የላፍቶ ቢላል መስጂድ የትምህርት መድረክ Telegram Posts

ይህ ቻናል በላፍቶ ቢላል መስጂድ የሚሰጡ ደርሶችን እና የተለያዩ ሙስሊሙን የሚጠቅም ሙሀደራዎችና አጫጭር መልዕክቶች የሚለቀቅበት ሲሆን ሊንኩን በመጠቀም ለራሳችንም ሌሎችም እንዲጠቀሙ እናድርግ
https://t.me/lafto_qirat
https://t.me/lafto_qirat
1,739 Subscribers
195 Photos
65 Videos
Last Updated 09.03.2025 05:06
Similar Channels

13,761 Subscribers

2,978 Subscribers

2,208 Subscribers
The latest content shared by የላፍቶ ቢላል መስጂድ የትምህርት መድረክ on Telegram
ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም በላፍቶ ቢላል መስጂድ❗️
⚡️ሊያመልጦ የማይገባ ወሳኝ ፕሮግራም
🎙 በኡስታዝ ተውፊቅ ራህመቶ
🗓 እሁድ የካቲት 30 ዙሁር እንደተሰገደ
⚠️ሴቶችንም ወንዶችንም ይመለከታል❗️❗️❗️
🔖ኑ! ተባብረን የተሻለ ማንነት በመፍጠር የሁለት ሀገር ስኬትን እንጎናፀፍ!
ሼር በማድረግ ላልደረሰው ያድርሱ!
⚡️ሊያመልጦ የማይገባ ወሳኝ ፕሮግራም
🎙 በኡስታዝ ተውፊቅ ራህመቶ
🗓 እሁድ የካቲት 30 ዙሁር እንደተሰገደ
⚠️ሴቶችንም ወንዶችንም ይመለከታል❗️❗️❗️
🔖ኑ! ተባብረን የተሻለ ማንነት በመፍጠር የሁለት ሀገር ስኬትን እንጎናፀፍ!
ሼር በማድረግ ላልደረሰው ያድርሱ!
⚫️السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
በሸገር ሲቲ ገላን ክ/ከተማ አንዶዴ ወረዳ ላይ 2013 ዓ.ል ذا النورين (ዘኑረይን) ለተሰኘ መስጂድ መስሪያ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ከሆነ ግለሰብ ላይ 300 ካሬ የተገዛ ሲሆን ከርሱም ላይ 100 ካሬ ማለትም 10*10 የሆነ አነስ ያለ መስጂድ በቆርቆሮ ተሰርቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ከግለሰቡ ቅንነት የተነሳ ተጨማሪ መሬት ለመስጠት ፈቃደኛ በመሆን ተጨማሪ 1400 ካሬ ልስጣችሁ ክፍያውንም(2 ሚሊየን ገደማ) በረጅም ጊዜ ክፍያ ትከፍላላችሁ በማለት ከሌላ እምነት ተከታዮች የመጣውን መሬቱን የመውሰድ ጉጉት ውድቅ በማድረግ በተለይ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች በፈለገው ዋጋ እንደሚስማሙ እና መሬቱን እንዲሰጣቸው ቢጠይቁትም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል።ነገር ግን የአካባቢው ሙስሊም ቁጥር አናሳ መሆንና በአቅም ማነስ ምክንያት አይደለም የተሻለ መስጂድ ለመገንባት የመሬቱን እዳ እንኳን ሳንሸፍን ለአመታት ቆይቷል፣ግለሰቡም ከዛሬ ነገ ይከፍሉኛል በሚል በትእግስት ሲጠባበቅ ቆይቷል።አሁን ግን የሚፈልገውን ጥቅም ባለማግኘቱ መሬቱን መልሶ መውሰድ እንደሚፈልግ አሊያም በአስቸኳይ ክፍያውን እንድንፈፅም ለመስጂዱ ጀመአና ኮሚቴ በተደጋጋሚ እያስጠነቀቀ ይገኛል። ስለዚህ ይህንን የአላህ ቤት ለማስፋፋት (መድረሳ እና ሌሎች ለአካባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ ሚጠቅሙ) ስራዎችን ላዩ ላይ ለመስራት መሬቱ የግድ ስለሚያስፈልገን የሌሎች ሙስሊም ወገኖቻችን እርዳታ ያሻናል!!!
🔗(የዘኑረይን መስጂድ ጀመዐ እና ኮሚቴው)
ንግድ ባንክ: 1000614390321 የአካውንት ስም: zenureyn mesjd (ዘኑረይን መስጂድ)
አዋሽ ባንክ: 014251315326100 ኤሊያስ፣ ኡስማን እና ጀማል
በሸገር ሲቲ ገላን ክ/ከተማ አንዶዴ ወረዳ ላይ 2013 ዓ.ል ذا النورين (ዘኑረይን) ለተሰኘ መስጂድ መስሪያ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ከሆነ ግለሰብ ላይ 300 ካሬ የተገዛ ሲሆን ከርሱም ላይ 100 ካሬ ማለትም 10*10 የሆነ አነስ ያለ መስጂድ በቆርቆሮ ተሰርቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ከግለሰቡ ቅንነት የተነሳ ተጨማሪ መሬት ለመስጠት ፈቃደኛ በመሆን ተጨማሪ 1400 ካሬ ልስጣችሁ ክፍያውንም(2 ሚሊየን ገደማ) በረጅም ጊዜ ክፍያ ትከፍላላችሁ በማለት ከሌላ እምነት ተከታዮች የመጣውን መሬቱን የመውሰድ ጉጉት ውድቅ በማድረግ በተለይ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች በፈለገው ዋጋ እንደሚስማሙ እና መሬቱን እንዲሰጣቸው ቢጠይቁትም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል።ነገር ግን የአካባቢው ሙስሊም ቁጥር አናሳ መሆንና በአቅም ማነስ ምክንያት አይደለም የተሻለ መስጂድ ለመገንባት የመሬቱን እዳ እንኳን ሳንሸፍን ለአመታት ቆይቷል፣ግለሰቡም ከዛሬ ነገ ይከፍሉኛል በሚል በትእግስት ሲጠባበቅ ቆይቷል።አሁን ግን የሚፈልገውን ጥቅም ባለማግኘቱ መሬቱን መልሶ መውሰድ እንደሚፈልግ አሊያም በአስቸኳይ ክፍያውን እንድንፈፅም ለመስጂዱ ጀመአና ኮሚቴ በተደጋጋሚ እያስጠነቀቀ ይገኛል። ስለዚህ ይህንን የአላህ ቤት ለማስፋፋት (መድረሳ እና ሌሎች ለአካባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ ሚጠቅሙ) ስራዎችን ላዩ ላይ ለመስራት መሬቱ የግድ ስለሚያስፈልገን የሌሎች ሙስሊም ወገኖቻችን እርዳታ ያሻናል!!!
🔗(የዘኑረይን መስጂድ ጀመዐ እና ኮሚቴው)
ንግድ ባንክ: 1000614390321 የአካውንት ስም: zenureyn mesjd (ዘኑረይን መስጂድ)
አዋሽ ባንክ: 014251315326100 ኤሊያስ፣ ኡስማን እና ጀማል
ጥፋት ላይ መውደቅ እና ጥፋትን መንገድ አድርጎ መያዝ የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው። ጥፋት ላይ መውደቅ እንደ ሰው ማንንም ሰው የሚያጋጥም ነው። በሐዲሥ እንደተጠቀሰው "ሁሉም የሰው ልጅ በጣም ተሳሳች ነው።"
ጥፋትን የሚጓዙበት መንገድ አድርጎ መያዝ ግን የተለየ ከባድ ጥፋት ነው።
ጥፋትን የሚጓዙበት መንገድ አድርጎ መያዝ ግን የተለየ ከባድ ጥፋት ነው።
አደራህን❗️
✨የአላህ ዲን አንድ ነው እና በዲን ጉዳይ አትለዋወጥ✨
(ታላቁ ሰሀቢ ሁዘይፋ ቢን የማን رضي الله عنه)
✨የአላህ ዲን አንድ ነው እና በዲን ጉዳይ አትለዋወጥ✨
(ታላቁ ሰሀቢ ሁዘይፋ ቢን የማን رضي الله عنه)
ጃቢር ኢብኑ ዐብዲላህ እንዲህ ብሏል፦
“ፆመኛ ከሆንክ ዓይንና ጆሮህም ይፁም ፤ ምላስህም ከውሸት እና ከክፉ ነገር ይፁም ፤ የፆምክ ቀን ፍፁም የሆነ መረጋጋትም ይታይብህ፤ የፆምክበት እና ያፈጠርክበት ቀን እኩል እንዲሆንም አትፍቀድ።”
(ሹዐቡ’ል ኢማን 3374)
#ረመዷን_1
“ፆመኛ ከሆንክ ዓይንና ጆሮህም ይፁም ፤ ምላስህም ከውሸት እና ከክፉ ነገር ይፁም ፤ የፆምክ ቀን ፍፁም የሆነ መረጋጋትም ይታይብህ፤ የፆምክበት እና ያፈጠርክበት ቀን እኩል እንዲሆንም አትፍቀድ።”
(ሹዐቡ’ል ኢማን 3374)
#ረመዷን_1
ምን አልባት የመጨረሻው ረመዳንህ ሊሆን ይችላልና ነገ ትሞታለህ ቢባል የምትፆመውን ፆም ለመፆም ቆራጥ ሁን❗️
🔴ሰበር ዜና
የዘንድሮው1446/2025 የረመዳን ወር ጨረቃ በሳውዲ አረቢያ ታይቷል!
በዚህም መሰረት ነገ ቅዳሜ ረመዳን 1 ይሆናል።
የዘንድሮው1446/2025 የረመዳን ወር ጨረቃ በሳውዲ አረቢያ ታይቷል!
በዚህም መሰረት ነገ ቅዳሜ ረመዳን 1 ይሆናል።
ደጋጎች በኢባዳ ትጉ ከመሆናቸዉ ጋር አይናቸዉ ያነባል ልባቸዉ በፍራቻ ተሞልቷል እኛ የወንጀል ማእበል ዉስጥ ሁነን ሳቅ ጨዋታችን በዛ ከአኺራ ተዘናጋን ።
رحماك يا رب
رحماك يا رب
* የሰው ሐቅ ተሸክመህ ወደ ረመዳን አትግባ። መክፈል እየቻልክ የሰው ሐቅ ይዘህ አታጉላላ። አቅቶህ ከሆነ ጊዜ እንዲሰጡህ በትህትና አስረዳቸው።
* የበደልከውን ይቅርታ ጠይቅ። የበደሉህን ይቅር በል።
* መክፈል የማይችል ሰው ላይ ሐቅ ካለህ ብትችል እለፍ ወይም ቀንስላቸው። ካልሆነ ጊዜ ስጣቸው። "የትም ገብታችሁ አምጡ" አትበል። ወንጀል ላይ ገብተው ቢሰጡህ ሐላል አይሆንልህም።
* ስትሸጥም ስትገዛም ገር እና ቅን ሁን። ገዥም ሻጭም ሆነህ ሶደቃ የምታደርግበት ሁኔታ እንዳለ አስተውል።
* ግብይትህ ላይ ከውሸት፣ መሀላ ከማብዛት፣ ከማታለል፣ ... ተጠንቀቅ። ጊዜ ካለህ ቁርኣን ቅራ። ዚክር አድርግ።
* ቤትህ ውስጥ ሰላም ሁን። ከጭቅጭቅ ራቅ። ሶብር ይኑርህ። ለሚስትህ፣ ለልጆችህ አሳቢ፣ ተቆርቋሪ ሁን። ከአላህ በታች ያላንተ ማን አላቸው? ለባልሽ ምቹ ሁኚ። አንቺ ፈተና ከሆንሽበት ውሎውን ሁሉ ሰላም ያጣል።
=
ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
* የበደልከውን ይቅርታ ጠይቅ። የበደሉህን ይቅር በል።
* መክፈል የማይችል ሰው ላይ ሐቅ ካለህ ብትችል እለፍ ወይም ቀንስላቸው። ካልሆነ ጊዜ ስጣቸው። "የትም ገብታችሁ አምጡ" አትበል። ወንጀል ላይ ገብተው ቢሰጡህ ሐላል አይሆንልህም።
* ስትሸጥም ስትገዛም ገር እና ቅን ሁን። ገዥም ሻጭም ሆነህ ሶደቃ የምታደርግበት ሁኔታ እንዳለ አስተውል።
* ግብይትህ ላይ ከውሸት፣ መሀላ ከማብዛት፣ ከማታለል፣ ... ተጠንቀቅ። ጊዜ ካለህ ቁርኣን ቅራ። ዚክር አድርግ።
* ቤትህ ውስጥ ሰላም ሁን። ከጭቅጭቅ ራቅ። ሶብር ይኑርህ። ለሚስትህ፣ ለልጆችህ አሳቢ፣ ተቆርቋሪ ሁን። ከአላህ በታች ያላንተ ማን አላቸው? ለባልሽ ምቹ ሁኚ። አንቺ ፈተና ከሆንሽበት ውሎውን ሁሉ ሰላም ያጣል።
=
ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር