The Federal Supreme Court of Ethiopia (@fscethiopiapr)の最新投稿

The Federal Supreme Court of Ethiopia のテレグラム投稿

The Federal Supreme Court of Ethiopia
Federal Supreme Court is the highest court in Ethiopia. It is constitutionaly established court. It is also one of the three pillars of the federal state that assures the check and balance in & among.
10,732 人の購読者
1,807 枚の写真
21 本の動画
最終更新日 01.03.2025 06:39

The Federal Supreme Court of Ethiopia によってTelegramで共有された最新のコンテンツ


በፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለዎትን ቅሬታ/አስተያየት በቴክኖሎጂ በመታገዘ ያቅርቡ
********
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለተገልጋዮች ቅሬታ እና አስተያየት ማቅረቢያ የቴክኖሎጂ መተግበሪያ በውስጥ አቅም በማልማት ከየካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

ይህን መተግበሪያ ለመጠቀም ተገልጋዮች ወደ ተቋሙ በሚመጡበት ወቅት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያላቸውን ቅሬታ በድምፅ አሊያም በፅሁፍ የሚያሰፍሩበት ሲስተም ሲሆን ወደ ተቋሙ ለአገልግሎት በሚመጡበት ወቅት ተቋሙ ውስጥ በሚገኘው የወንጀል ይግባኝ ጉዳዮች የአንድ ማዕከል ሬጅስትራር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ውስጥ የዳኝነት ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ክፍል በመቅረብ በስራ ክፍሉ በሚገኙ ባለሙያዎች በመታገዝ አሊያም በእጅ ስልኮ በተቋሙ ኢንተርኔት/ዋይፋይ በመጠቀም የተቋሙን QR ኮድ ስካን በማድረግ የዳኝነት ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ፅ/ቤት የሚለውን በመጫን በድምፅ ወይንም በፅሁፍ ቅሬታዎን/አስተያየቶን ያቅርቡ ከሚሉ አማራጮች የሚፈልጉትን በመምረጥ ቅሬታዎን ማቅረብ ይችላሉ፡፡

ቅሬታው/አስተያየቱ የሚቀርበው በድምፅ ከሆነ የድምፅ ምልክቷን በመጫን መልእክቱን ማስተላለፍ የሚቻል ሲሆን በፅሁፍ የሚቀርብ ሲሆን ከተዘረዘሩት አስተያየት መስጫ ነጥቦች (እጅግ ከፍተኛ፣ ከፍተኛ፣ መካከለኛ ወይም ዝቅተኛ) አንዱን በመምረጥ አስተያየቶን መስጠት ይችላሉ፡፡

የተገልጋይ ቅሬታም ወደ ሰርቨር ገብቶ ደህንነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት የሚላክ መሆኑን በትህትና እንገልጻለን፡፡

የአጠቃቀሙን ቅደም ተከተል ከስር ባለው ምስል ይመልከቱ፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽንና ስትራቴጂያዊ አጋርነት ዳይሬክቶሬት

የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ የፍርድ ቤቶችን የሰው ኃይል አቅም መገንባት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተገለጸ
*********
በፌደራል ፍርድ ቤቶች የተጀመረውን የለውጥ ሥራ ተፈጻሚ ለማድረግ የፍርድ ቤቶችን የሰው ኃይል አቅም መገንባት ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ አበባ እምቢአለ ገለጹ፡፡

ክብርት ምክትል ፕሬዝደንት ይህን የገለጹት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባዘጋጀውና ከሶስቱም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ለተውጣጡ 110 ሠራተኞች ከየካቲት 20-22 ቀን 2017 ዓ.ም በተዘጋጀው የሶስት ቀናት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መክፈቻ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው፡፡

የፌደራል ፍርድ ቤቶች በጀመሩት የለውጥ ሥራ የተከናወኑ እና በመሠራት ላይ ያሉ ማሻሻያዎች እንደሚገኙ የጠቆሙት ም/ፕሬዚደንት ከእነዚህ መካከል የሕግ ማሻሻያዎች፣ የቴክኖሎጂ ሥራዎች እና የሰው ኃይል አቅም ግንባታ ሥራዎችን መሠረት ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸው እነዚህ ማሻሻያዎች የሚተገበሩት በሰው ኃይል በመሆኑ የሰው ኃይል ግንባታ ትኩረት ከተሰጣቸው የለውጥ ሥራዎች መካከል የሚመደብ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በዚሁ መሠረት ፍርድ ቤቶቹ ተግባራዊ ያደረጉትን ለውጥ መሠረት በማድረግ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቅልጥፍና፣ ጥራት እና ውጤታማነታቸው የተረጋገጠ እንዲሆን ከፍርድ ቤቶች የሰው ኃይል ምን እንደሚጠበቅ በቂ ግንዛቤ መያዝ፣ ለአንድ ዓላማ በጋራ መስራት እንዲሁም በቁርጠኝነት መፈጸም ከእያንዳንዱ ሠራተኛ የሚጠበቅ ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

ለሶስት ቀናት በሚቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ላይ በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሰው ሀብት ሥራ አመራር ደንብ እና መመሪያዎች፣ ተቋማዊ ለውጥ፣ የሥራ ባህል እና ሥነምግባር፤ አዲሱ የህዝብ አገልግሎት አቀራረብ ስልት ለተሻለ ተቋማዊ አፈጻጸም እንዲሁም የዲጂታላይዜሽን ጉዞ በፌደራል ፍርድ ቤቶች በሚሉ ርዕሶች ላይ ሥልጠና የሚሰጥ ይሆናል፡፡

ስልጠናው በተከታታይ 7 ዙሮች የሚሰጥ ሲሆን በክልል ከተሞች የሚገኙ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ሠራተኞችን ባካተተ ሁኔታ አሁን በሥልጠናው ላልታቀፉ ሌሎች ባለሙያዎችና የስራ ሃላፊዎችን ባሳተፈ መልኩ የሚሰጥ ይሆናል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ኮሙዩኒኬሽንና ስትራቴጅያዊ አጋርነት ዳይሬክቶሬት

"የፍርድ ቤቶችን አሰራር ለማሻሻል የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች አበረታች ናቸው!"

------ቋሚ ኮሚቴው------

(ዜና ፓርላማ) ጥር 30 ቀን ፣ 2017 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፍርድ ቤቶች አሰራር ለማሻሻል የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጿል።

ቋሚ ኮሚቴው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2017 በጀት አመት የ6 ወር የስራ አፈፃፀም፣ የፍርድ ቤቶች የለውጥ ፍኖተ ካርታ ያለበትን አፈፃፀም እና ቀጣይ ስራዎችን ገምግሟል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ እፀገነት መንግሥቱ ዕቅዱና አፈፃፀሙ ከፍርድ ቤቶች የለውጥ ፍኖተ ካርታ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን በጥንካሬ የሚታይ መሆኑንና ችግሮችን ለመፍታት የሚደረገው ጥረት ምን ያህል ትኩረት ተሰጥቶ እና የዕቅድ አካል ተደርጎ እየተሰራ እንደሆነ የሚያሳይ ነው ብለዋል።

አያይዘውም ለለውጥ ፍኖተ ካርታ የህግ ማሻሻያ ምሰሶ መሆኑን ጠቁመው ለአሰራር ማነቆ የሆኑ አሰራሮችን ማሻሻል ይገባል ብለዋል።

ችሎቶችን በቴክኖሎጂ ለማገዝ፣ ባለድርሻ አካላትን ለማሳተፍ፣ የባለ ጉዳይ አያያዝ፣ የፍርድ ቤቶችን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ፣ በተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮችን ወደ ህዝብ ለማድረስ እና ምቹ የስራ አካባቢን ለመፍጠር የተሰሩ ስራዎች አበረታች እና በጥንካሬ የሚጠቀሱ ስራዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።

መስሪያ ቤቱ ለብልሹ አሰራር ተጋለጭ የሆኑ ጉዳዮችን በየጊዜው ትኩረት ሰጥቶ እየፈተሹ፣ እያረሙና እያስተካከሉ መሄድ ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን፤ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ችግሩን መፍታት እንደሚቻልም አስገንዝበዋል።

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ኢሳ ቦሩ በበኩላቸው የስድስት ወራት አፈፃፀም እያንዳንዱ ስራ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።

ከዚህ በፊት በፍ/ቤቶች ያልታዩ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት፣ ፍርድ ቤቶችን ለመቀየር የተጀመረው ስራ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።

ከሰፋፊ የኔትዎርክ ዝርጋታ፣ ከስማርት ኮርት ሩም ሲስተም፣ ድምፅን ወደ ፅሁፍ የመቀየር ቴክኖሎጂዎች በስራ ላይ መዋላቸው ጥሩ ጅምሮ መሆናቸውን እና በሚፈለገው ፍጥነት መሄድ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

አያይዘውም ከፌዴራል ፍርድ ቤት ጀምሮ በአካል በመስክ ምልከታ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማየት መቻሉን እና ቀሪ ስራዎች በመኖራቸው ወደ ተጨባጭ ስራ መገባት እንዳለበትም አመላክተዋል።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በበኩላቸው የሩብ አመቱ ዕቅድ የአምስት አመቱ ስትራቴጅክ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ የህዝብ አመኔታ ያተረፈ የዳኝነት አካል ሆኖ ለመገኘትና ለማሳካት ስድስት ግቦችንና የትኩረት መስኮችን ለይተው በዝርዝር አቅርበዋል።

ከቅንጅት አሰራር ጋር ተያይዞ ከፌዴራል የዳኝነት እና የፍትህ አካላት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር ጥሩ መሆኑን ለአብነትም ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ጋር አንድ የቪዲዮ ኮንፍረንስ እና የኢፋይል አገልግሎት መስጫ ሞዴል ማዕከል መከፈቱንና ወደ ሌሎች የሚስፋፋ መሆኑን ገልጸዋል።

ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያየዘም ተገልጋዮች የሚያነሷቸውን ቅሬታዎች በመቀበል የማሻሻያ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አመላክተዋል።

የቋሚ ኮሚቴው አባላት በበኩላቸው በግማሽ አመት ዕቅድ አፈፃፀም ላይ ተመስረተው የተለያዩ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን ያቀረቡ ሲሆን በሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ምንጭ: የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሳባ የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልጋቸውም በማለት የወሰናቸው መዝገቦች ዝርዝር
ተ.ቁ መዝገብ ቁ.
1. 5096/12
2. 5215/12
3. 5279/12
4. 5333/13
5. 5355/13
6. 5357/13
7. 5359/13
8. 5457/13
9. 5466/13
10. 5516/13
11. 5517/13
12. 5912/13
13. 5960/13
14. 6015/13
15. 6564/14
16. 6579/14
17. 6582/14
18. 6595/14
19. 6597/14
20. 6603/14
21. 6608/14
22. 6614/14
23. 6660/14
24. 6907/14
25. 6921/14
26. 7854/15
27. 8732/16
28. 8798/16
29. 8866/16
30. 8908/16
31. 9008/16
32. 9032/17
33. 9037/17
34. 9131/17
35. 9282/17
36. 9283/17
37. 9371/17
38. 9372/17

*ማስታወሻ*
1. ቁጥራቸው የቅርብ ጊዜ የሆኑት ጉዳዮች ቀድመው የታዩበት ምክንያት በጉባዔው መመሪያ መሰረት ቅድሚያ አግኝተው ምርመራቸው የተጠናቀቀ (የወንጀል፣ የአካል ጉዳተኞች፣ የአሰሪና ሰራተኛ፣ ከፍ/ቤት ሪፈራል የተላኩ፣ የታገዱ መዝገቦች) መሆናቸውን እየገለፅን ከዚያ ውጭ ያሉት ግን እንደ አመጣጥ ቅደም ተከተላቸው የተስተናገዱ ናቸው፡፡
2. ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች የውሳኔ ግልባጭ ከሁለት ሳምንት በኋላ በጉባዔው ፅ/ቤት በመቅረብ ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ

ጉባዔው በ43 ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ፣ አቅጣጫ እና የውሳኔ ሐሳብ ሰጠ።
--------------------------------------------------------------------------

ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም (አዲስ አበባ)
የኢፌዴሪ የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሐሙስ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ጉባዔ በንዑስ አጣሪ ጉባዔ እና በአጣሪ ጉባዔ ጽ/ቤቱ የሕግ ተመራማሪዎች ተገቢው ምርመራ እና ጥናት ተደርጎባቸው ለውሳኔ ከቀረቡለት የሕገ መንግሥት የትርጉም አቤቱታዎች መካከል 43 በሚሆኑት ላይ ውሳኔ፣ የውሳኔ ሐሳብ እና አቅጣጫ ሰጥቷል።

በዚህም 38 የሚሆኑት የትርጉም አቤቱታዎች ሕገ መንግሥታዊ ጥሰት አልተፈፀመባቸውም በሚል እንዲዘጉ ጉባዔው ውሳኔ የሰጠ ሲሆን በ3 አቤቱታዎች ላይ ተጨማሪ ማጣራት ተደርጎባቸው ለውሳኔ እንዲቀርቡ እንዲሁም በአንድ አቤቱታ ላይ ደግሞ ተጠሪ ምላሽ እንዲሰጥበት ጉባዔው አዝዟል።

በዕለቱ ጉባዔው ከተወያዬባቸው አቤቱታዎች መካከልም በመ/ቁ 6124/.. የተመዘገበ አቤቱታ ሕገ መንግሥታዊ ጥሰት ተፈፅሞበታል በሚል የውሳኔ ሐሳቡ ለፌዴሬሽን ም/ቤት እንዲላክ የውሳኔ ሐሳብ ተሰጥቶበታል።

የኢፌዴሪ የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ

ምክር ቤቱ የፍትህና የህግ ኢንስቲትዩት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጸደቀ
-----------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥር 29 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ18ኛ መደበኛ ስብሰባው የፌደራል የፍትህና ህግ ኢንስቲትዩት እንደገና ለማቋቋም የቀረበው ረቂቅ አዋጅ መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ እጸገነት መንግስቱ ሪፖርት እና የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡

ሰብሳቢዋ አያይዘውም፤ ረቂቅ አዋጁ ነጻና ገለልተኛ የሆነ እና አደረጃጀቱ ከተጽዕኖ የጸዳ የህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት በማቋቋም ጠንካራ የዳኝነትና የፍትህ ተቋማት ለመፍጠር የህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ተጠሪነት ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማዕከል ያደረገ ጥናትና ምርምር በማድረግ የዳኝነትና የፍትህ ስርዓቱ ማዘመን እንዲሁም ህጎችን ከወቅታዊ የዓለም እና የሀገሪቱ የዕድገት ደረጃ ጋር እንዲጣጣሙ ለማድረግ ጠንካራ የህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የተከበሩ ወ/ሮ እጸገነት መንግስቱ አክለው አብራርተዋል፡፡

የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው፤ ኢንስቲትዩቱ እንደገና መቋቋሙ ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ታአማኒና ቀልጠፋ አገልግሎት ለመስጠት ያሚያስችሉ የህግ ሙያተኞች ለማፍራት እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡

ቀድመ ስልጠና የሚለው በስራ ላይ ሂደት የፍትህ ባለሙያዎችን እያበቁ መሄድ ቢቻል፣ በየቦታው የስልጠና መዕከል ከመክፈት ይልቅ በማዕከል በማድረግ ዘርፉን መደገፍ ቢቻል የሚል አስተያየት የምክር ቤት አባላት ሰጥተዋል፡፡

ከቅድመ ስልጠና ጋር በተያያዘ የፍትህ ባለሙያዎች ዳኞች እና ዐቃቢያን ህጎች በሰዎች ንብረት እና ህይወት ላይ ለሚወስኑት ውሳኔ በእውቅትና እና በክህሎት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የቅድመ ስልጠና አስፈላጊ መሆኑን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘካርያስ ኤርኮላ አስረድተዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ በህግ ጉዳዮች ጥናት እና ምርምር በማድረግ እና ፖሊሲዎችን በማመንጨት እንደሀገር በፍትህ ሥርዓቱ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለማረም እንደሚያግዝ አቶ ዘካርያስ ኤርኮላ አስረድተዋል፡፡

ኢንስቲትዩት ለፍትህ ሚኒስቴር ከነበረበት ተጠሪነት ወጥቶ፤ በአሁኑ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተጠሪ መሆኑን በረቂቅ አዋጁ ተመላክቷል፡፡

ምክር ቤቱ የፍትህና ህግ ኢንስቲትዩት እንደገና ለማቋቋም የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1369/2017 አድርጎ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

ምንጭ: የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ድምጽ ቅጂ ቅጽ 6 ክፍል 1
https://www.youtube.com/watch?v=hw0SEyyYG1c
በፍርድ ቤቱ ዩቲዩብ ቻናል http://www.youtube.com/@federalsupremecourtethiopi570 ወይም በቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/fscethiopiaPR ላይ በመግባት ይከታተሉ፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኮሚዩኒኬሽንና ስትራቴጂያዊ አጋርነት ዳይሬክቶሬት

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሳባ የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልጋቸውም በማለት የወሰናቸው መዝገቦች ዝርዝር
ተ.ቁ መዝገብ ቁ.
1. 5035/12
2. 5371/13
3. 5748/13
4. 5759/13
5. 6390/14
6. 6424/14
7. 6425/14
8. 6443/14
9. 6453/14
10. 6454/14
11. 6462/14
12. 6463/14
13. 6464/14
14. 6465/14
15. 6543/14
16. 6544/14
17. 6546/14
18. 6547/14
19. 6548/14
20. 6551/14
21. 6554/14
22. 6568/14
23. 6572/14
24. 6573/14
25. 6574/14
26. 6575/14
27. 8608/16
28. 9211/17

*ማስታወሻ*
1. ቁጥራቸው የቅርብ ጊዜ የሆኑት ጉዳዮች ቀድመው የታዩበት ምክንያት በጉባዔው መመሪያ መሰረት ቅድሚያ አግኝተው ምርመራቸው የተጠናቀቀ (የወንጀል፣ የአካል ጉዳተኞች፣ የአሰሪና ሰራተኛ፣ ከፍ/ቤት ሪፈራል የተላኩ፣ የታገዱ መዝገቦች) መሆናቸውን እየገለፅን ከዚያ ውጭ ያሉት ግን እንደ አመጣጥ ቅደም ተከተላቸው የተስተናገዱ ናቸው፡፡
2. ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች የውሳኔ ግልባጭ ከሁለት ሳምንት በኋላ በጉባዔው ፅ/ቤት በመቅረብ ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ

አጣሪ ጉባዔው በ31 የትርጉም አቤቱታዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እና አቅጣጫ ሰጠ።
----------------------------------------------------------------------
አርብ ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም (አዲስ አበባ)

የኢፌዴሪ የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሐሙስ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ጉባዔ በንዑስ አጣሪ ጉባዔ እና በአጣሪ ጉባዔ ጽ/ቤቱ የሕግ ተመራማሪዎች ተገቢው ምርመራ እና ማጣራት ተደርጎባቸው ከቀረቡለት የሕገ መንግሥት የትርጉም አቤቱታዎች መካከል 31 በሚሆኑት ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እና አቅጣጫ ሰጥቷል።

በዕለቱ ጉባዔው ከተወያዬባቸው 31የሕገ መንግሥት ትርጉም አቤቱታዎች መካከል በቁጥር 28 የሚሆኑት ሕገ መንግሥታዊ ጥሰት አልተፈፀመባቸውም ሲል እንዲዘጉ ወስኗል።
በሌላ በኩል በ2 የሕገ መንግሥት ትርጉም አቤቱታዎች ላይ ደግሞ ተጨማሪ ማጣራት ተደርጎባቸው በአንደኛው ላይም የባለሙያ አስተያዬት ተሰብስቦ በድጋሚ ለውሳኔ እንዲቀርቡ ጉባዔው አቅጣጫ አስቀምጧል።

ጉባዔው በዕለቱ ከተወያዬባቸው ጉዳዮች መካከል በመዝገብ ቁጥር 8588/16 በተጠቀሰ በአንድ የሕገ መንግሥት የትርጉም አቤቱታ ላይ ደግሞ ሕገ መንግሥታዊ ጥሰት ተፈፅሟል በሚል የውሳኔ ሐሳቡ ለፌዴሬሽን ም/ቤት እንዲላክ ወስኗል።

የኢፌዴሪ የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ

የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበር የስራ አመራር ቦርድ አባላት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት ጉብኝት አደረጉ
********
የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበር የስራ አመራር ቦርድ አባላት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀን 22/05/2017 ዓ.ም በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡

የቦርድ አባላቱ በቆይታቸው የፌደራል ፍርድ ቤቶችን አጠቃላይ የሪፎርም ስራዎች ላይ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን በተለይም ፍርድ ቤቶቹ በቴክኖሎጂ ረገድ እየሰሩባቸው ያሉ የለውጥ ተግባራት ላይ ሰፊ ውይይት እንዲሁም ጉብኝት አድርገዋል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት አመራር አባላቱ ፍርድ ቤቱ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ለማየት መምጣታቸውን አድንቀው ፍርድ ቤቶች አሰራራቸውን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የጀመሩትን ጥረት ከማገዝ አንፃር የዳያስፖራው ማህበረሰብ በቴክኖሎጂ እና እውቀት ሽግግር ተሳትፎ ማድረግ የሚጠበቅበት ከመሆኑም በላይ እንደ ፍርድ ቤት ተገልጋይ በዳኝነት ስርዓቱ ያሉ ጠንካራም ሆነ ደካማ ጎኖች ላይ ግልፅ ግንዛቤ ሊኖረው ስለሚገባ ጉብኝቱ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የማህበሩ የስራ አመራር ቦርድ አባላት በበኩላቸው የፌደራል ፍርድ ቤቶች በቴክኖሎጂ ረገድ እያሳዩ ያለውን ለውጥ አድንቀው የዳኝነት ስርዓቱ መጠናከር እና መሻሻል ሁሉንም አካል የሚጠቅም በመሆኑ የተቋሙን ትክክለኛ ገፅታ ከማስገንዘብ እና አዎንታዊ ለውጦችን ከማጠናከር አንፃር የዲያስፖራው ማህበረሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ መደገፍ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽንና ስትራቴጅያዊ አጋርነት ዳይሬክቶሬት