Dernières publications de የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት (@aasundayschool) sur Telegram

Publications du canal የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
ይህ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ልሳን ነው።
10,161 abonnés
3,317 photos
37 vidéos
Dernière mise à jour 05.03.2025 22:10

Le dernier contenu partagé par የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት sur Telegram

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

30 Dec, 06:03

3,501

ሊቀ መአምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ በአጠቃላይ በቀኑ የተካሄደው ጉባኤ የቤተክርስትያን ጉዳይ ርእስ የሆነበት እና ሌሎች ክፍሎችም በዚሁ መልኩ በእቅድ የተመራ አሰራር ለማምጣት ሰንበት ት/ቤቶች ሀገረ ስብከቱን የመደገፍ ስራ መስራት አለባችሁ ያሉ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ስርአተ ትምህሩቱን ለመተግበር ያለውን የሀገረ ስብከቱ የገጠመውን በጀት ችግር እንደ ሀገረ ስብከት እንደሌላው ሀገረ ስብከት ሁሉ በጀት እንደሚመደብ ተገልጿል።
የሰንበት ት/ቤቶች የመማሪያ እና ሌሎች አገልግሎት የሚውሉ ለቢሮ ግንባታ የሚውል ቦታ ጉዳይ ወጥ የሆነ የህንጻ ዲዛይን የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት አንድነት እንዲያዘጋጅ መመርያ ያስተላለፋ ሲሆን በዛም መሰረት በየቦታው የሚገነቡ የሰንበት ት/ቤቶች ህንጻ አንድ አይነት እስታንዳርድ እንዲሆኑ እንዲሁም እስከ አሁን መማርያ መጽሐፍት ያልገዙ አጥቢያዎችን በሊስት እንዲቀርቡ መመረያ አስተላልፈዋል።
ብጹእ አቡነ ቀለሜንጦስ ለውጥ የሚመጣው እቅድን መሠረት አድርጎ ሲሰራ እና ዛሬ እንዳየነው ጉባኤ አባላት በጠንካራ ሀሳብ ሲሞግቱ መሆኑን ገልጸው ይህ አስራር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል ከዛም በተጨማሪ የበጀት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አለመኖሩ ግርምት የፈጠረባቸው መሆኑ እና ለስንት ሀገረ ስብከት በፈሰስ እያስተዳደረ ያለ ምሳሌ የሆነ ሀገረ ስብከት እንዴት ለራሱ አካል አጠገቡ ላለው በጀት አይኖረውም የሚል ጥያቄ ለክቡር ስራ አስኪያጁ አቅርበዋል። በምላሹም የበጀት ጉዳይ ጅማሮ እንዳለ እና እልባት እንደሚያገኝ የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ ለብጹእነታቸው ቃል ገብተዋል።

በስተመጨረሻም በተጓደሉ አመራር ምትክ ዲ. በእሱፈቃድ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዋናስራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲያገለግሉ በጉባኤ ጸድቆ ጉባኤው ከምሽቱ 12:30 በጸሎት ተጠናቋል።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

30 Dec, 06:03

2,677

ለምሳ እረፍት ከመውጣቱ በፊት የሀገረስበከቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሊቀመአምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ሀገረ ስብከቱ ሊመለሱ የሚገባቸውን ጥያቄዎች እና አጠቃላይ በእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱ ላይ ምክረ ሀሳብ ሰጥተው ጉባኤው ለምሳ እረፍት ወጥቷል።

ከሰአት በውኃላ ጉባኤው የቀጠለ ሲሆን ከዚህ ቀደም በትግበራ ሙከራ ላይ የነበረው የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶችን የማንዎል መረጃ አያያዝ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ወደ ዲጅታል የመቀየር እና የሰንበት ት/ቤቶችን አሰራር በማዘመን እና አገልግሎታቸውን ዘመኑን የዋጀ ለማድረግ ተጀምሮ የነበረውን እና በ25 ሰንበት ት/ቤቶች ሙከራ ላይ የነበረው የመጀመሪያ ዙር የዳታ ቤዝ ማበልጸግ የመጀመሪያ ደረጃ የተጠናቀቀ እና ከዛሬ ጀምሮ በሰንበት ት/ቤቶች ወደተግባር የሚገባ መሆኑ ተገልጿል።

በአበልጻጊው ባለሙያም ሰንበት ትቤቶችም ይህን በመተግበር አሰራራቸውን በማዘመን የተዘጋጀውን ሲስተም እንዲጠቀሙ ጥሪ ያስተላለፋ ሲሆን በዚህኛው ዙር ያለውን ጠንክረው በመተግበር ቀጣይ ለሚመጣው በከፍተኛ ደረጃ ሰንበት ት/ቤቶች አገልግሎትን ለማዘመን የሚያሰችለውን የሲስተም ማበልጸግ ስራ እድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ተላልፏል ።

በሁለተኝነት በልማት ተነሺዎች ዙሪያ ከተደረገው ጥናት በመነሳት ሰንበት ት/ቤቶች ራሳቸውን ካለው ወቅታዊ የልማት ሂደት ጋራ አገልግሎታቸውን ቀጣይ እንዲሆን ምን ማድረገ ይችላሉ የሚለው እና አባላት ካሉበት ቦታ ወደ ሌላ ሲዛወሩ እንዴት መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ይቀጥሉ የሚለው የቀረበ ሲሆን ሁሉም ሰንበት ት/ቤት የልማትስራው እየቀጠለ በመሆኑ ራሳቸውን ዝግጁ በማድረግ የአባለቱን መረጃ በተገቢው በመያዝ ኩነቱ በአጥቢያቸው ከደረሰ አባላቶቻቸው በሚሄዱበት ቦታ ሁሉ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ፣በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዬች ሊፈጠሩ የሚችሉ ተግዳሮቶችንም ሆነ እድሎችን እንዴት መጠቀም እንዳለባቸው በዲ.ዳንኤል ገብረ ማርያም የአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት ሰንበት ት/ቤት አንድነት ዋና ጸሐፊ ተብራርቷል።

ቀጥሎም በወጣት ኤልያስ አበበ የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ምክትል ሰብሳቢ በቤተክርስትያን አስተዳደርያዊ ችግሮች የሰንበት ት/ቤት ድርሻ በሚል መነሻ ሀሳብ የቀረበ ሲሆን በአጥቢያ፣ በመካከለኛ መወቅሮች እና በከፍተኛ መዋቅሮች ያሉ መሠረታዊ የቤተክርስትያን ችግሮች የተነሱ ሲሆን እነዚህ ችግሮች ካልተፈቱ እና ካልቀነሱ ለቤተክርስትያን አደጋ መሆናቸውን ግንዛቤ ተወስዶ ለመፍትሄው ሰንበት ት/ቤቶችም ከአጥቢያ ጀምሮ መረጃ እና ወቅታዋ ጉዳይ ክፍሉን በማደራጀት በተዋረድ ካሉ ክፍለ ከተማ አንድነት እና ሀገረስብከት አንድነት ከተዋቀሩ መረጃ እና ወቅታዊ ጉዳይ ክፍሎች ጋር በተወረድ በሚዘጋጁ መድረኮች በመወያየት ከሚመለከተው የቤተክርስትያን ኃላፊዎች ጋር በመረጃ በተደራጀ መልኩ በውይይት የሚፈቱትን በውይይት መፍታት እንዲሁም በውይይት የማይፈቱትን ባለን የልጅነት ግዴታ እና የአስተዳደር ድርሻ የሚመለከተውን አካል የቤተክርስትያናችንን ቃለ አዋዲ እና ሌሎች ህጎች በመንተራስ በመሞገት ወደ መፍትሄ እንዲመጡ የበኩላችንን እንድንወጣ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል ።
በዚህም በተለይ አሁን አሁን አንድ አንድ ኃላፊዎች በቤተክርስትያን ጉዳይ ምእመናን ምን አገባቸው እና ሰንበት ት/ቤት ተወካዮችን አለማሳተፍ እና እንደ ባለቤት አለማየት ከፍተኛ ችግር እየሆነ መምጣቱ ተጠቁሟል ።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

30 Dec, 06:02

2,729

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የ11ኛ አመት 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ታህሳስ 20/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመሰብሰቢያ አዳራሽ አከናወነ።

በእለቱ ብጹዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የሰሜን ሽዋ ሀገረስብከት እና በመንበረ ፖትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት  የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሊቀጳጳስ ፣  ሊቀ መአምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ፣  መጋቢ ሀዲስ ጸጋ ወልደ ትንሳኤ  የመንበረ ፖትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ፣ መምህር ደምስ አየለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ዋና ክፍል ኃላፊ ለእከ ኄራን መንክር ግርማ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት  ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ  የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አመራር እና አስፈጻሚዎች የክፍለ ከተማ አመራሮች እንዲሁም የገዳማት እና አድባራት ሰንበት ት/ቤት አመራሮች በተገኙበት ጉባኤው ተከናውኗል ።

መምህር ደምስ አየለ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፋ ሲሆን ከዛ በመቀጠል የሀገረ ስብከቱ አንድነት የ6ወር የአፈጻጸም ሪፖርት በ ዲ.በሱፈቃድ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዋና ስራ አስፈጻሚ  የስራ አስፈጻሚውን ሪፖርት  ከእቅድ አንጻር አቅርበዋል።
ላእከ ሔራን መንክር ግርማ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ የስራ አመራሩን ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ጉባኤተኞቹም በቀረበው ሪፖርት ላይ ጥያቄዎችን ያነሱ ሲሆን የሚመለከታቸው የአስፈጻሚ ክፍሎች እና የአመራር አባላት ለጥያቄዎቹ ምላሽ ሰጥተዋል ።
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

27 Dec, 07:06

985

...... ለረዥም ና ዝግ ላለ ለዲያቢሎስ ውጊያ አይነተኛ ምሳሌ የሚሆነን ሱስ (ልማድ) ነው። ማንኛውም ሱስ ወይም ልማድ ሲጀምሩት ሱስ ሆኖ አይጀምርም ሰውየዉ ከጅምሩ ቢቀጨው ተቀጭቶ መቅረት ይችል ነበር ነገር ግን በረዥምና ዝግ ባለ ውጊያ ሊቆጣጠረውና ሊያቆመው ስለማይችል እርሱ(ሱሱ) ይቆጣጠረዋል። ምን አልባት ዲያቢሎስ በመጀመሪያ የሚናገረው አንዲት ቃል ብቻ ነው "ሞክር" ወይም " ቅመስ" የምትለዋን ከዚያ በመቀጠል ነው ህይወት ልምምድ ናት ሁሉን የምትወስነው አንተ ነህ በወደድክ ጊዜ ልታቆመው ወይም ልትተወው ትችላለህ የሚለው እንዲህ እንዲህ እያለ ሰውየዉ መቋቋም እስከማይችል ወይም ለመቋቋም ፍላጎቱን እስኪያጣ ድረስ ይዎጋዋል ይሁን እንጂ ሱስን ወይም ልማድን ማስወገድ ለሚወድ ሁሉ ማስወገድ ይቻላል ዲያቢሎስ ግን እንደማትችል ይነግርሀል ብትችል እንኳን ድጋሜ ወደ ተውከው ሱስ ትመለሳለ ይልሃል፡፡
ይህ የማያቋርጥ ውጊያ ስለሆነ አትንበርከክ ሱሰኝነት የሚመጣው ከሚደጋገም የፈቃድ ተግባር ነው፡፡ ይህን ተደጋጋሚ የፈቃድ ተግባር በሌሎች ተደጋጋሚና ተቀዋሚ የፈቃድ ተግባር ማስወገድ ትችላለህ፡፡ ታዲያ በእንዲባለ ተግባር ፅናት እንጂ መወላወል ሊታይበት አይገባም ፡፡ እንዲህ ያለውን የዲያቢሎስ አዝጋሚ የውጊያ ዕቅድ እንዴት መቋቋም እንድትችል የምንነግር ነገር ቢኖር ምንም እንኳን ሀሳቡ መልካም መስሎ ቢታይ እና ቀሎ እንዲታይ በማድረግ ዲያቢሎስ ቢያሳምንህም የመጀመሪያውን ደረጃ አለመፈፀም እንዳለብህ /መጀመሪያም መሞከር እንደሌለብህ/ ነው።.........
ምንጭ ፡- የዲያቢሎስ ውጊያዎች
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

26 Dec, 10:56

1,586

‹‹አንድነታችን ለቤተክርስቲያናችን››

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት #የ11ኛ_ዓመት #1ኛ ዙር የ2017 ዓ.ም መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ የክብር እንግዶች እና የአንድነቱ የጠቅላላ ጉባዔ አባላት በተገኙበት ታኅሣሥ 20/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30-11:00 ሰዓት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ያከናውናል።

በመሆኑም 👇
የየሰንበት ት/ቤቱ የሥራ አመራር የጽ/ቤት አባላት (ሰብሳቢ፥ ም/ሰብሳቢ እና ጸሐፊ) የሆናችሁ ፤ የሰባቱም ክፍላተ ከተማ አንድነት የሥራ አመራር አባላት የሆናችሁ ፤ በአንድነቱ ክፍላት ውስጥ እያገለገላችሁ የምትገኙ አባላት ፤ እንዲሁም የቀድሞ የአንድነቱ አመራር የነበራችሁ በሙሉ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት (4 ኪሎ) የስብሰባ አዳራሽ በመገኘት የስብሰባው ተሳታፊ እንድትሆኑ በልዑል እግዚአብሔር ስም ጥሪያችንን በጥብቅ እናሳተላልፋለን ።

#የአዲስ_አበባ_ሀገረ_ስብከት_የሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

24 Dec, 18:33

1,439

https://www.youtube.com/watch?v=SuZSvLQAa-E
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

24 Dec, 18:19

1,703

<<ኦርቶዶክሳዊ መሪነት>>

በቦሌ ክ/ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የስልጠናና አቅም ማጎልበቻ ክፍል ከአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር በአያት ምድብ ስር ላሉ 8 አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች  አመራሮችና ስራ አስፈጻሚዎች << ኦርቶዶክሳዊ መሪነት >> ቀሚል ርዕስ ስልጠና አካሂዱዎል።
ቦታ:- በአያት ጸበል መድኃኔዓለም እና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክን ወልድ ዋህድ
ቀን:- ታኅሣስ 13 ቀን 2017 ዓ ም 
ምንጭ:- የአ/አ/ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

24 Dec, 08:50

1,791

🌸 ‹‹#አንድነታችን ለቤተክርስቲያናችን››🌸
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት #የ11ኛ_ዓመት #1ኛ ዙር የ2017 ዓ.ም መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ የክብር እንግዶች እና የአንድነቱ የጠቅላላ ጉባዔ አባላት በተገኙበት ታህሣሥ 20/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30-11:00 ሰዓት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ያከናውናል።
#በጉባዔው_የሚነሱ_የመወያያ_አጀንዳዎች ፦
የስድስት ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት እና ውይይት ፤
በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የውይይት አጀንዳዎች ናቸው።
በመሆኑም ፦
👉#ታህሣሥ_20_2017_ዓ_ም
👉#ከጠዋቱ_3_30_11_00_ሰዓት
የየሰንበት ት/ቤቱ የሥራ አመራር የጽ/ቤት አባላት (ሰብሳቢ፥ ም/ሰብሳቢ እና ጸሐፊ) የሆናችሁ ፤ የሰባቱም ክፍላተ ከተማ አንድነት የሥራ አመራር አባላት የሆናችሁ ፤ በአንድነቱ ክፍላት ውስጥ እያገለገላችሁ የምትገኙ አባላት ፤ እንዲሁም የቀድሞ የአንድነቱ አመራር የነበራችሁ በሙሉ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት (4 ኪሎ) የስብሰባ አዳራሽ በመገኘት የስብሰባው ተሳታፊ እንድትሆኑ በልዑል እግዚአብሔር ስም ጥሪያችንን በጥብቅ እናሳተላልፋለን ።
#የአዲስ_አበባ_ሀገረ_ስብከት_የሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

23 Dec, 08:05

2,337

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

ገቢው ማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል እያስገነባ ላለው ባለ 12 ፎቅ የሕፃናት እና ወጣቶች ስብእና መገንቢያ ማእከል እና አገልግሎት ማስፋፍያ የሚውል በመቶ ብር ትውልድ የሚታነጽበትን ፕሮጀክት እየደገፉ ይሸለሙ!!!
👉ሙሉ ወጪዎ ተችሎ ወደ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ጉብኝት
👉የግብጽ ገዳማት ጉብኝት
👉 የሀገር ውስጥ ገዳማት ጉብኝት
👉የብራና ሥዕለ አድኅኖ
👉የአንገት ወርቅ እና ሌሎችም በርካታ ዕጣዎች ለባለ እድለኞች ተዘጋጅተዋል ይህ ሁሉ በመቶ ብር ።

🔻የዚህ ሕንጻ ፕሮጀክት አስፈላጊነት በጥቂቱ ፥
👉በሁለት በኩል የተሳለ ትውልድ ማፍራት
👉የግቢ ጉባኤ አገልግሎትን ማሳደግ
👉 የአብነት ትምህርትን ማስፋፋት
👉ዘመኑን የዋጁ ካህናትና ሰባኪያን ማፍራት
👉ኢ-አማንያንን ማስተማርና ማጥመቅ
👉ሴተኛ አዳሪ እህቶቻችንን ካሉበት ሕይወት ማውጣት
👉እነዚህን እና ሌሎች አገልግሎቶችን ለመደገፍ እና ለማስፋፋት በቋሚነት የቦታም ሆነ የፋይናንስ ችግር የሚፈታ የሕንጻ ፕሮጀክት ለመስራት የበኩልዎን ይወጡ።

ትኬቶቹን :--
👉በሁሉም የአሐዱ ባንክ ቅርንጫፎች
👉በአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤቶች
👉በማኅበረ ቅዱሳን ንዋየተ ቅድሳት መሸጫ ሱቆች
👉በአጥቢያ ቤተክርስቲያናት ሰንበት ት\ቤት በሙሉ ያገኙታል።

      ድጋፍ ለማድረግ
አሐዱ ባንክ. 0002505310101
ኢ.ንግድ ባንክ. 1000303949112
አቢሲንያ ባንክ. 68960665
አዋሽ ባንክ. 01304868950900
ዳሽን ባንክ 0088211311011
ዓባይ ባንክ 1891119601313011

         በለጠ መረጃ 👇
0902 50 11 31
0946 38 38 92

ለዚህ  የትውልድ መገንቢያ ሕንፃ ግንባታ የበረከት እጅዎን ይዘርጉ!!!
          #ማኅበረ_ቅዱሳን_አዲስ_አበባ_ማዕከል

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

21 Dec, 09:09

2,623

💫🌺💫🌺🌷💐🌷💫🌺💫🌷💐🌷🌺🌺🌺💫🌺

          ‹‹
#ትብብራችን_ለአንድነታችን››

    በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት  ት/ቤቶች አንድነት ሥር ለምትገኙ የየሰንበት ት/ቤቱ የሥራ አመራር የጽ/ቤት አባላት (ዋና ሰብሳቢ ፥ ምክትል ሰብሳቢ እና ዋና ጸሐፊዎች)  በሙሉ የተላለፈ
#የ11ኛ_ዓመት_1ኛ_መደበኛ_ጠቅላላ_ጉባዔ ጥሪ!!!

              
#ታህሣሥ_20_2017_ዓ_ም
             
#ከጠዋቱ_3_30_11_00_ሰዓት

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት  ት/ቤቶች አንድነት
#የ11ኛ_ዓመት #1ኛ ዙር የ2017 ዓ.ም መደበኛ ጠቅላላ  ጉባዔውን  ብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ የክብር እንግዶች እና የአንድነቱ የጠቅላላ ጉባዔ አባላት በተገኙበት ታህሣሥ 20/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30-11:00 ሰዓት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመሰብሰቢያ  አዳራሽ ያከናውናል።

📌
#በጉባዔው_የሚነሱ_የመወያያ_አጀንዳዎች
👉 የስድስት ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት እና ውይይት ፤
👉 በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የውይይት  አጀንዳዎች ናቸው።

  📌 በመሆኑም ፦
👉
#ታህሣሥ_20_2017_ዓ_ም 
👉
#ከጠዋቱ_3_30_11_00_ሰዓት 
የየሰንበት ት/ቤቱ የሥራ አመራር  የጽ/ቤት አባላት (ሰብሳቢ፥ ም/ሰብሳቢ እና ጸሐፊ) የሆናችሁ ፤ የሰባቱም ክፍላተ ከተማ አንድነት የሥራ አመራር አባላት  የሆናችሁ ፤ በአንድነቱ ክፍላት ውስጥ እያገለገላችሁ የምትገኙ አባላት ፤ እንዲሁም የቀድሞ የአንድነቱ አመራር የነበራችሁ በሙሉ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት (4 ኪሎ) የስብሰባ አዳራሽ በመገኘት የስብሰባው  ተሳታፊ እንድትሆኑ በልዑል እግዚአብሔር  ስም ጥሪያችንን በጥብቅ እናሳተላልፋለን ።

#የአዲስ_አበባ_ሀገረ_ስብከት_የሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት

💫🌺💫🌺🌷💐🌷💫🌺💫🌺🌺💫🌺💫🌺🌷💐🌷💫🌺💫🌺