Everest Youth Academy (Kara Kore Branch) @everestyouthacademykara Channel on Telegram

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

@everestyouthacademykara


Everest Youth Academy (Kara Kore Branch) (English)

Welcome to Everest Youth Academy (Kara Kore Branch), a Telegram channel dedicated to empowering and inspiring young individuals to reach their full potential. Our channel aims to provide a supportive community where youth can engage in meaningful discussions, participate in educational activities, and connect with like-minded individuals. Who is it? Everest Youth Academy (Kara Kore Branch) is a branch of Everest Youth Academy, a renowned institution that focuses on holistic development and academic excellence for young students. The Kara Kore Branch specifically caters to youth in the Kara Kore region, offering a range of educational programs and resources to help them succeed in their personal and academic lives. What is it? Our Telegram channel serves as a platform for young people to access valuable resources, participate in interactive workshops, and engage in discussions on various topics such as leadership, career development, and personal growth. With a team of experienced mentors and educators, Everest Youth Academy (Kara Kore Branch) is dedicated to nurturing the next generation of leaders and change-makers. Join us on Everest Youth Academy (Kara Kore Branch) and be a part of a supportive community that encourages growth, learning, and collaboration. Together, we can empower young individuals to climb the metaphorical Everest of success and make a positive impact on the world. We look forward to welcoming you to our channel and supporting you on your journey to greatness.

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

12 Feb, 15:27


ዜና ስፖርት ( ቀን ፡ 05/06/2017)

"ስፖርት ለአንድነትና ለእድገት"
በሚል መሪ ቃልበኮልፌ ቀራንዮ ክፍለከተማ ወረዳ 03 ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በወረዳው ስር በሚገኙ የመንግስትና የግል ት/ቤቶች መካከል ከጥር 27/2017 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የጥሎ ማለፍ ውድድር ኤቨረስት ዩዝ አካዳሚ እና  ካራቆሬ ት/ቤት ቅዳሜ ለሚካሄደው የፍጻሜ  የዋንጫ ውድድር አልፈዋል።

በውድድሩ
ኤቨረስት ዩዝ አካዳሚ ሙሴ ት/ቤትን 6 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ያሸነፈ ሲሆን ካራቆሬ ት/ቤት ከሀምዛ ት/ቤት በጫወታ 1 ለ 1 አቻ በመውጣታቸው በመለያ ምት ካራቆሬ ት/ቤት 4 ለ 3 በማሸነፍ ለፍጻሜ ደርሷል።

ስፓርታዊ ውድድሩን አቶ ታከለ ደሳለው የኮልፌ ወረዳ 03 ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ የካራቆሬ ቅ/አ/አ/መካከለኛ ደረጃ ትቤት ርዕሳነ መምህራን ፣መምህራንና የወረዳው ስፓርት ጽ/ቤት አስተባባሪዎች ተማሪዎች ተገኝተው ተከታትለዋል።

ስለሆነም ቅዳሜ 8/6/17ዓ.ም ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ጥሎ ማለፉን ባጠናቀቁት በካራቆሬ እና ኤቨረስት ትምህርት ቤት መካከል በሚደረግ የዋንጫ ውድድር ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

12 Feb, 13:44


እንኳን ደስ አላችሁ
በዛሬው እለት በወረዳ 3 በሚገኙ የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች መካከል እየተካሄደ ባለው የእግር ኳስ ውድድር ት/ቤታችን ተጋጣሚው የነበረውን ሙሴ ትምህርት ቤትን 6 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለዋንጫ ሲያልፍ ጎሎቹን
አቤም ጌቱ 2 ጎሎችን ሲያስቆጥር የተቀሩትን አራት ጎሎች፣ነቢል ያሲን ፣ ቅዱስ መስፍን ፣አብደላ ኡስማን እና ወሊድ አህመድ አስቆጥረዋል።

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

07 Feb, 09:53


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 3/2017 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

ጥር 30/2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 3/2017 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

01 Feb, 18:10


https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSemXtdkY9PINBQVHxI-idM_FWTrCqXM4Y1MNyYJydrMuo2r4w/viewform?usp=sharing
ለወላጆች በሙሉ
በቅድሚያ የከበረ ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረስ እያልን የ 2017 ዓ.ም የመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት የደንበኞችን የእርካታ መጠን ለመለካት መጠይቅ ያዘጋጀን ሲሆን እናንተም ይህንን አውቃችሁ መጠይቆቹን በጥንቃቄ እንድትሞሉ በአክብሮት ለማሳሰብ እንወዳለን ።

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

01 Feb, 08:09


https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScQRh2bi9QsoVfVbFpHcx6ep9M6L6sobGh8V3xEUyXtW8oScQ/viewform?usp=sharing
ለተማሪዎች በሙሉ
በቅድሚያ ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረስ እያልን የ 2017 ዓ.ም የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት የመማር ማስተማር ሂደቱን እና ተማሪዎቻችን በት/ቤቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት አስተያየት እንድትሰጡ መጠይቅ ያዘጋጀን ሲሆን ከላይ ያለውን ማሰፈንጠሪያ በመጠቀም አስተያየታችሁን እንድትሰጡ በአክብሮት ለማሳሰብ እንወዳለን ።

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

24 Jan, 12:30


🇪🇹Happy International Day of Education! 🇪🇹
Today, we celebrate the power of education to transform lives and build a better future. A quality education opens doors to opportunities, encourages innovation, and promotes peace and inclusion.🏳🏳🏳

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

23 Jan, 18:02


🔤ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና

አዘጋጅ
👉አራዳ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት

⛔️መንፈቀ አመት
👉የመጀመሪያ መንፈቀ አመት 

⭐️የትምህርት አይነት
👉ሁሉም

⭐️አመት 👉2017

⭐️ክፍል 👉8️⃣

0️⃣ለሌሎች ማጋራት አንርሳ

🔠🔠🔠🔤 🔠🔠🔠
ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇👇
❤️❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/dam76

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

23 Jan, 18:02


🥰6️⃣ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና

አዘጋጅ
👉🔤🔤🔤🔤🔤ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት

⛔️መንፈቀ አመት
👉የመጀመሪያ መንፈቀ አመት 

⭐️የትምህርት አይነት
👉ሁሉም

⭐️አመት 👉2017

⭐️ክፍል 👉6️⃣

📘ለሌሎች ማጋራት አንርሳ‼️

🔤🔤🔤🔤 🔤🔤🔤
ቻናላችን ይህ ነው
🫴🫴🫴🫴🫴🫴
https://t.me/dam76

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

21 Jan, 14:56


የ6ኛ ክፍል የክወና እና እይታ ጥበባት አሳይመንት

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

05 Jan, 13:17


#Update

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ጥር 6/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ስለሆነም ምዝገባ ያላጠናቀቃችሁ ተማሪዎች ከቀነ ገደቡ አስቀድማችሁ እንድታጠናቅቁ አገልግሎቱ አሳስቧል።

አገልግሎቱ የ2017 ዓ.ም ፈተናዎች ይዘትን በተመለከተ ባስተላለፈው መልዕክት፤ የሀገር አቀፍ 12ኛ ክፍል ፈተና በአጠቃላይ ከ 9-12ኛ ክፍሎች እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከ7-8ኛ ክፍሎች እንደሚሸፍን ገልጿል።

ተማሪዎች በተማሩበት የክፍል ደረጀ የተማሪ መጽሐፍን መሠረት አድርገው ሊዘጋጁ እንደሚገባ አገልግሎቱ ጠቁሟል።

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

04 Jan, 15:59


የተከበሩ የትምህርት ቤታችን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ እንዳልካቸው አየለ ፣የትምህርት ቤታችን መምህራን እና የአስተዳደር ስራተኞች ትምህርት ቤታችን በዛሬው እለት በክፍለ ከተማ ደረጃ በተካሄደው የአሸናፊዎች አሽናፊ የጥያቄ እና መልስ ውድድር በሁለቱም የክፍል ደረጃዎች ባስመዘገብነው አመርቂ ውጤት የተሰማንን ደስታ ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው ለዚህ ውጤት መሳካት ላበረከታችሁት አስተዋፅኦ ምስጋናችን የላቀ ነው🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏ይህ ውጤት እንዲቀጥል የሁላችንንም የጋራ ጥረት ስለሚያስፈልግ ጥረታችን ቀጣይነት እንዲኖረው ለማሳሰብ እወዳለሁኝ።💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

04 Jan, 15:46


የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድሮች በተማሪዎችና በትምህርት ቤቶች መካከል ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ለማጠናከር እንሚያግዙ ተገለፀ።

ቀን ታህሳስ 26/2017ዓ.ም

የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅህፈት ቤት የ6ኛ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት የአሸናፊዎች አሸናፊ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በአየር ጤና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አካሒዷል።

ውድድሩን በንግግር የከፈቱት አቶ ገነነ ዘውዴ የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅህፈት ቤት ኃላፊ ውድድሩ ከትምህርት ቤቶችና በወረዳዎች ሲካሔድ መቆየቱን አስታውሰው የዛሬው የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር የአሸናፊዎች አሸናፊ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ፅህፈት ቤቱ የሚያዘጋጀው ጥያቄና መልስ ውድድሮች በትምህርት ቤቶች የእርስ በእርስ መቀራረብንና መተጋገዝን የሚያጎለብት እንዲሁም በተማሪዎችና በትምህርት ቤቶች ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ለማጠናከር፣ለሀገር አቀፍ እንዲሁም ክልል አቀፍ ፈተናዎች ተማሪዎችን የሚያዘጋጅ መሆኑን ገልፀው ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖራቸው ፉክክር ውስጥ እንዲገቡ እንደሚያግዝ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልፀዋል

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

04 Jan, 15:46


በዕለቱ ከ1ኛ-3ኛ ለወጡ ተማሪዎች በክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ በአቶ ገነነ ዘውዴ እና ግብዣ በተደረገላቸው እንግዶች የዋንጫ ፣የአጋዥ መጽሐፍት እና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።በዚህም መሰረት፣

#በስድስተኛ ክፍል በተደረገ የጥያቄና መልስ ውድድር አሸናፊዎች፦

1ኛ.ሰልዋ ዘይኔ ከኤቨረስት ት/ ቤት
2ኛ.ዮሴፍ መላኩ ከትጋት ቁ.2 ት/ቤት
3ኛ.ዘካሪያስ ሙሉጌታ ከቀራኒዮ መ.ቁ

# በስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች በተደረገው ጥያቄና መልስ ውድድር አሸናፊወች፦

1ኛ.የአብቃል ተስፋዬ ከጆይንት ቪዥን ት/ቤት
2ኛ.ሰኝ ጫላ ከኤቨረስት ት/ቤት
3ኛ.ኢብቲሳም አ/በር  ከአል-አፊያ ት/ቤት

#በ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መካከል በተደረገ ጥያቄ እና መልስ ወድድር አሸናፊወች፦

1ኛ.ኢያቄም ምትኩ ከቤተሰብ ት/ቤትበ12
2ኛ.ያብስራ አሸናፊ ከሬኔሰንስ ት/ቤት
3ኛ.ራያን ስላሐዲን ከቢኮሎስ

#በ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መካከል በተደረገ ጥያቄ እና መልስ ወድድር አሸናፊወች፦

1ኛ.በዕምነት ገዛኸኝ ከቤተሰብ ት/ቤት
2ኛ.ስማቸው ማልልኝ ከአየር ጤና ት/ቤት
3ኛ.ኑሃሚን ሰሙንጉስ ከሬኔሰንስ ት/ቤት  ተሸላሚ ሆነዋል።

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

31 Dec, 15:57


ተማሪዎች ትምህርት ቤት ለመመዝገብ የፋይዳ  ምዝገባ  አስገዳጅ  ቅድመ ሁኔታ ይሆናል ተባለ


በከተማው ውስጥ ባሉ ትምህርት ቤቶች ሁሉ ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የፋይዳ ምዝገባ እንደ ልደት ምዝገባ አስገዳጅ እንደሚሆንም ተገልጿል።


ይህ የተገለፀው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲና የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ከከተማው ትምህርት ቢሮ ጋር በመሆን  የፋይዳ እና የልደት ምዝገባን በተመለከተ ውይይት ባከናወነበት ወቅት ነው።

በዚህም በቀጣይ ግዚያት የፋይዳ ዘመቻ ምዝገባ ስራ በይፋ በግል ትምህርት ቤቶቹ በሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስተባባሪነት ይከናወናል ተብሏል።

የፋይዳ ምዝገባ እንደ ልደት ምዝገባ ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ቅበላ የምዘገባ ቅድሙ ሁኔታ እንደሚሆን ተነግሯል።

ለዓለም አሰፋ

ታኀሣሥ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

30 Dec, 14:40


📚 ⭕️ የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተናን ይመለከታል

የ2017 ዓ.ም የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና መረጃ ለ6ኛ ና 8ኛ  ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች

1️⃣ የ6ኛ ክፍል በተመለከተ

✍️ በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-

👉 አማርኛ
👉 English
👉 ሒሳብ
👉 አካ/ሳይንስ  እና
👉 ግብረ-ገብ

✍️ የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና የሚዘጋጀው ከ6ኛ ክፋል first semester (5ኛ ክፍልን first semester  ይጨምራል)

2⃣የ8ኛ ክፍል በተመለከተ

የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ሞዴል ፈተና የሚዘጋጀው ከ8ኛ ክፍል  first semester   (ከ7ኛ ክፋልን first semester ይጨምራል)

✍️ በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-

👉 English
👉 አማርኛ
👉 Mathematics
👉 Social Studies
👉 General Science
👉 Citizenship

📚 በመሆኑም የፈተና ወቅት እየተቃረበ በመሆኑ ተማሪዎች በዚህ መረጃ መሰረት በአግባቡ ማጥናት ይጠበቅባቸዋል::

⭕️ በዚህ መረጃ መሠረት  ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

28 Dec, 08:44


የ 2017 የህፃናት ፓርላማ አንደኛ አመት አንደኛ መደበኛ ስብሰባ

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

28 Dec, 05:29


አስደሳች ዜና :-

በቀን 18/04/2017 በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ትምህርት ጽ/ቤት በካራ ቆሬ ክላስተር ማዕከል አዘጋጅነት የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ።

በውድድሩ በወረዳው የሚገኙ 14 የመንግስትና የግል ት/ቤቶች የተሳተፉ ሲሆን
የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታከለ ደሳለው ባስተላለፉት መልዕክት "ውድድሩ በየደረጃው የሚቀጥል መሆኑን እና በዛሬው የጥያቄ እና መልስ ውድድር የተሻለ ውጤት የሚያመጡ ተማሪዎች በቀጣይ በክ/ከተማ ደረጃም በሚደረገው ውድድርም ወረዳውን በመወከል የሚወዳደሩ በመሆኑ ራሳቸውን ከወዲሁ ማዘጋጀት አለባቸው።" ብለዋል።

በመጨረሻም በውድድሩ በ6ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል በተደረገው ውድድር
1ኛ . ኤቨረስት ት/ቤት
2ኛ . ሀምዛ ት/ቤት
3ኛ . ኑር አፍሪካ ት/ቤት በመሆን ያጠናቀቁ ሲሆኑ

በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል በተደረገው ውድድር ደግሞ
1ኛ .ኤቨረስት ት/ቤት
2ኛ .ካራቆሬ ት/ቤት
3ኛ .ኑር አፍሪካ ት/ቤት በመሆን ሲያጠናቅቀቁ በእለቱም ለአሸናፊ ተማሪዎችና ትምህርትቤቶች እንደየደረጃቸው የዋንጫ፣ ሰርተፍኬትና አጋዥ መጽሀፍት ሽልማት ከጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ታከለ ደሳለው፤ ከካራ ክላስተር ማዕከሉ አስተባባሪ ከአቶ አብዱራዛቅ ኢሳና ከተለያዩ የትምህርት ስራ አመራሮች እጅ ተቀብለዋል ።

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

20 Dec, 07:59


🆕እንግሊዝኛ ቋንቋ ማሳደጊያ ፖርታል ጥቆማ
👉🏼የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና ተማሪዎችን እንግሊዘኛ ቋንቋን ለማሻሻል የሚያግዝ ፖርታል አዘጋጅቷል፡፡ 
🤏🏼ፖርታሉ ከቅድመ አንደኛ ጀምሮ በሁሉም የክፍል ደረጃዎች የተዘጋጁ ሁኔታና አውድን ያገነዘቡ እያዝናኑ የሚያስተሩ ግልጽና በቀላሉ ለመረዳት የሚያስችሉ  በድምጽ በጽሁፍና በምስል የተቀናበሩና የእንግሊዝኛ ቋንቋን የሚያሻሽሉ መረጃዎች ለማግኘት ያስችላል።
🫴🏼ፖርታሉን ለመጠቀም ኢንተርኔት ማብራት የሚያስፈልግ ቢሆንም  ኢንተርኔቱ ገንዘብ የማይቆርጥ ሲሆን  በስማርት ስልክ፣ ስማርት ቴሌቪዥን፣ በታብሌትና በኮምፒውተር በማንኛውም ብሮዘር መጠቀም ይቻላል፡፡
🫳🏼ፖርታሉን https://elearn-english.moe.gov.et በመንካት መክፈትና መጠቀም ይችላል፡፡

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

21 Nov, 16:02


አውስትራሊያ ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ማህበራዊ ሚዲያዎችን እንዳይጠቀሙ አገደች
On Nov 21, 2024 48

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) አውስትራሊያ ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ማህበራዊ ሚዲያዎችን እንዳይጠቀሙ የሚያግደውን ህግ በፓርላማ አፅድቃለች፡፡

በውሳኔው መሰረትም በሀገሪቱ እድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች የቲክቶክ፣ ስናፕ ቻት፣ ፌስቡክ፣ ሬዲት፣ ትዊተር (ኤክስ) እና ኢንስታግራም አካውንት መክፈት አይችሉም፡፡

ከላይ የተጠቀሱት የማህበራዊ ትስስር ገፆች ታዳጊዎች አካውንት እንዲከፍቱ የሚፈቅዱ ከሆኑ 50 ሚሊየን የአውስትራሊያ ዶላር ቅጣት እንደሚጠብቃቸው መንግስት አስጠንቅቋል።

የአውስትራሊያ መንግስት ኮሙኒኬሽን ሚኒስትር ሚሸል ሮውላንድ÷ በሀገሪቱ ሰፊ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ድጋፍ ያገኘው ይህ ውሳኔ የታዳጊዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በአውስትራሊያ እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ታዳጊዎች ጎጂ ይዘት ያላቸውን ጉዳዮች በማህበራዊ ትስስር ገፆች ሲመለከቱ እንደነበር አስታውሰው÷ ክልከላው ታዳጊዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚደርስባቸውን ጫና ይቀንሳል ብለዋል፡፡

ከአውስትራሊያ አስቀድማ ስፔን ባለፈው ሰኔ ወር ከ14 እስከ 16 ዓመት ያሉ ታዳጊዎች ማህበራዊ ሚዲያዎችን እንዳይጠቀሙ መከልከሏ ይታወቃል።

በአሜሪካም በተወሰኑ ግዛቶች ላይ ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል መባሉን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

20 Nov, 05:03


የክፍለ ከተማው አስተዳደር የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በአል ምክንያት በማድረግ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር አካሂዷል።

ህዳር 10/2017 ዓ.ም

የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ከክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት በመተባበር "ሀገራዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን 19ኛውን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ በአማረኛ እና በአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር አካሄደዋል።

ውድድሩ ያስጀመሩት የተከበሩ አቶ ሚልኪያስ ገበየሁ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ምክትል ዋና አፈ ጉባኤ እንደተናገሩት የዛሬ ተማሪዎች የነገ ሀገር ተረካቢዎች በመሆናችሁ የፌደራል ስርዓት፣ ህገመንግስትና ህገመንግስታዊነት ዙሪያ የተዘጋጀው ጥያቄና መልስ በአግባቡ ተረድታችሁ በትምህርት ቤታችሁ ለመተግበር ያስችላችኋል ብለዋል።

የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ በበኩላቸው ትምህርት ቤቶች የትንሿ ኢትዮጵያ መገለጫ በመሆናቸው የበአሉ መከበር እህትማማችነትና ወንድማማችነትን ለማጠናከር ይረዳል ያሉ ሲሆን በእለቱ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች የምስክር ወረቀት በማበርከት በቀጣይም መልካም ውጤት እንዲገጥማቸው አበረታቷቸዋል።

የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ የተዘጋጀው የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በትምህርትቤቶችና በወረዳ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን አሸናፊዎቹ በቀጣይ በከተማ ለሚዘጋጀው ውድድር ክፍለ ከተማው ወክሎው እንደሚወዳደሩ ማወቅ ተችለዋል።

🙏🏾ኮልፌ ኮሙኒኬሽን

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

19 Nov, 10:24


19ኛ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን አስመለክቶ በክፍለ ከተማ ደረጃ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በ21 ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው ውድድር ወረዳ 03 ትምህርት ጽ/ቤት ወክሎ የተወዳደረው ቃልዓብ ደረጀ ከኤቨረስት አካዳሚ 3 ኛ በመውጣት ወረዳውንም ትምህርት ቤቱን በማስጠራት ተሸላሚ ሁኗል
እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን 👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

15 Nov, 15:19


በሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል በተደረገ የጥያቄና መልስ ውድድር ተማሪ አቤም ጌቱ የመለያ ጥያቄን ጨምሮ ከቀረቡለት ሰባት ጥያቄዎች ሰባቱንም በመመለስ ከ7D ክፍል አንደኛ ወቶ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

31 Oct, 14:57


በዛሬው እለት በ 8ኛ ክፍሎች መካከል በተካሄደው የጥያቄ እና መልስ ውድድር ተማሪ ሶልያና ሙሴ 1ኛ በመውጣት ወደሚቀጥለው ዙር ልታልፍ ችላለች

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

30 Oct, 13:31


የአካባቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ክበብ

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

30 Oct, 11:09


በ 2017 ዓ.ም ለሚደረገው የትምህርት ቤታቸን የህፃናት ፓርላማ የምርጫ ቅስቀሳ

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

30 Oct, 10:40


ለ 6ኛ እና ለ 8ኛ ክፍሎች የመጀመሪያውን ሞዴል ፈተና አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጠ

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

17 Oct, 14:54


ወቅታዊ ጉንፋንና ጉንፋን መሰል የመተፈንሻ አካላት ህመምን አሰመልክቶ የተሰጠ መግለጫ‼️

የጉንፋን ሕመም በተፈጥሮ የላይኛውን የመተንፈሻ የሰውነት ክፍሎች ማለትም አፍንጫን፣ ጎሮሮንና የአየር መተላለፊያ ባንቧን የሚያጠቃ ተላላፊ ሕመም ነዉ።

ሪኖ ቫይረስ ለጉንፉን መከሰት ዋና ምክንያት ሲሆን፣ ኮሮና፣ ኢንፍሉዌንዛ፣ ፓራ ኢንፍሉዌንዛ፣ አር ኤስ ቪ(RSV) ቫይረሶች ደግሞ ለጉንፉን መሰል ህመሞች መከሰት ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸዉ። ከተጠቀሱት ቫይረሶችም ለጉንፋን ሕመም መከሰት 50 በመቶ ድርሻውን የሚይዘው ሪኖ ቫይረስ ነው፡፡ በደረቅ ነፋሳማ ወቅት የአፍንጫ የውስጠኛው ስስ ሽፋን “ሙከስ መምብሬን” ስለሚደርቅ የጉንፋን ሕመም እና ተላላፊነቱ ይጨምራል፡፡ የክረምት ወራት ወይም የዝናብ ወቅት ማብቃቱን ተከትሎ መስከረምን ጨምሮ በጥቅምትና ህዳር ወራት እንደዚህ አይነት ጉንፋን መሰል ህመም የሚጠበቅ ነው፡፡

ሕመሙ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈውም በቫይረሱ የተጠቃ ሰው በሚያስልበት ወይም በሚያስነጥስበት ጊዜ እንደሆነና በተጨማሪም ሰዎች ቫይረሱ ያረፈበትን የበር እጀታ፣ ጠረጴዛ ወይም በሕመምተኛው የተነካካንን ሰው እጅ ከነኩ በኋላ አፋቸውንና አፍንጫቸውን ሲነካኩ ቫይረሱ ለመተላለፍ በሚፈጠርለት ምቹ ሁኔታ ነው።

የጉንፋን ሕመም የመጀመሪያ ምልክቱ ከመጀመሩ አንድ ቀን በፊት ተላላፊ ሊሆን ይችላል፤ ሕመሙ ከጀመረ ከ 5 እስከ 10 ባሉት ቀናት ደግሞ ሕመምተኛው ቫይረሱን ያስተላልፋል። ህመሙ አብዛኛዉን ጊዜ እስከ 2 ሳምንት ሊቆይ ይችላል። ምልክቶቹም እንደ የአፍንጫ ፈሳሽ መብዛት፣ ሳል፣ ትኩሳት፣ ራስ ምታትና ጉሮሮን መከርከር፣ ማስነጠስ፣ አይን ማሳከክ እና መቅላት፣ ማስታወክ፣ ከፍ ሲልም የትንፋሽ ማጠር፣ ከፍተኛ ድካምና የምግብ ፍላጎት መቀነስ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ።

በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከ2003 ዓ ም ጀምሮ የእንፍሉዌንዛ እና መሰል የመተንፈሻ አካላት በሽታዎች ቅኝትና ምላሽ በሁሉም ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች እየተሰራ ይገኛል። ከመስከረም ወር ጀምሮ መሰል ህመም ተሰምቷቸው ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ናሙና ከሰጡት ታካሚዎች ውስጥ አር ኤስ ቪ የተገኘባቸዉ ቁጥር የመጨመር ሁኔታ ያሳያል፡፡ በዚሁ ወቅት የተከሰተው ጉንፋን መሰል ህመም (አር ኤስ ቪ) በተለይ በህጻናት ላይ በብዛት የተከሰተ ሲሆን ለዚህም ወቅቱ ትምህርት ቤት የተከፈተበት በመሆኑ ለበሽታው መስፋፋት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ባለፈዉ 1 ወር ዉስጥ ተመርምረዉ አር ኤስ ቪ ከተገኘባቸዉ ታካሚዎች መካከል 84% ያክሉ እድሜያቸዉ ከ5 አመት በታች ነዉ። እንደዚሁም ባለፈዉ ሳምንት ለአር ኤስ ቪ ከተመረመሩት 81 ናሙናዎች 49 (60.5%) ያህሉ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።

አስፈላጊው ጥንቃቄ ካልተደረገ በሽታው የመዛመት እድሉ ከፍ ሊል እንደሚችል፤ በተለይ ቀዳሚ ተጎጅ ሊሆኑ የሚችሉ እንደ ህጻናትና አረጋውያን ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች አና ተጓዳኝ የጤና ችግር እንደነ አስም፣ የስኳር በሽታ፣ ካንሰር እና ሌሎች ሥር የሰደዱ በሽታዎች ያሉባቸው ሕሙማን ከፍተኛ ጥንቃቄ ልናደርግላቸው እና ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ አስፈላጊዉን ምርመራና ህክምና ሊያደርጉ ይገባል1፡፡ በተጨማሪም የጉንፋን ሕመም የጆሮ ኢንፌክሽን እና የሳንባ ምች ሕመምን ጨምሮ ለተለያዩ ሕመሞች ተጋላጭ ሊያደርግ ይችላል፡፡

ጉንፋን መሰል በሽታን ከምንከላከልባቸው መንገዶች መካከልም የእጅ ንጽህናን መጠበቅ፣ ሰዎች በተሰበሰቡበት ቦታ የአፍና አፍንጫ ጭምብል(ማስክ) በማድረግና በዕለት ኑሯችን የምንጠቀምባቸውን በከባቢዎቻችን የሚገኙ ቁሳቁሶችን ማጽዳት እና የብዙሃን ማጓጓዣ ትራንስፖርት ላይ መስኮቶችን በመክፈት በቂ የአየር ዝዉዉር እንዲኖር በማድረግ የበሽታዉን የመተላለፍ ዕድል መቀነስ ይቻላል፡፡ ስለዚህ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃዎችን እንዲወስድና ጠንከር ያለ የበሽታው ምልክት የሚታይበት ሰው በፍጥነት በአቅራቢያው ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን የህክምና ምክር አና ዕርዳታ ማግኘት አለበት፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በ952 እና 8335 ነጻ የስልክ መስመር መደወል የሚቻል መሆኑን እያስታወስን ሕብረተሰቡ ሊከተላቸው የሚያስፈልጉ የጥንቃቄ እርምጃዎችን አስመልክቶ ዝርዝር መግለጫ እና መረጃዎችን በየጊዜው የምንሰጥ መሆኑን እንገልጻለን።

የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ጥቅምት 7 ቀን 2017 ዓ.ም

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

16 Oct, 12:26


Once, in a telephone interview, a radio host asked Ratan Tata, "What has been the happiest moment in your life?" He replied:

"I have gone through four different stages of happiness in life, and in the end, I realized what true happiness is.

The first stage was when I earned a lot of money and wealth. But I didn’t find the happiness I desired there. Then came the second stage. At that point, I began collecting valuable things. I soon realized that this happiness too was only temporary. After that, I moved into the third stage. Here, I started several new projects. Soon, I was in charge of distributing 95% of oil in India and Africa. I also became the owner of the largest steel factory in India and Asia. But still, I couldn’t find the happiness I dreamed of.

Finally, the fourth stage arrived. It was like this: Once, a friend of mine told me that we should buy and donate wheelchairs for 200 disabled children. I did so immediately. He then insisted that I personally attend the event to distribute them. I agreed. I personally handed over the wheelchairs to all 200 children. As they accepted them, I saw a certain wild light of joy on their faces. It was as if they had all just arrived at a scenic picnic spot. That day, I understood what true happiness was.

As I was about to leave, one child clung tightly to my legs. No matter how hard I tried, I couldn’t move. Finally, I asked him, 'Do you want something else?' Looking directly at my face, the child said, 'I want to remember your face well, so that tomorrow, when we meet in heaven, I can thank you again.'

So, dear friends, we must realize that true happiness doesn’t lie in money, power, or fame. It lies in embracing others and including them in our lives."

Tribute — Ratan Naval Tata 🙏🏼🌹

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

14 Oct, 08:44


17ኛው የሰንደቅ አላማ ቀን ሰንደቅ አላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን ፣ ለሉአላዊነታችን እና ለኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪ ቃል በትምህርት ቤታችን የተከበረ ሲሆን በእለቱም በመምህር መሳይ ፣ በተማሪ ናርዶስ ተሰማ እና በተማሪ ቃለአብ ደረጄ የተለያዩ ፅሁፎች ሊቀርቡ ችለዋል

Everest Youth Academy (Kara Kore Branch)

12 Oct, 11:04


ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ በድምቀት እንደሚከበር የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታውቋል።

(ጥቅምት 2/2017 ዓ.ም) “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን ፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!” በሚል መሪ ሀሳብ የ2017 ዓ.ም 17ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን የሚከበር መሆኑን የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታውቋል።

በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት መሪነት 17ኛው የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል በፌደራል ፣ በክልሎችና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች ከተሞች በሚገኙ የመንግስት ተቋማት ፣ በትምህርት ቤቶችና በመከላከያ ሰራዊት ካምፖች ውስጥ በተመሳሳይ ሰዓት 4፡30 የሚሰቀል መሆኑ ተገልጻል፡፡