来自 JUECSF Main & Beco (@juecs_fellowship) 的最新 Telegram 贴文

JUECSF Main & Beco Telegram 帖子

JUECSF Main & Beco
ይህ በኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስትያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማህበር (EvaSUE) የጅማ ዩኒቨርስቲ (Main and Beco Campus) ወንጌላውያን ክርስትያን ተማሪዎች ህብረት የመገናኛ የtelegram channel ነው


ለማንኛውም ጥያቄ :
@juecsfmainbeco
0936281818

ንግድ ባንክ አካውንት
1000306692147
(Naol Ararsa and/or Tigist Dereje)
1,512 订阅者
1,345 张照片
19 个视频
最后更新于 09.03.2025 12:13

JUECSF Main & Beco 在 Telegram 上分享的最新内容

JUECSF Main & Beco

17 Jan, 17:59

769

ሰው አይሆንም ብለው ሰው አረገኝ ጌታ (ጌታዬ ጌታ ጌታዬ)
ደጀን የለው ብለው ሆነልኝ መከታ (ጌታዬ ጌታ ጌታዬ)
እንዳሰቡት ሳይሆን እንዳሰበልኝ ነው (ጌታዬ ጌታ ጌታዬ)
ገና መቼ አዩ ይሄ ጅማሬ ነው (ጌታዬ ጌታ ጌታዬ)

አምላኬ የእኔማ ተስፋ
እንዳልወድቅ ከቶ እንዳልጠፋ
የእኔ አባት የእኔ መድኃኒት
በአንተ ነው እዚህ የደረስኩት

አንተ ነህ እኔማ ተስፋ
እንዳልወድቅ ከቶ እንዳልጠፋ
የእኔ አባት የእኔ መድኃኒ
በአንተ ነው እዚህ የደረስኩት

በአንተ ነው እዚህ የደረስኩት
በአንተ ነው ሁሉን ያለፍኩት
በአንተ ነው ቀን የወጣልኝ
ጌታዬ ተመስገንልኝ (2x)

አስታዋሽ ለሌለኝ ለተረሳሁ በሰው (ጌታዬ ጌታ ጌታዬ)
ከተፍ ብሎልኛል ፍቅሩ በተግባር ነው (ጌታዬ ጌታ ጌታዬ)
እንባ አወጡ አይኖቼ በደስታ ተሞሉ (ጌታዬ ጌታ ጌታዬ)
ህመሜኮ ያመዋል ስለሆንኩ አካሉ (ጌታዬ ጌታ ጌታዬ)

አምላኬ የእኔማ ተስፋ
እንዳልወድቅ ከቶ እንዳልጠፋ
የእኔ አባት የእኔ መድኃኒት
በአንተ ነው እዚህ የደረስኩት

አንተ ነህ እኔማ ተስፋ
እንዳልወድቅ ከቶ እንዳልጠፋ
የእኔ አባት የእኔ መድኃኒ
በአንተ ነው እዚህ የደረስኩት

በአንተ ነው እዚህ የደረስኩት
በአንተ ነው ሁሉን ያለፍኩት
በአንተ ነው ቀን የወጣልኝ
ጌታዬ ተመስገንልኝ (2x)

የምስኪኑ ወዳጅ ለተከፋው ፈራጅ
ለድሃደጉ አባት ለደከመው ብርታት (2x)

ማረፊያ ጥላዬ
መጠጊያ ከለላዬ
ኢየሱስ ጌታዬ (2x)

ኢየሱስ ጌታዬ (4x)
JUECSF Main & Beco

17 Jan, 17:58

658

እጅጉን ሲራራ በብዙ ሲምር
ከቶ ያበቃለትን የሞት ፍርድ ሲሽር
ሲስብ ወደራሱ ለክብር መንግስቱ
እኔ እርሱን የማውቀው በሰፊ ትዕግስቱ

መክሮ ሲመልስ ለክብር ሲያበቃ
ውጦ ከሚያስቀር ከረግረጉ ጭቃ
ታሪክ ቀይሮ ሥምንም ሲለውጥ
ነጥቆም ሲታደግ ካንሸራታቹ ድጥ (2x)

አዝ፦ይሄ ነው የኔ ጌታ
ይሄ ነው አምላኬ የምለው
ይሄ ነው ደግ ቸር ያልኩት
እግዚአብሔርን የወደድኩት (2x)

የተራበው ሲጠግብ ሲረካ ጠጥቶ
ሲድን ከጠላቱ ወደ አምላኬ ሸሽቶ
በኖርኩበት ዘመን ይሄንን አውቃለሁ
መልካም ቸር እረኛ እንደ እግዚአብሔር ማነው

ከጥላው በታች ማረፍ የወደደ
በዓለም በረሃ ከስሎ የነደደ
ሸክሙ ሲራገፍ እፎይ ሲል ሲቀለው
በርሱም ሲታሰብ ባይኔ አይቻለሁ (2x)

አዝ፦ይሄ ነው የኔ ጌታ
ይሄ ነው አምላኬ የምለው
ይሄ ነው ደግ ቸር ያልኩት
እግዚአብሔርን የወደድኩት (2x)

ክፉኛ ተወግቶ ልቡ ለቆሰለ
በኃዘን ተከቦ አበቃልኝ ላለ
ወዳጅ ይሆነዋል ጌታ ተጠግቶ
ቁስሉን ያክመዋል በዘይት ቀብቶ

ቀና ሲያደርገው አንገቱን ላይደፋ
የሚጤሰውን ጧፉን ሳያጠፋ
አትሞትም በሕይወት ትኖራለህ ሲለው
የአምላኬን ፍቅር እኔ አውቀዋለሁ (2x)

አዝ፦ይሄ ነው የኔ ጌታ
ይሄ ነው አምላኬ የምለው
ይሄ ነው ደግ ቸር ያልኩት
እግዚአብሔርን የወደድኩት (2x)

አለኝ ሊቀ-ካህን በላይ በሰማይ
አዝኖ የሚራራ ድካሜን የሚያይ
ለበደሌ ስርየት ለሐጥያቴ ይቅርታ
ሰጠኝ በምህረቱ ይሄ መልካም ጌታ

አባባ የሚል የልጅነት መንፈስ
ውስጤ አፈሰሰ ቸሩ ጌታ ኢየሱስ
መንፈሱን ታጥቅኩኝ ድኛለሁኝ በቃ
ሞትና እርግማን ከእንግዲህ አበቃ

አዝ፦ይሄ ነው የኔ ጌታ
ይሄ ነው አምላኬ የምለው
ይሄ ነው ደግ ቸር ያልኩት
እግዚአብሔርን የወደድኩት (4x)
JUECSF Main & Beco

17 Jan, 17:57

661

በእረኝነቱ ተመርቻለሁ
ጠንቀቅ አድርጌም ድምፁን አውቃለሁ
በአረንጓዴው መስክ ባማረው ላይ
አንሰራፍቶኛል ሳይኖር ከልካይ

አልፈራም አውሬ ደፋር አርጎኛል
የአራዊት ድምፅ መቼ ያስፈራኛል
ባለመናወጥ ከምንጩ ልርካ
ከጭንቀት ማረፍ እንዲህ ነው ለካ

እንዲህ ነው ለካ አሃ
እንዲህ ነው ለካ (፬x)

ኧረ እንዴት ተለዪው ይሉኛል
ይህን የቅርብ ወዳጄን
ኧረ እንዴት ተለዪው ይሉኛል
ይህን የበረሃ ጓዴን
ኧረ እንዴት ተለዪው ይሉኛል
ይህን ሚስጢረኛዬን
ኧረ እንዴት ተለዪው ይሉኛል
ይህን መልካም እረኛዬን

አልለየውም አልለየውም
ያለ እርሱ መኖር እኔስ አልችልም
አልለየውም አልለየውም
ያለ እርሱ ውበት ወዝም የለኝም ( 2x)

ዝቅ ዝቅ ያልኩትን ያለ ከፍታዬ ከፍ ከፍ ያረገኝ
ወገን ያልሆንኩትን በልጁ ልጅ አርጎ ማዕረግን ያሳየኝ
የተደረገውን በጎነት ቸርነት አልችልም መሸከም
የምልህ የለኝም በሰጠኸኝ ዘመን ከፊት ፊቴ ቅደም

ብርታቴ እኮ ነህ ብርታቴ
ህይወቴ እኮ ነህ ህይወቴ
ጉልበቴ እኮ ነህ ጉልበቴ
ኢየሱስ ለእኔ መድኃኒቴ ( 2x)
መድኃኒቴ መድኃኒቴ ( 2x)
JUECSF Main & Beco

17 Jan, 17:56

677

ተራራው ከፊቴ እንደሰም ቀለጠ ምሥጋናዬ ነህ
ቃልህም ሲወጣ ጫካው ተገለጠ ምሥጋናዬ ነህ
እግሮቼም ፀኑልኝ እንደዋላ እግር ምሥጋናዬ ነህ
ረዳት ሆነኸኛል አምላኬ ክበር ምሥጋናዬ ነህ

አዝ፦ ልሰዋ የምሥጋናን መስዕዋት (2x)
ሆነኸኝ አይቻለሁ አባት (2x)
ላክብርህ እኔ ደጋግሜ (2x)
ከፍ በል ላዚም ፊትህ ቆሜ (2x)
አቤቱ ተደንቄያለሁኝ እና (2x)
ልሰዋ ምሥጋና (4x)

ምህረትህ ከሕይወት በርግጥም ይበልጣል ምሥጋናዬ ነህ
ደጅ ጥናት የለም በፍጥነት ያነሳል ምሥጋናዬ ነህ
ድንጋይ ተደርድሮ ሞት ሲጠብቃት ምሥጋናዬ ነህ
ሀፍረቷን ሸፍነህ ሰላም ሂጂ አልካት ምሥጋናዬ ነህ

አዝ፦ ልሰዋ የምሥጋናን መስዕዋት (2x)
ሆነኸኝ አይቻለሁ አባት (2x)
ላክብርህ እኔ ደጋግሜ (2x)
ከፍ በል ላዚም ፊትህ ቆሜ (2x)
አቤቱ ተደንቄያለሁኝ እና (2x)
ልሰዋ ምሥጋና (4x)
JUECSF Main & Beco

17 Jan, 06:25

1,112

የጌታ ሰላም ይብዛላችሁ!

ነገ(ቅዳሜ ) እንደተለመደው 11:30 ላይ የአጠቃላይ ህብረታችን የአምልኮ ጊዜ ይቀጥላል። በዚህም "የመንፈስ ፍሬ እና የስጋ ስራ" በሚል ርዕስ የትምህርት ጊዜ ይኖረናል። ስለሆነም ሁላችንም ማስታወሻ እና መፅሀፍ ቅዱሳችንን እየያዝን  በአንድነት ሆነን ጌታን ለማምለክ በጊዜ እንድንገኝ ስንል በጌታ ፍቅር እናሳስባለን።

“የክርስቶስ ኢየሱስ የሆኑት ሥጋን ከክፉ ምኞቱና መሻቱ ጋር ሰቅለውታል።”
— ገላትያ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)

ነገ (ቅዳሜ)- 11:30-2:00
💒መሰረተ ክርስቶስ ቤ/ክ

ተባረኩ!

@JUECS_Fellowship
JUECSF Main & Beco

13 Jan, 17:57

994

ሰላም ቅዱሳን!

ነገ(ማክሰኞ) የአጠቃላይ ህብረቱ የፀሎት ጊዜ ስለሆነ የምንችል ሁላችን እንድንገኝና እንድንፀልይ ስንል በጌታ ፍቅር እናሳስባለን።

“እንግዲህ ከሁሉ አስቀድሞ ልመናና ጸሎት፣ ምልጃና ምስጋና ለሰዎች ሁሉ፣ ለነገሥታትና ለባለ ሥልጣናት ሁሉ እንዲደረግ አሳስባለሁ፤”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥1 (አዲሱ መ.ት)

ማክሰኞ 12:00-2:00
📍MKC

ተባረኩ!
JUECSF Main & Beco

10 Jan, 19:20

1,155

የተወደዳችሁ  ቤተሰቦቻችን

ነገ(ቅዳሜ ) እንደተለመደው 11:30 ላይ የአጠቃላይ ህብረታችን የአምልኮ ጊዜ ይቀጥላል። ስለሆነም ሁላችንም ማስታወሻ እና መፅሀፍ ቅዱሳችንን እየያዝን  በአንድነት ሆነን ጌታን ለማምለክ በጊዜ እንድንገኝ ስንል በጌታ ፍቅር እናሳስባለን።

“እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ፤ ስምህ በምድር ሁሉ ላይ ምንኛ ግርማዊ ነው! ክብርህ ከሰማያት በላይ፣ ከፍ ከፍ ብሎአል።”
— መዝሙር 8፥1 (አዲሱ መ.ት)

ነገ (ቅዳሜ)- 11:30-2:00
💒መሰረተ ክርስቶስ ቤ/ክ

ተባረኩ!

@JUECS_Fellowship
JUECSF Main & Beco

07 Jan, 00:35

1,154

ተሽቀዳደሙ ኑ እዩት
የሚመስልህ የለም በሉት
_______________
————————————

Inbox 👉🏽 @Debbie_gecho
JUECSF Main & Beco

06 Jan, 16:03

1,230

ዝግጅታችንን ጨርሰን እየጠበቅናቹ ነው።💚💚
JUECSF Main & Beco

06 Jan, 09:05

1,050

👆👆👆በዛሬው ዕለት( የአዳር መረሀ ግብር ) ላይ ባለን የ ህብረት ጊዜ በህብረት ለመዘመር የተመረጡ መዝሙሮች ናቸው እየሰማችኋቸው እንድትቆዩ ይሁን::