ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም - አዲስ አበባ
**
“ገብርየ ቢሞት ተተካ ባልቻ፤
መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ፡፡” (ኢትዮጵያዊያን)
የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጂም አባላትና ሰራተኞች የአድዋ ድል ሙዚዬምን ጎበኙ፡፡ በፒያሳ እምብርት ላይ የሚገኘው ይህ ሙዚየም የአድዋ ጦርነት ታሪክን ከመነሻው እስከ ፍፃሜው ያሉውን ሂደት በዝርዝር የሚያስቃኝ ነው፡፡ የነገስታቱ አልባሳት፣ ቁሳቁስና የጦር መሳሪያዎች አሁንም ድረስ ከነ ግርማ ሞገሳቸው በሙዚዬሙ ይገኛሉ፡፡ ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳን ጨምሮ፣ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች በጉብኝቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል፡፡