ቅድመ ታክስ /With Holding Tax/
የፈደራል ገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008፤የፈደራል ታክስ አስተዳደር ቁጥር 983/2008፤ በመመሪያ ቁጥር 2/2011 መሰረት :-
ቅድመ ታክስ ማለት አንድ አገልግሎት ወይም የዕቃ ግዢ በሚከናወንበት ግዜ ገዢዉ ለአገልግሎት ወይም ለዕቃ ከሚከፍለዉ ክፍያ ላይ ግብር ቀንሶ ለመንግስት የሚያሳዉቀዉ የግብር አይነት ነዉ ፡፡
አላማ፡-መንግስት ቅድመ ግብርን በበጀት አመቱ መጨረሻ ከሚሰበስብ ይልቅ ገቢ በተገኘበት ወቅት ሰብስቦ ልማትን ለማፋጠን አመቺ ነዉ ከሚል አንጻር የመጣ ነዉ፡፡
ምጣኔው...
አንደኛ:-ለንግድ ለሚዉሉ ዕቃዎችን ወደ አገር ስያስገቡ የእቃዎቹ የጉምሩክ ዋጋ ፤ የመጓጓዣ ዋጋ (CIF) መሰረት በማድረግ 3%የንግድ ስራ ገቢ ግብር በቅድሚያ ለባለስልጣኑ ይከፍላል ፡፡
ሁለተኛ:-በሀገር ዉሰጥ ከሚፈፀሙ ክፍያዎች ላይ ግብር ቀንሶ የማስቀረት ግደታ የተጣለባቸዉ ድርጅቶች (ሰዎች)፤
✅በአንድ የዕቃ ግዥ ከ10,000 በላይ ለሆነ የዕቃ አቅርቦት ለሚፈፀም ክፍያ እና
✅በአንድ በአገልግሎት ዉል ከ3,000 በላይ ለሚፈፀም ከፍያ 2% ግብር ቀንሰዉ የማስቀረት ግዴታ አለባቸዉ ፡፡
በመጨረሻ
✍️ግብር ተቀናሽ የሚደረግበት ዕቃ ወይም አገልግሎት አቅራቢ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩን እና የፀና የንግድ የስራ ፈቃዱን ግብር ቀንሰዉ ለሚያስቀረዉ ገዢ ልያቀርብ ካልቻለ ገዢዉ ለአቅራቢዉ ከሚፈጽመዉ ጠቅላላ ክፍያ ላይ 30% ግብር ተቀናሸ ማድረግ አለበት ፡፡
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
ለበለጠ ስለ ግብር ለመማር ከ 78,600 በላይ ተከታይ ያለውን የ You Tube ቻናል ማለትም Hani Tube ይቀላቀሉ
አካውንቲንግ ትምህርት እና የኢትዮጵያ ታክስ አሰራር እና አዋጆችን ለመማር :-
📣You tube:- https://www.youtube.com/@Ethiopiatax
📣ዌብሳይት:Www.hanitube.com
📣https://t.me/hanitube ቴሌግራም ቻናል
#Withholdingtax #ታክስ #ንግድ #ገቢዎች #አዲስአበባገቢዎች #በመርካቶ #ethiotax #EthiopiaTaxlaw #የተጨማሪ_እሴት_ታክስ_አዋጅ #የቴምብር_ቀረጥ_አዋጅ #AddisAbaba