أحدث المنشورات من Ethio telecom (@ethio_telecom) على Telegram

منشورات Ethio telecom على Telegram  

Ethio telecom
The first Telecom operator in Africa https://t.me/EthiotelecomChatBot
335,074 مشترك
6,383 صورة
115 فيديو
آخر تحديث 01.03.2025 04:18

قنوات مشابهة

Zehabesha
62,348 مشترك
DStv Ethiopia
47,575 مشترك

أحدث المحتوى الذي تم مشاركته بواسطة Ethio telecom على Telegram


ኩባንያችን ከጅማ ከተማ አስተዳደር ጋር በከተማዋ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርግ የስማርት ሲቲ “ስማርት ጅማ” ፕሮጀክትን ለመተግበር የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት አደረገ።

ፕሮጀክቱ ከተማዋን በሁለገብ ዲጂታል ሶሉሽኖች ለማዘመን ያለመ ሲሆን፣ የክላውድ መሰረተ ልማትን፣ የጥሪ ማዕከልን፣ ጠንካራ የመረጃ ማዕከልን፣ እጅግ ከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት ያለው ኢንተርኔትን፣ የላቀ የሲሲቲቪ ደህንነት ካሜራ ሲስተምን፣ የኦፕቲካል ፋይበር እንዲሁም ሌሎች የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን ያካትታል።

ስምምነቱ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶችን ጨምሮ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና፣ በትራንስፖርት፣ ግብር የመሳሰሉ አገልግሎቶችን ለማዘመን ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ከመሆኑም ባሻገር እጅግ ቀልጣፋ አገልግሎት አሰጣጥን ዕውን በማድረግ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ህይወት ቀላል ያደርጋል።

ጅማ ለቱሪዝም ቀዳሚ መዳረሻነት፣ ለኮንፈረንስ፣ ለኢንዱስትሪ እና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተመራጭ እንድትሆን የሚያስችላትን አቅም በማጎልበት ተወዳዳሪነቷን የሚያሳድግ ሲሆን፣ ይህም የንግድ እንቅስቃሴን በማነቃቃት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ያሳድጋል።

የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት በአዲስ አበባ (ሲቲኔት)፣ አዳማ፣ ሸገር ሲቲ፣ ሐረር፣ ደሴ፣ ኮምቦልቻ እና ባህር ዳር የመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት የተገበርን ሲሆን በጅግጅጋ ከተማ በትግበራ ሂደት እንዲሁም ከሌሎች ከተሞች አስተዳደሮች ጋር በውይይት ላይ እንገኛለን።

#Jimma #SmartCity #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #SmartAfrica #Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia

ኢትዮ ቴሌኮም በጅማ ከተማ የ5ጂ ኔትወርክ አገልግሎት አስጀመረ፤ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ በማፋጠን ላይ!

በኢትዮጵያ ቀዳሚው የቴሌኮም እና ዲጂታል አገልግሎቶች አቅራቢ የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም በሀገር አቀፍ ደረጃ የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) ኔትወርክ ማስፋፊያ አጠናክሮ በመቀጠል በዛሬው ዕለት በጅማ ከተማ አገልግሎቱን በይፋ አስጀምሯል፡፡

ኩባንያችን የ5ጂ አገልግሎትን በአዲስ አበባ እ.ኤ.አ በ2022 ካስጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ እስካሁን ድረስ፣ ጅማን ጨምሮ በ12 ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በጅግጅጋ፣ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በባህር ዳር፣ በሐዋሳ፣ በወላይታ ሶዶ፣ በሆሳዕና፣ በአርባ ምንጭ እና በቢሾፍቱ አገልግሎቱን ዕውን አድርጓል።

ቴክኖሎጂው የኔትወርክ አቅም ከመጨመር ባሻገር አዳዲስ የዲጂታል እና የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ ለኦንላይን ትምህርት፣ ለጀማሪ የንግድ ተቋማት (startups)፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የዲጂታል ክፍተትን ለማጥበብ፣ የስማርት ስልክ አቅርቦት ለማሳደግ እና የዲጂታል ሊትሬሲን ለመጨመር አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል።

የ5ጂ ቴክኖሎጂ የድርጅት ደንበኞችን የዕለት ተዕለት አሰራርን ከማዘመን በተጨማሪ፣ ቁልፍ በሆኑ ዘርፎች ላይ ማለትም ጤናን፣ ግብርናን፣ ትምህርትን፣ ማኑፋክቸሪንግን እና ማዕድንን፣ ትራንስፖርትን፣ ቱሪዝምን፣ መዝናኛን በስማርት ቴኮኖሎጂ በማዘመን ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡

ክቡራን ደንበኞቻችን የ5ጂ አገልግሎት ማስተናገድ የሚያስችሉ ቀፎዎች እና ሲም እንደፍላጎት በአገልግሎት ማእከላችን በማግኘት የእጅግ ፈጣኑን ኔትወርክ ተጠቃሚ በመሆን አስደናቂ ተሞክሮ እንድታገኙ በደስታ እንጋብዛለን፡፡

ለተጨማሪ፡- https://bit.ly/42Z0ygF
አዲስ ፍጥነት፣ አዲስ ምቾት፣ አዲስ አኗኗር!

የካቲትን ለወደቁትን አንሱ!!

በዚህ ወር በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን በሚቀላቀሉ አዲስ ተከታዮች (Followers) ብዛት ልክ 30 ብር እንዲሁም በሚጋሩ ልጥፎች (Share) ልክ 10 ብር ለወደቁትን አንሱ የነዳያን በጎ አድራጎት ማኅበር እንለግሳለን!

🤝 እርስዎም ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ፤ ፖስቶቻችንን ያጋሩ፤ ለወገን ድጋፍ ይተባበሩ!

ቴሌግራም | ፌስቡክ | ኢንስታግራም | ሊንክዲን | ዩትዩብ | ቲክቶክ

በተጨማሪም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ለበጎ አድራጎት በሚለው አማራጭ የፈቀዱትን የገንዘብ መጠን በመለገስ ለወገንዎ ተስፋ ይሁኑ!

🙏 ዘላቂ የጋራ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለወገን ብሩህ ተስፋ!


#MatchingFundForSustainableFuture
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

መልካም የሥራ ሳምንት!


#Monday #MondayMotivation
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

በበጎነት የሚያሳልፉት መልካም የእረፍት ቀን ይሁንልዎ!


#Sunday
#StayConnected
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

ገንዘብዎን በፍጥነትና ቅልጥፍና ይረከቡ፤ 5%🎁 ተጨማሪ የገንዘብ ስጦታዎን ይውሰዱ!!

🌐ከባህርማዶ በቴሌብር ሬሚት፣ በቪዛ፣ በዌስተር ዩኒየን፣ ኦንአፍሪክ እንዲሁም በቱንስ የተላከልዎን ዓለም አቀፍ ሐዋላ በቴሌብር ሲቀበሉ ከዕለታዊ የምንዛሬ ተመን በተጨማሪ 5% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፡፡

🗓 እስከ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም


ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia

🪪 የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባ በመላ የአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሄደው የካርድ ኅትመት በቀላሉ በቴሌብር ሱፐርአፕ ይዘዙ!

በአዲስ አበባ፣ ሐዋሳ፣ አዳማ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ነቀምቴ፣ ቢሾፍቱ፣ ዱከም፣ ወንጂ፣ ወለንጭቲ፣ ለኩ፣ ይርጋለም፣ አለታ ወንዶ፣ ዲላ፣ ይርጋጨፌ፣ ቡሌሆራ፣ ባኮ እና አረካ ከተሞች የካርድ ኅትመት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡

👉 ቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ላይ ‘’NID (Fayda) Printing’’ በሚለው ሚኒ መተግበሪያ!


🔗 የመረከቢያ ቦታዎቹን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ


ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

https://youtu.be/gL9ttFeQAsk

የካቲትን ለወደቁትን አንሱ!!

በዚህ ወር በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን በሚቀላቀሉ አዲስ ተከታዮች (Followers) ብዛት ልክ 30 ብር እንዲሁም በሚጋሩ ልጥፎች (Share) ልክ 10 ብር ለወደቁትን አንሱ የነዳያን በጎ አድራጎት ማኅበር እንለግሳለን!

🤝 እርስዎም ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ፤ ፖስቶቻችንን ያጋሩ፤ ለወገን ድጋፍ ይተባበሩ!

ቴሌግራም | ፌስቡክ | ኢንስታግራም | ሊንክዲን | ዩትዩብ | ቲክቶክ

በተጨማሪም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ለበጎ አድራጎት በሚለው አማራጭ የፈቀዱትን የገንዘብ መጠን በመለገስ ለወገንዎ ተስፋ ይሁኑ!

🙏 ዘላቂ የጋራ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለወገን ብሩህ ተስፋ!


#MatchingFundForSustainableFuture
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

በጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ኩባንያችን በማህበራዊ ኃላፊነት ረገድ በድምሩ ከ287.17 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉ ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለሰብአዊ ድጋፍ፣ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአረንጓዴ ልማትና ማስዋብ እንዲሁም ለሀገራዊ ፕሮጀክቶች የተደረገ ሲሆን፣ በዓይነት 131.3 ሚሊዮን ብር፣ በገንዘብ ደግሞ ከ155.9 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።

የኩባንያችን ሰራተኞች፣ አጋር አካላት እና የአካባቢ ማህበረሰብ ክፍሎችን በአረንጓዴ ልማት ሥራዎች በንቃት በማሳተፍ፣ በበጀት አመቱ አጋማሽ በ105 ቦታዎች ከ446,000 በላይ ችግኞችን ለመትከል ተችሏል፡፡

የኩባንያችን ሰራተኞች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር፣ ደም በመለገስ እና የተለያዩ አይነት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን በመስጠት በማህበራዊ ኃላፊነት አርአያ የሚሆን ተግባር አከናውነዋል።

ለተጨማሪ https://bit.ly/40RlnYV ይጫኑ

#CSR #Ethiotelecom #telebirr #GSMA #ITU #WorldBank #OECD #G6countries #HOPR #HoF