Últimas publicaciones de ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር (@ethiopianorthodoxtewahdomezmurs) en Telegram

Publicaciones de Telegram de ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን

🚶‍♂️እንኳን ደህና መጡ👋

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶችን መዝሙሮች ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።

👥 ✅ @yemezmurgetemoche

📝ለማንኛውንም ሀሳብናአስተያየት
✅ @KIDAN_MEHRET_ENATEbot

ለማስታወቂያ ስራዎች ✅ @gutaitagu16

የቻናላችን ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን
34,681 Suscriptores
3,183 Fotos
223 Videos
Última Actualización 06.03.2025 17:05

El contenido más reciente compartido por ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር en Telegram

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

14 Feb, 11:38

3,396

#የካቲት_8

አንድ አምላክ በሆነ በ #አብ በ #ወልድ በ #መንፈስ_ቅዱስ ስም
የካቲት ስምንት በዚህች ዕለት #ጌታችን_አምላካችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ከከበረ ልደቱ ከአርባ ቀኖች በኋላ ወደቤተ መቅደስ የገባበት ሆነ፣ የከበረች እመቤት #አመተ_ክርስቶስ አረፈች፣ ከአሴር ወገን የሆነች የፋኑኤል ልጅ #ነቢዪት_ሐና አረፈች፣ በትሩፋቱ ፍጹም የሆነ ታላቅ አረጋዊ የገዳመ ሲሐቱ #ቅዱስ_ኤልያስ አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ስምዖን_አረጋዊ

የካቲት ስምንት በዚህች ዕለት #ጌታችን_አምላካችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ከከበረ ልደቱ ከአርባ ቀኖች በኋላ ወደቤተ መቅደስ የገባበት ሆነ።

ለዚህ ምሥጢር አገልጋይ የሆነ ጻድቁ ቅዱስ ዮሴፍና የወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል #ማርያም የክብር ባለቤት እርሱ በእስራኤል ሕዝብ ላይ የሠራውን ሕግ ይፈጽሙ ዘንድ መሥዋዕትም ሊአቀርቡ መጡ። ጻድቅ ሰው ስሞዖን ካህንም ሕፃኑን ተቀብሎ አቀፈው።

እንዲህም ሆነ አባታችን አዳም ከተፈጠረ በአምስት ሽህ ሁለት መቶ ዓመት አሸናፊ የተባለ በጥሊሞስ በነገሠ ጊዜ የአይሁድ ወገኖች ከሥልጣኑ በታች ነበሩ። ወደ ኢየሩሳሌምም ልኮ ከሊቃውንቶቻቸው፡ ከአዋቂዎች መምህራኖቻቸው ሰብዓ ሰዎችን መርጦ ወደርሱ ወሰዳቸው የኦሪትንም መጻሕፍት ከዕብራይስጥ ቋንቋ ወደ ጽርዕ ቋንቋ የተረጕሙ ዘንድ አዘዛቸው። ይህም የሆነ በ #እግዚአብሔር ፈቃድ ነው ከአይሁድ ሕጉና ሥርዓቱ እንደሚፈልስና በዓለም ሁሉ ላሉ ለክርስቲያን ወገን ይሆን ዘንድ አለውና።

ዳግመኛም ሁለት ሁለት እያደረጉ እንዲለዩአቸው አዘዘ እነርሱ ሰባ ሁለት ስለሆኑ ሠላሳ ስድስት ድንኳን አዘጋጅቶ በዚያ ሁለት ሁለቱን አኖራቸው ተገናኝተው በመስማማት የሚጽፉትን የሕጉን ቃል እንዳይለውጡ በላያቸው ጠባቂዎችን አኖረ። እነርሱ በተንኰል ሥራ የታወቁ ናቸውና።

ለዚህም ለስሞዖን ይተረጒም ዘንድ የነቢዩ ኢሳይያስ መጽሐፍ ደረሰውና እነሆ ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም #አማኑኤል ትለዋለች ከሚለው ደረሰ። ይህንንም ቃል ይጽፍ ዘንድ ፈራ ይህ እንዴት ይሆናል ብሎ ንጉሥ እንደሚዘብትበት ቃሉንም እንደማይቀበለው አስቧልና እርሱ ራሱም እንዴት ሊሆን ይችላል ብሎ ተጠራጠረ። ይህንንም ሲያስብ እንቅልፍ መጣበትና አንቀላፋ የ #እግዚአብሔርም መልአክ ተገልጦ የተጠራጠርከውን ከድንግል የሚወለደውን እስከምታየውና እስከምትታቀፈው ሞትን አትቀምስም አለው ከዚህም በኋላ #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ እስከተወለደና በዚች ዕለት ወደ ቤተ መቅደስ እስከ አስገቡት ድረስ ስምዖን ሦስት መቶ ዓመት ኖረ ሕፃኑን #ጌታችንንም በታቀፈው ጊዜ ታውረው የነበሩ ዓይኖቹ ተገለጡ ሁለመናውም ሐዲስ ሆነ #መንፈስ_ቅዱስም የምትጠብቀው የነበረ ሕፃን ይህ ነው ብሎ ነግሮታልና።

#እግዚአብሔርንም አመሰገነው። እንዲህም አለ ባርያህን በሰላም አሰናብተው በአንተ ምክንያት በዚህ በኃላፊው ዓለም ሕይወት ታሥሬ ኑሬአለሁና እነሆ አሁን መጥተህ አየሁህ ወደ ዘላለም ሕይወት እሔድ ዘንድ አሰናብተኝ ዓይኖቼ ትድግናህን አይተዋልና። በወገኖችህ ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ለአሕዛብ ብርሃንን ለወገኖችህ እስራኤልም ክብርን ትገልጥ ዘንድ።

እመቤታችንን እናቱ ድንግል #ማርያምንም እንዲህ አላት ይህ ልጅሽ ከእስራኤል ውስጥ ለብዙዎች ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው በሚፈረድባቸውም ገንዘብ ለምልክት የተዘጋጀ ነው።

ዳግመኛም በመከራው ጊዜ በልቧ የሚያድርባትን ኅዘን አስረዳት እንዲህም አላት በአንቺ ግን በልብሽ የሚከፋፍል ፍላፃ ይገባል ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ። በዚያም የከበረ ወንጌል ያወሳት የፋኑኤል ልጅ ነቢዪት ሐና ነበረች እርሷም ስለርሱ ትንቢት ተናገረች #እግዚአብሔርን እያመሰገነች እርሱ ከሰይጣን ባርነት የሚያድናቸው መድኃኒት እንደሆነ ነገረቻቸው።

#ለጌታችንና_ለመድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ከቸር #አባቱና ከ #መንፈስ_ቅዱስ ክብር ምስጋና ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን!!

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_ሐና_ነቢዪት

በዚህም ዕለት ከአሴር ወገን የሆነች የፋኑኤል ልጅ ነቢዪት ሐና አረፈች፡፡ የእርሷም ዘመኗ አልፎ ነበር በድንግልና ከኖረች በኋላ ከባሏ ጋር ሰባት ዓመት ኖረች። ሰማንያ አራት ዓመት ፈት ሁና ኖረች በጾምና በጸሎትም እያገለገለች ቀንም ሌትም ከምኲራብ አትወጣም ነበር።

#ጌታችን_ኢየሱስን ከተወለደ በኋላ በአርባ ቀን ወደ ቤተ መቅደስ በአስገቡት ጊዜ በዚያን ሰዓት ተነሥታ አመነች #እግዚአብሔርንም አመሰገነችው። የኢየሩሳሌምን ድኅነት ተስፋ ለሚያደርጉ ሁሉ ስለርሱ ነገረች። ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈች።

#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ሐና ጸሎት ይማረን በረከቷም ይደርብን ለዘላለሙ አሜን።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_አመተ_ክርስቶስ

በዚህችም ቀን የከበረች እመቤት አመተ #ክርስቶስ አረፈች ሁለቱም አገልጋዮቿ። ይችም ቅድስት ከቍስጥንጥንያ አገር ሰዎች ውስጥ ናት ከንጉሥ መሳፍንቶችም ባል ነበራት እርሱም በጐልማሳነቱ ሙቶ ዕድሜዋ ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆናት ፈት አረጋት።

ከጥቂትም ቀን በኋላ ከመንግሥት ታላላቆች ከሆኑት ውስጥ አንድ ሰው በኃይል ወስዶ ሊአገባት ፈለገ እርሷም ጽኑ ደዌ አለብኝ እስከምድን ጠብቀኝ አለችውና ከዚህ በኋላ ገንዘቧን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች በተነች ወንዶችና ሴቶች ባሮቿን ነጻ አወጣች ሁለት ሴቶች ባሮቿንም ከእርሷ ጋር ይዛ ማንም ሳያያት በሌሊት ወጣች ከኰረብታ በታች ጥልቅ ከሆነ ቦታ ውስጥ ወዳለ ዋሻ ገብታ በዚያ ዐሥራ አንድ ዓመት ኖረች በየዕለቱም ከዕፀዋት ፍሬ አዕዋፍ እያመጡላት ከአገልጋዮቿ ጋር ትመገባለች።

ከዚህም በኋላ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘመን ከጸሐፊዎች አንዱ እንዲህ አለ ግብር እሰበስብ ዘንድ ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ሔድኩ ወደ አንድ ገዳምም ደረስኩ መነኰሳቱና አበ ምኔቱም ተቀበሉኝ እርስበርሳችንም እጅ ተነሣሥተን ተቀመጥን ከዚያ በየአይነቱ ፍሬ ያላቸው ዛፎች አሉ አዕዋፍም ቅርንጫፉን ከፍሬው ጋር እየቆረጡ ይበራሉ እነርሱ ራሳቸው አይበሉም።

እኔም አይቼ አደነቅሁ መነኰሳቱንም ይህ ሥራ ምንድን ነው አልኳቸው እነርሱም እንዲህ ሲያደርጉ ዐሥራ አንድ ዓመት ነው የሚሆነውን ግን አናውቅም አሉኝ እኔስ በተራራ ውስጥ ለሚኖር መነኰሳት የሚወስዱ ይመስለኛል አልኳቸው።

ይህንንም ስናገር ቊራ መጥቶ ቅርንጫፍን ቆርጦ ከፍሬው ጋር ይዞ በረረ ሥራውን አውቅ ዘንድ ከአበ ምኔቱ ጋር ተከተልኩት የሚገባበትንም አየን ወደዚያም ቦታ ደርሰን ደንጋይ ጣልን ክርስቲያኖች ከሆናችሁ አትግደሉን የሚል ቃልን ሰማን እናንተ ከወዴት ናችሁ አልናቸው እኛን ለማየት ከፈለጋችሁ ራቁታችንን ስለሆን ሦስት ልብሶችን ጣሉልን አሉን እኛም ልብሶችን ጣልንላቸውና ወደርሳቸው ጭንቅ በሆነች መንገድ ወረድን በደረስንም ጊዜ ተቀበሉን እርስበርሳችንም እጅ ተነሣሥተን አንዲቱ ከእኛ ጋር ተቀመጠች ሁለቱ ግን በፊቷ ቆሙ።

አበ ምኔቱም እናቴና እመቤቴ ሆይ ከወዴት ነሽ ወደዚህስ አወጣጥሽ እንዴት ነው አላት እርሷም ሥራዋን ሁሉ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ነገረችው አበ ምኔቱም የምትፈቅጂ ከሆነ ከገዳም ምግብ እናምጣላችሁና ከእናንተ ጋር በአንድነት እንመገብ አላት። እርሷም ወደዚህ ከመጣን ቅዱስ ቁርባንን አልተቀበልንምና የ #ክርስቶስን #ቅዱስ_ሥጋና #ክብር_ደም አምጥቶ እንዲአቀብለን ቄስን እዘዝልን አለችው።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

09 Feb, 04:00

1,331

እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።

ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት (ራዕይ 1፥10) ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።


መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን 🙏🙏🙏
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

08 Feb, 18:44

2,767

የሰንበት ትርጉም በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች:-

፩. እረፍት
እግዚአብሔር ዓለምን በስድስት ቀናት ከፈጠረ በኋላ በሰባተኛው ቀን ነቀለ (ዘፍጥረት 2:2-3)። ይህ ሰንበት እንደ እረፍት፣ እንደ የአምላክ እድል ማስታወሻ፣ እና እርሱን በማመስገን የሚታወስበት ቀን እንዲሆን ያስተምራል።

፪. በቃል ኪዳን ምልክት
ሙሴ ለእስራኤል ሕዝብ እንዲከተሉት ያዘዛቸው ከአሥርቱ ትእዛዛት አንዱ ሰንበትን ማክበር ነው (ዘፀአት 20:8-11)። ይህ ሕዝቡ እግዚአብሔርን እንደ ፈጣሪ እና ነጻ አውጪ እንዲያከብሩ የሚያስታውሳቸው ቀን ነበር።

፫. የመንፈስ ቃል ትርጉም
በአዲስ ኪዳን፣ ኢየሱስ እንደተናገረው፣ *"ሰንበት ለሰው ተደርጎ ነው የተሠራው፣ ሰውም ለሰንበት አይደለም"* (ማርቆስ 2:27)። ይህ የሰንበት እረፍት ለሰው ልጅ ሥነ ልቦናዊ፣ አካላዊ፣ እና መንፈሳዊ ማደሪያ እንደሆነ ያሳያል።

ሰንበትን እንዴት እንደሚከበር
ሀ. ከሥጋዊ ሥራ መቆጠብ
እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል፣ በዚህ ቀን ከዕለታዊ ሥራዎች (ለምሳሌ፣ ንግድ፣ ግንባታ፣ ወዘተ) ተቆጥበን እግዚአብሔርን በጸሎት፣ በምስጋና፣ እና በአንድነት እንከብረው።

ለ. የመንፈስ ልማድ ማድረግ
- ቤተ ክርስቲያን ይጎበኙ።
- ቤተሰብ ወይም ጓደኞች ጋር የመጽሐፍ ቅዱስን ጥናት ያካሂዱ።
- ለሌሎች በመርዳት እና በምህረት ይተዋወቁ።

፫. ራስዎን በእረፍት ይውሰዱ
እግዚአብሔር ሰንበትን ለሰው ልጅ የሰጠው እንደ ምህረት ነው። የሰውነትዎን፣ አእምሮዎን፣ እና ነፍስዎን ለማሳደድ ይህን ቀን ይጠቀሙበት።

ጸሎት ለሰንበት
"አባቴ ሰማያዊ፣ በዚህ ቅዱስ ቀን ላይ ስለ እረፍትህና ስለ ምህረትህ አመሰግንሃለሁ። እንደ አብርሃም፣ ሙሴ፣ እና የእስራኤል ሕዝብ ያከበሩህት ሁሉ፣ እኔም ልቤን ለአንተ አቀርባለሁ። በዚህ ቀን ሥጋዊ ሥራዬን በማቆም፣ መንፈሴን እንድታስተካክልለት እለምንሃለሁ። የሰንበትን በረከት በሕይወቴ ላይ አሳድረኝ፤ እረፍቴ በአንተ የተሞላ እንዲሆን። አሜን።"

ማስታወሻ
ሰንበት የሚያስተላልፈው በሰላም፣ በምስጋና፣ እና በእግዚአብሔር ጋር በሚደረግ ግኑኝነት ነው። እርሱን በመከተል የሰው ልጅ የተሻለ ኑሮ፣ የበለጠ ዕረፍት፣ እና የማያበቃ ተስፋ እንደሚያገኝ አምናለሁ።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

08 Feb, 18:23

2,216

"በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

እንኳን #ለዘመነ_አስተርዮ_አምስተኛ_ሳምንት #ለዕለተ_እሑድ_ሰንበት #እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

#የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፫ "#ኢየሩሳሌም_ትቤ_ተወልደ_ንጉሥየ_ወአምላኪየ ኢየሩሳሌም ትቤ በቤተ ልሔም ተወልደ በተድላ መለኮት፤(ኢ) #አክሊለ_ሰማዕታት_ሠያሜ_ካህናት፤ (ኢ) ዘይሴብሕዎ ሐራ ሰማይ በማኅበረ ቅዱሳን (ኢ) #አጥመቆ_ዮሐንስ_ለኢየሱስ_በፈለገ_ዮርዳኖስ ኢየሩሳሌም ትቤ ኢየሩሳሌም አእኰተቶ"። ትርጉም፦ #ኢየሩሳሌም_አለች_ንጉሤና_አምላኬ የሆነ ተወለደ ኢየሩሳሌም አለች በመለኮት ተድላ በቤተ ልሔም ተወለደ #የሰማዕታት_አክሊል_የካህናት_ሻሚያቸው የቅዱሳን ማኅበር የሰማይ ሠራዊት የሚያመሰግኑት በዮርዳኖስ ወራጅ #የቅዱስ_ዮሐንስ_ኢየሱስን አጠመቀው ኢየሩሳሌም አመሰገነችው አለች። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

08 Feb, 18:21

1,702

††† እንኳን ለታላቁ ገዳማዊ አባ ጳውሊ እና ለጻድቁ አባ ለንጊኖስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ታላቁ ቅዱስ ጳውሊ †††

††† በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ "ታላቁ /ዐቢይ/ THE GREAT" የሚል ስም የሚሰጣቸው አባቶች የተለዩ ናቸው። አንድም እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን የሠሩ ናቸው። በሌላ በኩል ደግሞ በተመሳሳይ ስም ከሚጠሩ ሌሎች ቅዱሳን እንለይበታለን።

ገዳማዊ ሕይወት ጥንቱ ብሉይ ኪዳን ነው። በቀዳሚነትም በደብር ቅዱስ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ደቂቀ ሴት እንደ ጀመሩት ይታመናል። ሕይወቱ በጐላ በተረዳ መንገድ የታየው ግን በታላቁ ጻድቅ ሄኖክ ከዚያም በቅዱሱ ካህን መልከ ጼዴቅ አማካኝነት ነው።

ቀጥሎም እነ ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ እነ ኤልሳዕ ደቀ መዝሙሩ ኑረውበታል። በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ሙሉ ሕይወቱን በገዳም (በበርሃ) ያሳለፈው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅድሚያውን ይይዛል።

ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና መድኃኒታችን ክርስቶስ በገዳመ ቆረንቶስ ለአርባ ቀናት በትሕርምት ኑሮ ገዳማዊ ሕይወትን ቀድሷል፤ አስተምሯል። በዘመነ ስብከቱም ያድርባት የነበረችው የደብረ ዘይቷ በዓቱ (ኤሌዎን ዋሻ) በራሷ ለዚህ ሕይወት ትልቅ ማሳያ ናት።

ከጌታ ዕርገት በኋላም ክርስቲያኖቹ የዓለም ሁካታ ሲሰለቻቸው አንድም በንጹሕና በተሸከፈ ልቡና ለፈጣሪያቸው መገዛትን ሲሹ ከከተማ ወጣ እያሉ ይኖሩ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ። አኗኗራቸውም በቡድንም በነጠላም ሊሆን ይችላል። ዋናው ነገር ግን በጾምና በጸሎት መትጋታቸው ነው። ይህም ሲያያዝ እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ደረሰ። በዚህ ዘመን ግን አባ ጳውሊ የሚባል ንጹሕ ክርስቲያን ይህንን ሕይወት ወደ ሌላ ደረጃ ከፍ አደረገው። ለሰማንያ ዓመታት ሰው ሳያይ ተጋድሎ "የባሕታውያን አባት" ተባለ። ደንብ ያለው ተባሕትዎም ጀመረ።

ይህ ከሆነ ከሃያ ዓመታት በኋላ ደግሞ አባ እንጦንስ የሚባሉ ደግ ክርስቲያን ይህንን ገዳማዊ ሕይወት በሌላ መንገድ አጣፈጡት። በቅዱስ ሚካኤል አመንኳሽነት ገዳማዊ ሕይወት በምንኩስና ተቃኘ። ስለዚህም አባ እንጦንስ የመነኮሳት አባት ተባሉ።

እርሳቸውም ሕይወቱን ለማስፋፋት ከተለያዩ አሕጉር ደቀ መዛሙርትን እየተቀበሉ አመንኩሰዋል። ቅዱሳን የአባ እንጦንስ ልጆችም ወደየ ሃገራቸው ተመልሰው ሕይወቱን በተግባር አሳይተው ገዳማዊነትን አስፋፍተዋል።

አንድ ቀን ቅዱስ እንጦንስ (የመነኮሳት ሁሉ አባት) እንዲህ ሲል አሰበ። "በውኑ በበርሃ ለበርካታ ዘመናት በመኖር ከእኔ የሚቀድም (የሚበልጥ) ሰው ይኖር ይሆን?"
ይህንን ሃሳቡን ገና ሳይጨርሰው ቅዱስ ሚካኤል ወደ እርሱ ዘንድ ደረሰ።

"እንጦንስ ሆይ! ከእኔ የሚቀድም የበርሃ ሰው ይኖር ይሆን ብለህ አስበሃል። በእርግጥም ከአንተ ሃያ ዓመታትን ቀድሞ ወደ በርሃ የገባ፣ በቅድስናው ፈጣሪውን ያስደሰተ፣ ዓለም ከነ ክብሯ የእግሩን መረገጫ ያህል እንኳ የማትመጥነው በጸሎቱና በምልጇው ዓለም የምትጠበቅለት ሞገስን የተሞላ አንድ ሰው በበርሃ ስላለ ሒድና ተመልከተው።" ብሎት ተሠወረው።

ቅዱስ እንጦንስም ከሰማው ነገር የተነሳ እየተደነቀ ተነሳ። እርሱ ካለበት በርሃ በራቀ መንገድም ለቀናት ተጉዞ አንድ በዓት (ዋሻ) በር ላይ ደረሰ። በበሩ አካባቢ የሰውና የአራዊት ኮቴ ተመልክቶ በሩን ጸፋ (ቆፈቆፈ)። በውስጥ ያለው አረጋዊ ሰው ግን ትልቅ ድንጋይ ገልብጦ በሩን አጠበቀው። ለሰማንያ ዓመታት ሰውን አይቶ አያውቅምና ሰይጣን ሊያታልለኝ መጥቷል ብሎ አስቧል። ቅዱስ እንጦንስ ግን "ኃሠሥኩ እርከብ ጐድጐድኩ ይትረኃው ሊተ - ሽቻለሁና ላግኝ፤ ደጅ መትቻለሁና ይከፈትልኝ።" ሲል አሰምቶ ተናገረ።

ቅዱሱ ገዳማዊም ሰው መሆኑን ሲያውቅ በሩን ከፈተለትና ወደ ዋሻው አስገባው። መንፈሳዊ ሰላምታንም ተለዋወጡ። ሲመሽም ቅዱስ እንጦንስ ሽማግሌውን ገዳማዊ "ስምህ ማን ነው?" ቢለው "ስሜን ካላወክ ለምን መጣህ?" ሲል መለሰለት።

ያን ጊዜ ቅዱስ እንጦንስ ቀና ብሎ ሰማይን ሲመለከት ምሥጢር ተገለጠለትና "ቅዱስ ጳውሊ ሆይ! ከአንተ ጋር ያገናኘኝ ፈጣሪ ይክበር፤ ይመስገን።" ሲል ፈጣሪውን ባረከ። ቅዱስ ጳውሊም መልሶ (በጸጋ አውቆት) "አባ እንጦንስ ሆይ! እንኳን ደህና መጣህ።" አለው። ሁለቱም ደስ ብሏቸው ፈጣሪያቸውን እያመሰገኑ ተጨዋወቱ።

ቤተ ክርስቲያን ለሁሉም ዓይነት የቅድስና ሕይወት የመጀመሪያ የምትላቸው አላት። ለምሳሌ፦
የመጀመሪያው ሐዋርያ ቅዱስ እንድርያስ፣
የመጀመሪያው ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ፣
የመጀመሪያው ባሕታዊ (ገዳማዊ) ቅዱስ ጳውሊ እና የመጀመሪያው መነኮስ ቅዱስ እንጦንስን ማንሳት እንችላለን።

ቅዱስ ጳውሊ የተወለደው በሰሜናዊ ግብጽ በእስክንድርያ ከተማ ሲሆን ዘመኑም ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነው። ወላጆቹ ባለጸጐች ነበሩ። ቅዱሱንና ታላቅ ወንድሙን አባ ጴጥሮስን ወልደዋል። ሁለቱ ክርስቲያን ወንድማማቾች ገና ወጣት ሳሉ ወላጆቻቸው ሞቱባቸው። ሃዘናቸውን ፈጽመው ሃብት ሲካፈሉ ግን መስማማት አልቻሉም።

ምክንያቱ ደግሞ ትልቁ ጴጥሮስ ደህና ደህናውን እቃ ወስዶ መናኛ መናኛውን ለትንሹ ለጳውሎስ (ጳውሊ) መስጠቱ ነበር። ስለዚህ ነገር ተካሰው ወደ ፍርድ ቤት ሲሔዱ ግን መንገድ ላይ አንድ ባለጸጋ ሙቶ ደረሱ።

ቆመው ሳሉም ቅዱስ መልአክ ሰው መስሎ ጳውሊን "ይህ ሰው ባለጸጋ ነው። በገንዘቡ የሰጠውን ፈጣሪ ሲበድልበት ኑሮ እነሆ ተሸኘ። በሰማይም አስጨናቂ ፍርድ ይጠብቀዋል።" ሲል ነገረው።

በዚያች ቅጽበት የወጣቱ ጳውሊ ሐሳብ ተለወጠ። ወደ ወንድሙ ተመልሶ "ወንድሜ ሆይ! ሁሉ ንብረት ያንተ ይሁን።" ብሎት ከአካባቢው ጠፋ። በመቃብር ሥፍራ ለሦስት ቀናት ያለ ምግብ ጸልዮ የእግዚአብሔር መልአክ ሰው ወደ ማይደርስበት በርሃ ወሰደው።

በዚያም ምንጭ ፈለቀችለት። እየጾመ ይጸልይ ይሰግድ ገባ። ሁሌ ማታ ግማሽ ሕብስት ከሰማይ እየወረደለት ቅዳሜና እሑድ መላእክት እያቆረቡት ለሰማንያ ዓመታት ኖረ። (አንዳንድ ምንጮች ግን ለዘጠና ዓመታት ይላሉ።) ከቅዱስ እንጦንስ ጋር የተገናኙትም ከዚህ በኋላ ነው።

ከቅዱስ እንጦንስ ጋር በነበራቸው የሁለት ቀናት ቆይታም ቅዱስ ጳውሊ ብዙ ትንቢቶችን ተናግሯል። በዚህች ቀን ሲያርፍም መቃብሩን አናብስቱ ቆፍረዋል። ቅዱስ እንጦንስም በክብር ቀብሮታል። ለሰማንያ ዓመታት የለበሳት የዘንባባ ልብሱም ሙት አስነስታለች።

††† ጻድቅ፣ ቡሩክ፣ ቀዳሚው ገዳማዊ፣ መላእክትን የመሰለና የባሕታውያን ሁሉ አባት ለተባለ ለቅዱስ ጳውሊ ክብር ይገባል!
አሜን 🙏🙏🙏
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

08 Feb, 18:17

1,635

²² አንዱ ከባሪያይቱ አንዱም ከጨዋይቱ የሆኑ ሁለት ልጆች ለአብርሃም እንደ ነበሩት ተጽፎአልና።
²³ ነገር ግን የባሪያይቱ ልጅ እንደ ሥጋ ተወልዶአል፥ የጨዋይቱ ግን በተስፋው ቃል ተወልዶአል።
²⁴ ይህም ነገር ምሳሌ ነው፤ እነዚህ ሴቶች እንደ ሁለቱ ኪዳኖች ናቸውና። ከደብረ ሲና የሆነችው አንዲቱ ለባርነት ልጆችን ትወልዳለች፥ እርስዋም አጋር ናት።
²⁵ ይህችም አጋር በዓረብ ምድር ያለችው ደብረ ሲና ናት፤ አሁንም ያለችውን ኢየሩሳሌምን ትመስላለች፥ ከልጆችዋ ጋር በባርነት ናትና።
²⁶ ላይኛይቱ ኢየሩሳሌም ግን በነጻነት የምትኖር ናት እርስዋም እናታችን ናት።
²⁷ አንቺ የማትወልጅ መካን፥ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ አምጠሽ የማታውቂ፥ እልል በዪና ጩኺ፤ ባል ካላቱ ይልቅ የብቸኛይቱ ልጆች በዝተዋልና ተብሎ ተጽፎአል።
²⁸ እኛም፥ ወንድሞች ሆይ፥ እንደ ይስሐቅ የተስፋ ቃል ልጆች ነን።
²⁹ ነገር ግን እንደ ሥጋ የተወለደው እንደ መንፈስ የተወለደውን በዚያን ጊዜ እንዳሳደደው ዛሬም እንዲሁ ነው።
³⁰ ነገር ግን መጽሐፍ ምን ይላል? የባሪያይቱ ልጅ ከጨዋይቱ ልጅ ጋር አይወርስምና ባሪያይቱን ከልጅዋ ጋር አውጣት።
³¹ ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጨዋይቱ ልጆች ነን እንጂ የባሪያይቱ አይደለንም።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
1ኛ ጴጥሮስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥
²-³ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።
⁴ በሰውም ወደ ተጣለ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ወደ ተመረጠና ክቡር ወደ ሆነው ወደ ሕያው ድንጋይ ወደ እርሱ እየቀረባችሁ፥
⁵ እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።
⁶ በመጽሐፍ፦ እነሆ፥ የተመረጠና የከበረን የማዕዘን ራስ ድንጋይ በጽዮን አኖራለሁ በእርሱም የሚያምን አያፍርም ተብሎ ተጽፎአልና።
⁷ እንግዲህ ክብሩ ለእናንተ ለምታምኑት ነው፤ ለማያምኑ ግን አናጢዎች የጣሉት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ የዕንቅፋትም ድንጋይ የማሰናከያም ዓለት ሆነ፤
⁸ የማያምኑ ስለ ሆኑ በቃሉ ይሰናከሉበታልና፤ ለዚህ ደግሞ የተመደቡ ናቸው።
⁹ እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ሐዋርያት 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ ሊቀ ካህናቱ ግን የሰዱቃውያን ወገን ሆነውም ከእርሱ ጋር የነበሩት ሁሉ ተነሡ ቅንዓትም ሞላባቸው።
¹⁸ በሐዋርያትም ላይ እጃቸውን ጭነው በሕዝቡ ወኅኒ ውስጥ አኖሩአቸው።
¹⁹ የጌታ መልአክ ግን በሌሊት የወኅኒውን ደጅ ከፍቶ አወጣቸውና፦
²⁰ ሂዱና ቆማችሁ የዚህን ሕይወት ቃል ሁሉ ለሕዝብ በመቅደስ ንገሩ አላቸው።
²¹ በሰሙም ጊዜ ማልደው ወደ መቅደስ ገብተው አስተማሩ። ግን ሊቀ ካህናቱና ከእርሱ ጋር የነበሩት መጥተው ሸንጎውንና የእስራኤልን ልጆች ሽማግሌዎች ሁሉ በአንድነት ጠሩ፥ ያመጡአቸውም ዘንድ ወደ ወኅኒ ላኩ።
²²-²³ ሎሌዎችም መጥተው በወኅኒው አላገኙአቸውም፤ ተመልሰውም፦ ወኅኒው በጣም በጥንቃቄ ተዘግቶ ጠባቂዎችም በደጁ ፊት ቆመው አገኘን፥ በከፈትን ጊዜ ግን በውስጡ አንድ ስንኳ አላገኘንም አሉአቸው።
²⁴ የመቅደስ አዛዥና የካህናት አለቆችም ይህን ነገር በሰሙ ጊዜ፦ እንጃ ይህ ምን ይሆን? እያሉ ስለ እነርሱ አመነቱ።
²⁵ አንድ ሰውም መጥቶ፦ እነሆ፥ በወኅኒ ያኖራችኋቸው ሰዎች እየቆሙ ሕዝቡንም እያስተማሩ በመቅደስ ናቸው ብሎ አወራላቸው።
²⁶ በዚያን ጊዜ አዛዡ ከሎሌዎች ጋር ሄዶ አመጣቸው፥ በኃይል ግን አይደለም፤ ሕዝቡ እንዳይወግሩአቸው ይፈሩ ነበርና።
²⁷ አምጥተውም በሸንጎ አቆሙአቸው።
²⁸ ሊቀ ካህናቱም፦ በዚህ ስም እንዳታስተምሩ አጥብቀን አላዘዝናችሁምን? እነሆም፥ ኢየሩሳሌምን በትምህርታችሁ ሞልታችኋል፤ የዚያንም ሰው ደም በእኛ ታመጡብን ዘንድ ታስባላችሁ ብሎ ጠየቃቸው።
²⁹ ጴጥሮስና ሐዋርያትም መልሰው አሉ፦ ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

#የካቲት_2_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበበው_የሚዜመው_የቅዳሴ_ምስባክ👇

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
"ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለ #እግዚአብሔር። ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን። እስመ አጽንዐ መናስግተ ኖኃትኪ። መዝ.147÷1-2
"እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ መዝሙር መልካም ነውና። ለአምላካችን ምስጋና ያማረ ነው። እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን ይሠራል፥ ከእስራኤልም የተበተኑትን ይሰበስባል"። መዝ.147÷1-2
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

#የካቲት_2_ቀን_የእለቱን_ወንጌል_እናንብብ📖👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ሉቃስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴² የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤
⁴³ ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር።
⁴⁴ ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለ መሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤
⁴⁵ ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።
⁴⁶ ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤
⁴⁷ የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ።
⁴⁸ ባዩትም ጊዜ ተገረሙ፥ እናቱም፦ ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው።
⁴⁹ እርሱም፦ ስለ ምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው።
⁵⁰ እነርሱም የተናገራቸውን ነገር አላስተዋሉም።
⁵¹ ከእነርሱም ጋር ወርዶ ወደ ናዝሬት መጣ፥ ይታዘዝላቸውም ነበር። እናቱም ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ ትጠብቀው ነበር።
⁵² ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
የሚቀደሰው ቅዳሴ የ #ቅዱስ_ዲዮስቆሮስ_ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ጳውሊ፣ የአባ ለንጊኖስ የዕረፍት በዓልና የቅዱስ ቶማስ ተዓምር ያደረገበት ቀን ለሁላችንም ይሁንልን።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

08 Feb, 18:17

1,816

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
#የካቲት_2_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበቡት_መልእክታት👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ገላትያ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ እናንተ ከሕግ በታች ልትኖሩ የምትወዱ፥ ሕጉን አትሰሙምን? እስኪ ንገሩኝ።
²² አንዱ ከባሪያይቱ አንዱም ከጨዋይቱ የሆኑ ሁለት ልጆች ለአብርሃም እንደ ነበሩት ተጽፎአልና።
²³ ነገር ግን የባሪያይቱ ልጅ እንደ ሥጋ ተወልዶአል፥ የጨዋይቱ ግን በተስፋው ቃል ተወልዶአል።
²⁴ ይህም ነገር ምሳሌ ነው፤ እነዚህ ሴቶች እንደ ሁለቱ ኪዳኖች ናቸውና። ከደብረ ሲና የሆነችው አንዲቱ ለባርነት ልጆችን ትወልዳለች፥ እርስዋም አጋር ናት።
²⁵ ይህችም አጋር በዓረብ ምድር ያለችው ደብረ ሲና ናት፤ አሁንም ያለችውን ኢየሩሳሌምን ትመስላለች፥ ከልጆችዋ ጋር በባርነት ናትና።
²⁶ ላይኛይቱ ኢየሩሳሌም ግን በነጻነት የምትኖር ናት እርስዋም እናታችን ናት።
²⁷ አንቺ የማትወልጅ መካን፥ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ አምጠሽ የማታውቂ፥ እልል በዪና ጩኺ፤ ባል ካላቱ ይልቅ የብቸኛይቱ ልጆች በዝተዋልና ተብሎ ተጽፎአል።
²⁸ እኛም፥ ወንድሞች ሆይ፥ እንደ ይስሐቅ የተስፋ ቃል ልጆች ነን።
²⁹ ነገር ግን እንደ ሥጋ የተወለደው እንደ መንፈስ የተወለደውን በዚያን ጊዜ እንዳሳደደው ዛሬም እንዲሁ ነው።
³⁰ ነገር ግን መጽሐፍ ምን ይላል? የባሪያይቱ ልጅ ከጨዋይቱ ልጅ ጋር አይወርስምና ባሪያይቱን ከልጅዋ ጋር አውጣት።
³¹ ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጨዋይቱ ልጆች ነን እንጂ የባሪያይቱ አይደለንም።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
1ኛ ጴጥሮስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥
²-³ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።
⁴ በሰውም ወደ ተጣለ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ወደ ተመረጠና ክቡር ወደ ሆነው ወደ ሕያው ድንጋይ ወደ እርሱ እየቀረባችሁ፥
⁵ እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።
⁶ በመጽሐፍ፦ እነሆ፥ የተመረጠና የከበረን የማዕዘን ራስ ድንጋይ በጽዮን አኖራለሁ በእርሱም የሚያምን አያፍርም ተብሎ ተጽፎአልና።
⁷ እንግዲህ ክብሩ ለእናንተ ለምታምኑት ነው፤ ለማያምኑ ግን አናጢዎች የጣሉት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ የዕንቅፋትም ድንጋይ የማሰናከያም ዓለት ሆነ፤
⁸ የማያምኑ ስለ ሆኑ በቃሉ ይሰናከሉበታልና፤ ለዚህ ደግሞ የተመደቡ ናቸው።
⁹ እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ሐዋርያት 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ ሊቀ ካህናቱ ግን የሰዱቃውያን ወገን ሆነውም ከእርሱ ጋር የነበሩት ሁሉ ተነሡ ቅንዓትም ሞላባቸው።
¹⁸ በሐዋርያትም ላይ እጃቸውን ጭነው በሕዝቡ ወኅኒ ውስጥ አኖሩአቸው።
¹⁹ የጌታ መልአክ ግን በሌሊት የወኅኒውን ደጅ ከፍቶ አወጣቸውና፦
²⁰ ሂዱና ቆማችሁ የዚህን ሕይወት ቃል ሁሉ ለሕዝብ በመቅደስ ንገሩ አላቸው።
²¹ በሰሙም ጊዜ ማልደው ወደ መቅደስ ገብተው አስተማሩ። ግን ሊቀ ካህናቱና ከእርሱ ጋር የነበሩት መጥተው ሸንጎውንና የእስራኤልን ልጆች ሽማግሌዎች ሁሉ በአንድነት ጠሩ፥ ያመጡአቸውም ዘንድ ወደ ወኅኒ ላኩ።
²²-²³ ሎሌዎችም መጥተው በወኅኒው አላገኙአቸውም፤ ተመልሰውም፦ ወኅኒው በጣም በጥንቃቄ ተዘግቶ ጠባቂዎችም በደጁ ፊት ቆመው አገኘን፥ በከፈትን ጊዜ ግን በውስጡ አንድ ስንኳ አላገኘንም አሉአቸው።
²⁴ የመቅደስ አዛዥና የካህናት አለቆችም ይህን ነገር በሰሙ ጊዜ፦ እንጃ ይህ ምን ይሆን? እያሉ ስለ እነርሱ አመነቱ።
²⁵ አንድ ሰውም መጥቶ፦ እነሆ፥ በወኅኒ ያኖራችኋቸው ሰዎች እየቆሙ ሕዝቡንም እያስተማሩ በመቅደስ ናቸው ብሎ አወራላቸው።
²⁶ በዚያን ጊዜ አዛዡ ከሎሌዎች ጋር ሄዶ አመጣቸው፥ በኃይል ግን አይደለም፤ ሕዝቡ እንዳይወግሩአቸው ይፈሩ ነበርና።
²⁷ አምጥተውም በሸንጎ አቆሙአቸው።
²⁸ ሊቀ ካህናቱም፦ በዚህ ስም እንዳታስተምሩ አጥብቀን አላዘዝናችሁምን? እነሆም፥ ኢየሩሳሌምን በትምህርታችሁ ሞልታችኋል፤ የዚያንም ሰው ደም በእኛ ታመጡብን ዘንድ ታስባላችሁ ብሎ ጠየቃቸው።
²⁹ ጴጥሮስና ሐዋርያትም መልሰው አሉ፦ ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

#የካቲት_2_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበበው_የሚዜመው_የቅዳሴ_ምስባክ👇

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
"ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለ #እግዚአብሔር። ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን። እስመ አጽንዐ መናስግተ ኖኃትኪ። መዝ.147÷1-2
"እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ መዝሙር መልካም ነውና። ለአምላካችን ምስጋና ያማረ ነው። እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን ይሠራል፥ ከእስራኤልም የተበተኑትን ይሰበስባል"። መዝ.147÷1-2
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

#የካቲት_2_ቀን_የእለቱን_ወንጌል_እናንብብ📖👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ሉቃስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴² የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤
⁴³ ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር።
⁴⁴ ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለ መሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤
⁴⁵ ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።
⁴⁶ ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤
⁴⁷ የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ።
⁴⁸ ባዩትም ጊዜ ተገረሙ፥ እናቱም፦ ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው።
⁴⁹ እርሱም፦ ስለ ምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው።
⁵⁰ እነርሱም የተናገራቸውን ነገር አላስተዋሉም።
⁵¹ ከእነርሱም ጋር ወርዶ ወደ ናዝሬት መጣ፥ ይታዘዝላቸውም ነበር። እናቱም ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ ትጠብቀው ነበር።
⁵² ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
የሚቀደሰው ቅዳሴ የ #ቅዱስ_ዲዮስቆሮስ_ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ጳውሊ፣ የአባ ለንጊኖስ የዕረፍት በዓልና የቅዱስ ቶማስ ተዓምር ያደረገበት ቀን ለሁላችንም ይሁንልን።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
#የካቲት_2_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበቡት_መልእክታት👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ገላትያ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ እናንተ ከሕግ በታች ልትኖሩ የምትወዱ፥ ሕጉን አትሰሙምን? እስኪ ንገሩኝ።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

08 Feb, 09:23

2,219

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ማይ ሽጉርቲ እና ሴሮ የሚገኙት የአቡነ እንድርያስ ኹለት ገዳማት። ከበዓለ ዕረፍታቸው ረድኤት በረከት ይክፈለን።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

02 Feb, 07:04

284

"በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

እንኳን #ለዘመነ_አስተርዮ_አራተኛ_ሳምንት ዕለተ ሰንበት (እሑድ) #እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

#የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፮ "#እሙነ_ኮነ_ልደቱ_ለመድኅኒነ_ክርስቶስ እምሰማያት ወረደ #ወእመላእክት_ተአኵተ_ወእማርያም_ተወልደ (እ)፣ በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ ወአስተርአየ ገሃደ (እ)፣ #ውእቱ_እክሊለ_ሰማዕት ውእቱ መድኀኔ ነገሥታት ኖላዊሆሙ ለአሕዛብ እሙነ ኮነ #ልደቱ_ብርሃነ_ኮነ_ምጽአቱ_ለመድኀኒነ_ክርስቶስ። ትርጉም፦ #የጌታችን _የመድኃኒታችን_የክርስቶስ_ልደት_እውነት_ነው፤ ከሰማያት ወረደ #በመላክት_ዘንድ_ተመሰገነ_ከማርያም_ተወለደ፣ እርሱም #የሰማዕታት_እክሊል_ነው፣ የነገሥታት መድኃኒት ነው የአሕዛብ እረኛቸው ነው፣ #የመድኃኒታችን_የክርስቶስ_ምጽአቱ_ብርሃነ_ልደቱ እውነት ነው"።

#ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

02 Feb, 05:41

699

ይህንን ቻናል እንዳያመልጣቹ ሁላቹም ተቀላቀሉ እናንተ ብቻ ሳትሆኑ እህት ወንድሞቻቹን እንዲሁም ጓደኞቻቹን አድ አድርጉዋቸው። ሌላ ነገር ላይ ጊዜያችን ከምናጠፋ የእግዚአብሔርን ቃል እንስማ 🙏🙏🙏🙏