከተማው እየዘመሩ ለመሄድ፣ በየወርሃዊ የዝክር መርሐግብሮች ላይ ጸበል ጸድቅ ለመቃመስ፣ በየልቅሶው ቤት አጽናኝኝ እመአምላክ እያሉ እየዘመሩ ሐዘንተኞችን ለማጽናናት፣ የታመሙትን ድውይ ነኝ አንተ አድነኝ እያሉ እየዘመሩ በሽተኞች በሽታቸውን እንዲረሱ ለማድረግ፣ በየሰርጉ ላይ መርአዊ ሰማያዊ እያሉ ለማጀብ፣ በየንግሱ ታቦታቱን በአልባሳት አሸብርቆ ለማጀብ ያለህን ፍቅር እና ፍላት ቅናት እና መነሳሳት አስበው ወንድሜ። እስኪ ትዝ ይበልሽ እህቴ!

ዛሬስ? ዛሬማ ትልቅ ሆንና! መንግስት ሰራተኞች ደመወዝተኞ ሆንና! ዛሬማ ጊዜ የለንማ፣ ትላልቆች ሆነን አግብተን ወልደን ከበድና፣ ዛሬማ ዕድሜያችን ገፍቶ አልባሳት ለብሶ ማገልገል ያሳፍረናላ፣ ጡረታ ወጣና! ያሳዝናል።

ግን የቤተክርስቲያን ፍቅር እና አገልግሎት በእውቀት ለገባው ምንም ነገር ላለማገልገል ምክንያት አይሆነውም። ብዙዎች መንፈሳዊው እውቀት ላይ ደካሞች ስለሆኑ ተበተኑ። የገባቸው ግን ምንም አይገድባቸውም። ልክ እንደኚህ አባት! ለአባታችን ረዥም እድሜ ከጤና ጋር ያድልልን!

ንሽኩር ረቢና!
24/11/2013 ዓ.ም (ቅዳሜ)

ተወዳጆች ሆይ !!

… ለሁላችሁ ይድረስ ዘንድ ከዋልድባ አባቶች የመጣውን መልእክት እና የጻፉትን ደብዳቤም እነሆ ለጥፌላችኋለሁ። የዋልድባ አባቶች የችግራቸውን ዝርዝር ሁኔታ አንድ ሁለት ብለው ገልጸውላችኋል። የባንክ ደብተራቸውንም ልከዋል። እናም በተጠቀሰው የባንክ አካውንት በሃገር ውስጥም ከሃገር ውጪም ያላችሁ እስከ ነገ ረቡዕ ድረስ እያስገባችሁ ጠብቁኝ። ገንዘቡ በሦሥተኛም በሁለተኛም ሰው እጅ አይነካካም። በዚያ በኩል ስጋት አይግባችሁ።

… እናንተ ከያላችሁበት ሆናችሁ የተቻላችሁን አስገቡላቸው። አስገቡና ያስገባችሁበትን ሪሲቱን የክርስትና ስማችሁን እየጻፋችሁበት በውስጥ መስመር ላኩልኝ። ነገ ረቡዕ በመረጃ ቲቪ፣ በኢትዮ ቤተሰብ፣ በዘወንጌል እና ( አግኝቼ አላስፈቀድኩትም ነገር ግን በኋላ ደውዬ እነግረዋለሁ) በወንድሜ በዲን ዓባይነህ ካሤ የፅዋዕ የዩቱዩብ ቻናሎች ላይ ለታላቁ ገዳማችን ለዋልድባ አብረንታንት ገዳም የገቢ ማሰባሰቢያ እናደርግላቸዋለን።

… እግዚአብሔር የፈቀደልን አሁኑኑ መስጠት እንጀምር። ከበረከቱም ለመሳተፍ እንሽቀዳደም። ጀምሩ … እንጀምር።

… ማነው?  የዋልድባ ወዳጅ የመጀመሪያው ፈር ቀዳጅ? እኔ ነኝ በልማ። ፍጠን፣ ፍጠኚ።

ጎንደር ዐቢይ ቅርንጫፍ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የሂሳብ ቁጥር 1000018796779
SWIFT = CBETETAA
ዋልድባ አብረንታንት ገዳም ዘቤተ ሚናስ ማኅበር

“አሁንም፦ አይዞአችሁ ብዬ እመክራችኋለሁ፤ ይህ መርከብ እንጂ ከእናንተ አንድ ነፍስ እንኳ አይጠፋምና።” ሐዋ 27፥22

+ ለምን ትቀናለህ? +

በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡

አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ‘ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ’ ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡

ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው ‘በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ’ ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::

ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡

ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡

ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡

ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ ‘ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ’ ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡

የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ ‘እምቢየው አልገባም’ እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡

ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር’ ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡

የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መከፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ ‘የቤትህ ቅናት በላኝ’ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡

ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡

ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡

ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡

በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡

‘በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን’ ሮሜ 13፡13

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
አለታ ወንዶ ኢትዮጵያ
ጥር 5 2013 ዓ.ም.

መነሻ ሃሳብ:- የአንድ በቅናት ጦስ ሊያበሩ ሲችሉ ብዙ ዋጋ የከፈሉ ቤተሰቦች ታሪክ

የማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተሰቦች እንደምን ከረማችሁ?

ለመጀመሪያዋ ቋንቋችን፣ ለመጨረሻዋ እናታችን ምስጋናን እናቅርብ!! #ዕግትዋ_ለጽዮን ፤ #ጽዮንን_ክበቡአት!!

ዕድሜያችን ባከነ እየተሳቀቀ፣
ልጅ ሆነን አጓጉቶን ፥ ልጅ ሆነን አለቀ ።

እንደገና መወለድ ቢቻል እንኳ አልፈልግም እንጂ ፤ እንደገና ብወለድ ኖሮ ብዙ የማስተካክላቸው የቤት ሥራዎችና የማካክሳቸው የባከኑ ጊዜያት ነበሩኝ። እጅግ በጣም ብዙ!!

አሁን ግን በተሰጠኝ ዕድሜ እንድሠራበትና ዕድሜ ለንስሐ ፥ ዘመን ለፍስሐ እንዲሆነኝ አምላኬን እለምናለሁ፡፡ እናቴን እመ ብርሃንን እማልላለሁ።

የመልከአ ማርያም ደራሲ ይህን እንዳለ፡-

#ሕይወትዬ_በንዝህላል_እመ_ተሰልጠ_ወኀልቀ፤
#ወስክኒ_ክራማተ_እስከ_እገብር_ጽድቀ፡፡

"እናቴ ማርያም ሆይ ዘመኔ ህይወቴ በዋዛ ፈዛዛ በንዝላልነት አልቋልና መልካም [እስክሠራ] የምሠራበትን፣ ጽድቅ [እስክፈጽም] የምፈጽምበትን ጊዜ፣ ዘመን፣ ዓመት፣ ዕድሜ ጨምሪልኝ" እያልኩ እማጸንሻለሁ።

ጣዕምሽን በአንደበቴ፣ ፍቅርሽን በልቦናዬ፣ ንፅሕናሽን በህሊናዬ፣ ቅድስናሽን በሰውነቴ እንዲስልብኝ፤ እንዲያሳድርብኝ!! አዎ ይሳልብኝ፤ ያሳድርብኝ!! ይበልጡኑ ለውዳሴሽ እንድተጋ ….. ወስክኒ ክራማተ እስከ እገብር ጽድቀ፡፡

ስብሐተ እግዚአብሔር ሌትና ቀን በሚፈስበት በዓል፣ ንግሥተ ሰማይ ወምድር እመ ብርሃን ክብሯ በሚነገርበት፣ ቅዳሴዋ ውዳሴዋ በሚደርስበት በድንግል እናታችን መታሰቢያ ዕለት መወለዴ እጅግ ሲበዛ ያስደስተኛል፡፡

ለእመ ብርሃን የሚገባትን ክብር የሚሰጣትና በምልጃዋ ተማምኖ በእናትነት የሚቀበላት ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ሁሉ ይህን ቀን መመኘቱ ግን አይቀርም፡፡ እኔም በዓለ ጽዮንን ክብሩን ሳስብ ልደቴ በዚሁ ቀን የመሆኑ ደስታዬ ወደር የለውም፡፡ የማከብረው ልደቴን ሳይሆን፤ የእመቤቴን በዓለ ክብር ነውና!!

በዓሉ የሁላችንም ኦርቶዶክሳዊያን ስለሆነ መልካም በዓል እንዲሆንልን እየተመኘሁ፤ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እንደተናገረ፤ ክርስቲያኖች ሁላችን ፦

#ጽዮንን_ክበቡአት_በዙሪያዋም_ተመላለሱ፥
#ግንቦችዋንም_ቍጠሩ_በብርታትዋ_ልባችሁን_አኑሩ፤
#አዳራሽዋን_አስቡ_ለሚመጣው_ትውልድ_ትነግሩ_ዘንድ
#ለዓለምና_ለዘላለም_ይህ_አምላካችን_ነው፥
#እርሱም_ለዘላለም_ይመራናል።

(መዝ.48፥12-14) እያልን ዘር ቀለም ሳንለይ በእናታችን ጽዮን ማርያም ፍቅር አንድ ሆነን እንዘምር። በሃይማኖት አንድነት ቤተሰቦች እንሁን (ገላ.6፥10)።

ዘማሪ ዲ/ን ቴዎድሮስ ዮሴፍም "ማርያም ማርያም" በሚል መዝሙሩ ፦

#በተወለድኩበት_በመጀመሪያው_ቀን፣
#ስምሽን_እየጠራሁ_ወጣሁ_ከማኅፀን፡፡

ሲል እንደተቀኘ፤ ለመጀመሪያዋ ቋንቋችን፣ ለመጨረሻዋ እናታችን ምስጋናን እናቅርብ!!

መልካም በዓል ለሁላችንም 🌸🥀💐

#ዕግትዋ_ለጽዮን ፤ #ጽዮንን_ክበቡአት
ለመጀመሪያዋ ቋንቋችን፣ ለመጨረሻዋ እናታችን ምስጋናን እናቅርብ!!

(በሕዳር ጽዮን ቀን 2013 ዓ.ም)
@lijredeat07
ልጅ ረድኤት አባተ ዘጂንካ ሥላሴ

በትሕትናው ልዕልናን ላገኘ፣ ለፍጥረታት ባለው ርኅራኄ የአምላክ እናትን ለሚመስል፣ የተቸገሩትን ፈጥኖ መርዳት ልማዱ ላደረገው፣ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ፣ ደግ እና ሰውን ወዳጅ ለሆነው መልአክ ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል እንኳን በሰላም አደረሰን።

ቅዱሳን መላእክት በአንድ ኃጢአተኛ ወደ እግዚአብሔር መመለስ የሚደሰቱትን ያህል፣ ባልተመለሰው ኃጢአተኛ ደግሞ እንዲሁ ያዝናሉ። በአንዱ ኃጢአተኛ መመለስ የተሰማቸውን ደስታ ፈጣሪያቸውን በማመስገን እንደሚገልጹ፣ ባልተመለሰው ኃጥእ የተሰማቸውን ኃዘን ደግሞ አምላካቸውን "ማረው፣ ይቅር በለው" ብለው በመለመን ያሳያሉ። (ያዕ 5፥13) ቅዱስ ሚካኤል አሁን እንዴት እንደ ሆንን አይቶ ይዘንልን፣ አዝኖም ይለምንልን፣ ለምኖም ያስምረን!!!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

~ ማስታወቂያ እና
አጭር የዜና ጦማር
*~★★~*

• ቻናሌ 200 ሺ ሰው ብቻ ነው መቀበል የሚችለው፣ የሚፈቀድለትም። ቶሎ ቦታ ያዙ። ባለማዕተብ ጓደኞቻችሁንም ጋብዙ። ፍጠኑ።

#ETHIOPIA | ~ አዲስ የመወያያ ቻናል መከፈቱን ስለማሳወቅ። Comment መስጠትም ይቻላል። ጓደኞቻችሁንም ጋብዙ።

https://t.me/zemede_Discussion

•••
የፌስቡክ ፔጄ ቢዘጋብኝ ወደ ዩቲዩብ መንደር ሄድኩኝ። በዚያም መንደር ብዙ ሳልቆይ የዩቲዩብ ቻናሌንም ዘግተው፣ አዳፍተውና ገፍትረው ተረባርበው ወደታች ወረወሩኝ። እነሱ በአፍጢሙ ይደፋል ብለው ሲጠብቁኝ እግዚአብሔር ጭራሽ ላያወርዱኝ፣ ላይደርሱብኝም ከፍ አድርጎ ወደ ላይ በአየር ላይ አስቀመጠኝ። ያለ ዋይፋይ፣ ያለ ኢንተርኔት በየቤቱ በቴሌቭጅን እንድገለጥ አደረገኝ። ክብር ለመድኃኔዓለም። ለወለደችው ለእናቱም ይድረስልኝ አሜን።

•••
ፌስቡክና ዩቲዩብ በተጣሉኝ ጊዜ እስከአሁን ፊቱን ያላጠቆረብኝ የራሺያ ኦርቶዶክሱ የቴሌግራም ካምፓኒ ነው። ቴሌግራም ሆደሰፊ፣ ታጋሽም ነው። ደግሞም ከእነዚያ መንደር ባለቤቶችም ይለያል። ቢያንስ የእመቤታችንን ስም ይጠራል። እናም እኔም የአዛኚቱ ወዳጅ አሽከር የሥላሴ ባርያም መሆኔን አይቶ ነው መሰል እስከአሁን አንዳችም የመግፋት ምልክት አላሳየኝም። ቴሌግራምም ቴሌግራሜም እስከአሁን ሰላም ነን።

•••
በቴሌግራም መንደር አንድ የነበረው ቅሬታ በቻናሉ ውይይት፣ ኃሳብ መለዋወጥ ያለመቻል ብቻ ነበር። እሱን ነገር በዛሬው ዕለት፣ ህዳር 3/2013 ዓም መፍትሄ አግኝቷል። በተመረጠ ርዕስ፣ በተመረጠው ሰዓት፣ የመወያያ፣ ሃሳብ የመለዋወጫ ቻናልም ይኸው ከፍቻለሁ። ከዛሬ ጀምሮ በምጽፈው ጦማር ላይ አስተያየት መስጠትም ይቻላል። ታዲያ በጨዋ ደንብ ነው። በቴሌግራም ደግነቱ ሁሉም ሰው በራሱ የግል ስልክ ቁጥሩ ነው የሚገባው። የብዕር ስም እንጂ የሚኖረው የብዕር ስልክ ቁጥር የለውም። እንደ ፌስቡክ ለመሳደብም፣ ባለጌ ለመሆንም አይመችም። በቴሌግራም ጨዋ መሆን ግድ ነው። ከቴሌግራም ቻናሌ አንድ ጊዜ ከተወገዱ አከተመ። እናም ጨዋ መሆን ለራስ ነው።

•••
የቴሌግራም ቻናል የሚፈልገው የሰው ብዛት ሁለት መቶሺህ ሰው ብቻ ነው። ሁለት መቶ ሺ ሰው። ከዚህ በላይ አይይዝም። አይፈቅድምም። እናም ነፍስ ያላቸው ባለ ማዕተብ ጓደኞቻችሁን ጭምር በመጋበዝ ወደ ዘመዴ የውይይት መድረክ አምጧቸው። ጋብዟቸው።

https://t.me/zemede_Discussion አዲሱ ቻናሌ ነው። የሚገርመው ነገር ገና የመወያያ ቻናሉን ሳላስተዋውቀው ከአሁኑ ወደ 154 ጓደኞቼ ቤት ለእምቦሳ ብለው ተከስተዋል። እንኳን ደህና መጣችሁ።

… በመጨረሻም !!

ዛሬ ከወደ ራያ ቆቦ አንድ ጆሮ ጭው የሚያደርግ መረጃ ደርሶኛል። ህወሓት በራያ ግንባር ከሰሞኑ ልክ እንደማይካድራው አይነት ዘግናኝ መርዶ ሳታሰማን አትቀርም እየተባለ ነው። በራያ ንፁህ ዐማሮች ናቸው የተባሉትን በሙሉ ህወሓት ለቃቅማ ወደ መታረጃ ከምፖች መውሰዷን ከሥፍራው አምልጠው የመጡ ዐማሮች ተናግረዋል ተብሏል። ውጊያው ሊጀመር ከጫፍ ደርሷል። እናም ህወሓት መሸነፌ ካልቀረ በማለት በራያ ላይ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ለመፈጸም መዘጋጀቷ ነው የሚነገረው። የሚገርመው ነገር ፦

• በሶማሊያም የታረደው ዐማራ
• በደቡብም የታረደው ዐማራ
• በቤኒሻንጉልም የታረደው ዐማራ
• በኦሮሚያም የታረደው ዐማራ
• ትናንት በማይካድራም የታረደው ዐማራ
• ዛሬም ሊታረድ ወደ መታረጃ ቄራው የገባው ዐማራ።

… በቃ ዐማራ ማለት የኢትዮጵያ ኃጢአት የማስተሰረያ በግ ሆነ ማለት ነው? ህወሓቶች ይሄን ነገር ባይሞክሩት ይሻላቸዋል። ለራሳቸውና ለዘራቸው ሲሉ ባይሞክሩት ይሻላቸዋል። ምክሬ ነው።

•••
በተረፈ እንደተለመደው ዛሬም እንደ ትናንቱ በተለመደው ሰዓት በመረጃ ቲቪ እንገናኛለን። ሰብሰብ ብላችሁ ጠብቁኝ።

ሰምታችኋል ! ኣ

@zemede_Discussion

https://youtu.be/nlveTj5bWwE