Últimas Postagens de Ethiopia Insider (@ethiopiainsidernews) no Telegram

Postagens do Canal Ethiopia Insider  

Ethiopia Insider
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
15,446 Inscritos
656 Fotos
40 Vídeos
Última Atualização 09.03.2025 10:29

Canais Semelhantes

Sheger Press️️
43,794 Inscritos

O conteúdo mais recente compartilhado por Ethiopia Insider no Telegram

Ethiopia Insider

18 Feb, 20:01

7,251

የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ “ቴክኒካዊ ድርድር” በመጪው መጋቢት ወር ይቀጥላል ተባለ

የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ከፍተኛ ባለስልጣናት የተሳተፉበት የመጀመሪያው ዙር ቴክኒካዊ ድርድር ተጠናቀቀ። በቱርክ አንካራ ከተማ በተካሄደው ድርድር፤ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ እና የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ሞሐመድ ዑመር ተገኝተዋል።

በቱርክ በኩል በድርድሩ የተገኙት፤ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች በታህሳስ ወር መጀመሪያ ፊት ለፊት ከመገናኘታቸው በፊት በአዲስ አበባ እና በሞቃዲሾ ተመላልሰው ውይይቱን ያመቻቹት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሐካን ፊዳን ናቸው።

በዛሬው ድርድር ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ የሁለቱን ሀገራት ልዑካን ቡድን በተናጠል እና በጋራ ማነጋገራቸውን መስሪያ ቤታቸው አስታውቋል።

ሐካን ፊደን በተናጠል እና በጋራ በተደረጉት ውይይቶች፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ልዩነት በበረታበት ዓለም ውስጥ ቀጠናዊ ትብብር ወሳኝ ጠቀሜታዎች እንዳሉት በአጽንኦት መናገራቸውን የቱርክ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አመልክቷል።

ፊዳን በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተጀመረው ድርድር “የአፍሪካን ቀንድ መጻኢ ጊዜ ታሪካዊ ዕድል ይወክላል” በማለት ፋይዳውን ገልጸዋል።

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15146/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

18 Feb, 15:50

6,862

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን “ደካማ የሆነ አፈጻጸም አሳይቷል ብለን እናስባለን” - ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ

ቪዲዮ፦ በዛሬው ዕለት በተካሄደው የፓርላማ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ ሪፖርት ያቀረቡት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፤ ኮሚሽኑ በአዋጅ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ የምክክር፣ የአጀንዳ መለየት እና ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። እነዚህ ሂደቶች በ10 ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቃቸውንም ገልጸዋል።

እርሳቸው ይህን ቢሉም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ግን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ “ደካማ የሆነ አፈጻጸም አሳይቷል ብለን እናስባለን” ሲሉ ተደምጠዋል። እንደ ዶ/ር ደሳለኝ ሁሉ፤ ሁለት የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ ተወካዮችም በኮሚሽኑ የስራ አፈጻጸም ያላቸውን አስተያየት እና ጥያቄ ሰንዝረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

🔴 ሶስቱ የፓርላማ አባላት በዛሬው ስብሰባ ላይ የተናገሩትን ለመመልከት ይህን ሊንክ ይጫኑ ➡️ https://youtu.be/xkJymS2kYOY

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

18 Feb, 11:13

7,199

የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በፌደራል ፍርድ ቤት ከቀረቡባቸው ክሶች በነጻ እንዲሰናበቱ ተፈረደላቸው

🔴 አቶ ጸጋዬ ቱኬ በሌላ ፍርድ ቤት ክሶች ያለባቸው በመሆኑ በእስር ላይ ይቆያሉ ተብሏል

ቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጸጋዬ ቱኬ ከቀረቡባቸው ሁለት ክሶች በነጻ እንዲሰናበቱ በዛሬው ዕለት የፍርድ ውሳኔ እንደተሰጣቸው ከተከላካይ ጠበቆች አንዱ የሆኑት አቶ ገብረመድህን ተክላይ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ።

ከቀድሞው ከንቲባ ጋር በአንድ መዝገብ የተከሰሱት የሲዳማ ክልል የቀድሞ ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ አበራ አሬራ እና የአቶ ጸጋዬ የእህት ልጅ የሆኑት አቶ አብርሃም አመሎም በተመሳሳይ በነጻ መሰናበታቸውን ጠበቃው ገልጸዋል።

በሶስቱ ተከሳሾች ላይ የፍርድ ውሳኔውን የሰጠው፤ ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሀዋሳ ማዕከል ነው። ፍርድ ቤቱ ዛሬ ማክሰኞ የካቲት 11፤ 2017 በዋለው ችሎት፤ “ሶስቱም ተከሳሾች የቀረበባቸውን ሁለቱንም የወንጀል ክሶች ያልፈጸሙና በሚገባ የተከላከሉ መሆናቸው በነጻ ተሰናብተዋል” ሲል ውሳኔ ማስተላለፉን ጠበቃ ገብረመድህን ገልጸዋል።

የሲዳማ ክልል ፍትህ ቢሮ በአቶ ጸጋዬ እና በሁለቱ ተከሳሾች ላይ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ክስ የመሰረተው፤ “የማይገባ ጥቅም በመቀበል የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል” እንዲሁም “በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ወይም ንብረትን ህጋዊ አስመስለው አቅርበዋል” በሚል ነበር።

ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሀዋሳ ማዕከል፤ ሶስቱም ተከሳሾች የቀረቡባቸውን ክሶች እንዲከላከሉ ባለፈው ጥቅምት ወር አጋማሽ ገደማ ብይን ሰጥቷል።

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15139/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

18 Feb, 10:20

5,873

የተወካዮች ምክር ቤት የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን ለአንድ ዓመት አራዘመ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኞ የካቲት 11፤ 2017 ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን ለአንድ አመት አራዘመ።

የኮሚሽኑን የስራ ዘመን ለማራዘም የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ፤ በሶስት የፓርላማ አባላት ተቃውሞ በአብላጫ ጽምጽ ጸድቋል። 

መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ለተፈጠሩ ልዩነቶች “ወሳኝ ምክንያቶችን የመለየት” እና ውይይቶች የሚካሄዱባቸውን ርዕሰ ጉዳዮች በመለየት “ምክክር እንዲደረግባቸው የማመቻቸት” ዓላማ ይዞ የተቋቋመው ኮሚሽኑ፤ በአዋጅ የተቀመጠለት የስራ ዘመን ሶስት ዓመት ነው።

የተወካዮች ምክር ቤት በእረፍት ላይ ያሉትን የፓርላማ አባላት አስቸኳይ ስብሰባ የጠራው፤ የኮሚሽኑ የስራ ዘመን ከማለቁ ሁለት ቀን አስቀድሞ ነው።

ፓርላማው ኮሚሽኑ ለተጨማሪ አንድ ዓመት በስራ ላይ እንዲቆይ ውሳኔ ከማሳለፉ አስቀድሞ፤ የተቋሙን የሶስት ዓመታት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጧል።

ሪፖርቱን ለፓርላማ አባላት በንባብ ያቀረቡት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፤ ኮሚሽኑ በዚህ ጊዜ ውስጥ የምክክር፣ የአጀንዳ መለየት እና ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ስራዎችን በ10 ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ማጠናቀቁን አስታውቀዋል። 

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15130/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

17 Feb, 14:44

6,117

የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ “ቴክኒካዊ ድርድር” ዛሬ ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አመቻችነት የሚያካሄዱት “ቴክኒካዊ ድርድር” ዛሬ ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል።
በሶማሊያ
የማስታወቂያ፣ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር ዳውድ አዌይስ የተመራ የልዑካን ቡድን ዛሬ ሰኞ ወደ አንካራ አቅንቷል። 

ሚኒስትሩ በኤክስ ይፋዊ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ የሁለቱን ሀገራት የመጀመሪያ ዙር ቴክኒካዊ ውይይት ለማስጀመር በአንካራ የሶማሊያ ልዑካንን መቀላቀላቸውን አስታውቀዋል።

ዳውድ አዌይስ በዚሁ መልዕክታቸው፤ ውይይቱ “የአንካራ ቃል ኪዳንን ተግባራዊ ለማድረግ መንገዶች ለማፈላለግ” ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ “ልዩነቶቻቸውን እና አወዛጋቢ ጉዳዮችን ወደ ኋላ ለመተው” እና “ትብብር ለማበጀት” በአንካራ ስምምነት የተፈራረሙት ባለፈው ታህሳስ ወር መጀመሪያ ላይ ነበር።

ሁለቱ ሀገራት በቱርክ አመቻችነት በተፈራረሙትን በዚሁ ስምምነታቸው፤ “አንዳቸው ለሌላው ሉዓላዊነት፣ አንድነት፣ ነጻነት እና የግዛት አንድነት ያላቸውን ክብር እና ቁርጠኝነት” መግለጻቸው ይታወሳል።   

🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15123/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

17 Feb, 09:45

5,274

በጋምቤላ ክልል በተከሰተ የአተት ወረርሽኝ፤ ዘጠኝ ሰዎች ሲሞቱ 136 ሰዎች በበሽታው ተይዘዋል

በጋምቤላ ክልል ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ በተከሰተ የአጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት (አተት) ወረርሽኝ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ማለፉን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ በአራት ወረዳዎች ላይ የተከሰተው ወረርሽኝ፤ መነሻው በአጎራባች ከሚገኙት የደቡብ ሱዳን አካባቢዎች መሆኑንም የጤና ቢሮው ገልጿል።

የክልሉ ጤና ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ ወንድማገኝ በላይነህ፤ ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው ከአንድ ሳምንት ገደማ በፊት በአኮቦ ወረዳ መሆኑን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

በአተት ወረሽኝ ለመጀመሪያ ጊዜ መያዛቸው በምርመራ የተረጋገጠው በ9 ሰዎች ላይ ቢሆንም፤ ከአንድ ሳምንት በኋላ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር 136 መድረሱን ኃላፊው አስረድተዋል።

በወረርሽኙ የተጠቁ ሰዎች በአጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት የሚያጋጥማቸው በመሆኑ በአተት መጠቃታቸው ይገልጽ እንጂ፤ በህሙመኑ ላይ የታዩት የበሽታው ምልክቶች በዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ትንታኔ መሰረት በኮሌራ መያዛቸውን የሚያመለክት መሆኑን አቶ ወንድማገኝ አብራርተዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ወረርሽኙ ኮሌራ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ ናሙና ወደ አዲስ አበባ አበባ መላኩንም አክለዋል። “እኛ ከዚህ ወደ ኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ናሙና ልከናል። ትክክለኛ ኮሌራ ነው ብሎ ማረጋገጫ አላከልንም” ሲሉ አቶ ወንድማገኝ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ኮሌራ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በማስከትል፣ በሰውነት ውስጥ የሚገኝን ፈሳሽ አሟጥጦ በማስወጣት፣  አቅምን በማዳከም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሞት የሚዳርግ በሽታ ነው።

🔴 ለዝርዘሩ ▶️ https://ethiopiainsider.com/2025/15099/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

15 Feb, 17:23

6,553

ፓርላማው በመጪው ማክሰኞ በሚያካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን ያራዝማል ተብሎ ይጠበቃል

የሶስት አመት የስራ ዘመኑን እያገባደደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን በመጪው ማክሰኞ በሚካሄድ አስቸኳይ የፓርላማ ስብሰባ ላይ ሊያቀርብ ነው።

በዚሁ ስብሰባ ላይ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ “የስራ ዘመን ይራዘማል” ተብሎ እንደሚጠበቅ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

በታህሳስ 2014 ዓ.ም የጸደቀው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ፤ የኮሚሽኑ የስራ ዘመን ሶስት ዓመት እንደሆነ ይደነግጋል።

የኮሚሽኑ የስራ ዘመን የሚቆጠረው፤ በአዋጁ መሰረት የሚመረጡ ኮሚሽነሮች በፓርላማ ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ እንደሆነ በድንጋጌው ላይ ሰፍሯል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በዕጩነት የቀረቡ 11 ኮሚሽነሮችን ሹመት ያጸደቀው የካቲት 14፤ 2014 ዓ.ም. ነው።

ፓርላማው ለአንድ ወር እረፍት የተበተኑ አባላቱን ለመጪው ማክሰኞ አስቸኳይ ስብሰባ የጠራው፤ የኮሚሽኑ የስራ ዘመን ድፍን ሶስት ዓመት ከሚሞላበት ዕለት ሁለት ቀናት አስቀድሞ ነው።

የተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ረቡዕ ለአባላቱ ባሰራጨው የስብሰባ ጥሪ፤ ለኮሚሽኑ ጥያቄ ማቅረብ የሚፈልጉ አባላት እስከ ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 8፤ 2017 ድረስ እንዲመዘገቡ አሳስቦ ነበር።

🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15089/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

14 Feb, 20:54

7,077

ከመተሐራ ከተማ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 6.0 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

ከመተሐራ ከተማ ስድስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ አካባቢ ላይ በሬክተር ስኬል 6.0 የደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ዛሬ አርብ ምሽት 5ሰዓት ከ28 ደቂቃ ላይ የደረሰው ርዕደ መሬት፤ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ ከተመዘገቡት ሁሉ በመጠን ከፍተኛው ነው።

የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት “በጣም ጠንካራ” ሆኖ የተሰማው በመተሐራ ከተማ ይሁን እንጂ መዲናይቱን አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ ከተሞችን ማዳረሱን የአሜሪካው የምርምር ተቋም ገልጿል። የርዕደ መሬቱ ንዝረት በአዋሽ ከተማ “መጠነኛ” እንደነበር ያመለከተው ተቋም፤ በአዳማ፣ ሞጆ፣ ቢሾፍቱ እና ደብረ ብርሃን ከተሞችም በተመሳሳይ መጠን መከሰቱን ጠቁሟል።

በመተሐራ እና አዋሽ ከተሞች አቅራቢያ ያሉ አካባቢዎች ባለፉት ወራት የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ ሲከስትባቸው የቆዩ ናቸው። በአካባቢዎቹ በመስከረም እና ጥቅምት ወራት ሲከሰት የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ በህዳር ወር ጋብ ያለ ቢመስልም፤ በታህሳስ እና ጥር ወራት በቀን ለበርካታ ጊዜያት ጭምር ሲመዘገብ ቆይቷል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦችን የሚመዘግበው “ቮልካኖ ዲስከቨሪ”፤ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ መጠናቸው በሬክተር ስኬል 4.0 እና ከዚያ በላይ የሆኑ 173 ርዕደ መሬቶች በኢትዮጵያ መከሰታቸውን አስታውቋል። እስከ ዛሬ ምሽቱ ክስተት ድረስ በመጠኑ ከፍተኛ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ ታህሳስ 26 ለሊት የተከሰተው እና በሬክተር ስኬል 5.8 የተለካው ርዕደ መሬት ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

[በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ታክሎበታል]

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

13 Feb, 13:15

7,680

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓትን ለሶስት ወራት ከማንኛውም ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አገደ 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ለሶስት ወራት “በምንም አይነት” ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳይሳተፍ አገደ። በዚህ ጊዜ ውስጥ ህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ የሚያስችል “የእርምት እርምጃ” ካልወሰደ፤ የፓርቲው ምዘገባ በቀጥታ እንደሚሰረዝ ቦርዱ አስታውቋል።

ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ይህን ያስታወቀው፤ ህወሓትን በተመለከተ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 6፤ 2017 ባወጣው መግለጫ ነው። ቦርዱ ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት “በልዩ ሁኔታ” መስጠቱን የገለጸው፤ በነሐሴ 2016 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ ነበር። 

ይህ እርምጃ በጥር 2013 ዓ.ም. በምርጫ ቦርድ አማካኝነት ከፓርቲነት የተሰረዘው ህወሓትን፤ ወደ “ህጋዊ ሰውነት” የመለሰ እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾ ነበር። ቦርዱ ህወሓትን ከፓርቲነት ሰርዞ የነበረው፤ “ኃይልን መሠረት ባደረገ የአመጻ ተግባር ላይ መሳተፉን” እንዳረጋገጠ በመጥቀስ ነበር። 

ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማጣት በምክንያትነት ተጠቅሶ የነበረው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተካሄደ የግጭት ማቆም ስምምነት በጥቅምት 2015 ዓ.ም. መቋጨቱ ይታወሳል።

ስምምነቱን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈራረመው ህወሓት፤ ህጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስ ለቦርዱ ያቀረበው ጥያቄ “በህግ የተደገፈ አይደለም” በሚል ውድቅ ተደርጎ ነበር። 

🔴 ለዝርዝሩ:- https://ethiopiainsider.com/2025/15059/

@EthiopiaInsiderNews
Ethiopia Insider

12 Feb, 14:46

7,041

ኢትዮ ቴሌኮም በግማሽ አመት ብቻ 32.8 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዘገቡን ገለጸ

ኢትዮ ቴሌኮም ባለፈው ግማሽ ዓመት 61.9 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ። በዚሁ ጊዜ ውስጥ 32.8 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዘገቡን የገለጸው ተቋሙ፤ የደንበኞቹን ቁጥር 80.5 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉንም ይፋ አድርጓል።

ይህ የተገለጸው የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬሕይወት ታምሩ፤ የተቋማቸውን የግማሽ አመት አፈጻጸም ዛሬ ረቡዕ የካቲት 5፣ 2017 በአዲስ አበባው ስካይ ላይት ሆቴል ባቀረቡበት ወቅት ነው። ኢትዮ ቴሌኮም በ2017 በጀት ዓመት ለማግኘት ያቀደው አጠቃላይ ገቢ 163.7 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ባለፈው መስከረም አስታውቆ ነበር።

መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ኩባንያ በመንፈቅ ዓመቱ ያገኘው ገቢ፤ ከእቅዱ 90.7 በመቶ ያሳካ መሆኑን አመልክቷል። ኩባንያው በዚሁ ወቅት ያስገባው ገቢ፤ በ2016 ዓ.ም. ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ19 ቢሊዮን ብር ጨምሯል።

ኢትዮ ቴሌኮም ለገቢው መጨመር በምክንያትነት ከጠቀሳቸው ውስጥ፤ የሞባይል ስልክ ደንበኞቹ የዳታ እና የድምጽ አጠቃቀም ማደግ ይገኝበታል። የኩባንያው ደንበኞች የዳታ አጠቃቀም፤ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ሲነጻጸር በ48.8 በመቶ እድገት ያስመዘገበ መሆኑ በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተጠቅሷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)