የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

@senbetmezmurat


በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሥርዓትና ደንብ መሠረት በሰ/ት/ቤት የሚዘመሩ መዝሙሮች የሚቀርቡበት ቻናል ነው

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

03 Oct, 19:00


መንፈሳዊ የዜማ መሳሪያ
የምርቃት መርሐ ግብር

⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺
“በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤ በበገናና በመሰንቆ አመስግኑት።”መዝ ፻፶፥፫

የደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ፈለገ ዮርዳኖስ ሰንበት ትምህርት ቤት በ2017 ዓ.ም በበገና እና በመሰንቆ ሲያሰለጥናቸው የቆየውን ተማሪዎች ሊያስመርቅ መርሃ ግብር አዘጋጀጅቷል።

እሁድ መስከረም 26/2017ዓ.ም

⌚️  ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ
በዕለቱ፦
        ▹ትምህርተ ወንጌል
        ▹የበገና መዝሙር
        ▹ያሬዳዊ ዝማሬ
       
➝ቦታ፡በፈለገ ዮርዳኖስ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ
አድራሻ➛አውቶብስ ተራ(መናህሪያ) ከፍ  ብሎ ደብረ  መዊዕ  ቅዱስ  ሚካኤል  ካቴድራል(አዲሱ  ሚካኤል )

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

10 Sep, 14:50


​​🌼 አበባ አየሽ ወይ 🌼

እሰይ /ደስ ደስ ይበለን/(2)
አዲሱ አመት መጣልን ደስ ደስ ይበለን

ሆ ብለን መጣን ሆ ብለን(2)
ጌቶች አሉ ብለን
ሆ ብለን መጣን ሆ ብለን(2)
እሜቴ አሉ ብለን
ሆ ብለን መጣን ሆ ብለን(2)
ዘመን መጣ ብለን

አበባ አየሽ ወይ           ለምለም(2)
ባልንጀሮቼ                        "
ግቡ በተራ                        "
በእግዚአብሔር መቅደስ     "  
በዚያች ተራራ                   "   
እንድታደንቁ                      "          
የአምላክን ሥራ                 "    
ህይወት ያገኛል                 "  
እርሱን የጠራ                    "      

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ(2)

አበባ አየሽ ወይ          ለምለም (2)
ክረምት አለፈ                   "
ጨለማው ጠፋ                "   
የመስቀሉ ቃል                  "
ሆነልን ደስታ                    "   
እናገልግለው                   "  
ቤቱ ገብተን                     "     
ትንሽ ትልቁ                      "  
ተሰልፈን                         "        

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ(2)

አበባ አየሽ ወይ     ለምለም(2)
ያንን ኩነኔ                    "
ዘመነ ፍዳ                    " 
የሞቱ በራፍ                 "
ያ ምድረበዳ                 "
ልክ አንደ ክረምት         "
ሄደ ተገፎ                     "
ፀሐይ ወጣልን             "
ጨለማው አልፎ           "

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ (2)

አበባ አየሽ ወይ         ለምለም(2)
ይኸው መስከረም           "
ይኸው ፀሐይ                 "    
ንጉሡ ወርዶ                  "       
ከላይ ሰማይ                  "        
አውደ ዓመት ሆነ            "
ደስታ ሰላም                   "
ፍቅር ሲገለጥ                "   
በአርያም                       "       

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ(2)

አበባ አየሽ ወይ         ለምለም(2)
ይኸው አበባ                  "
ለምለም ቄጤማ             "
አዲሱ ዘመን                  "
አምጥቷልና                    "    
በሩን ክፈቱ                     "       
መኳንንቶቹ                     "       
የክብር ንጉሥ                 "    
ይግባ ቤታችሁ               " 

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ(2)

አበባ አየሽ ወይ         ለምለም(2)
ቤታችሁ ይሙላ             "
ሰላም ደስታ                   "
ሰጥቷችሁ እርሱ            "
የሁሉ ጌታ                     "      
ከዘመን ዘመን                "     
ያሸጋግራችሁ                "      
የሽበትን ዘር                  "   
ይሸልማችሁ                 "      

አበባ አበባ ፈካ ዘመን ሲተካ

ይሸታል ዶሮ ዶሮ የእማምዬ ጓሮ
ይሸታል ጠጅ ጠጅ የአባብዬ ደጅ

አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ
እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰዎት ብዬ

ከብረው ይቆዩን ከብረው
የክብርን ወንጌል ሰምተው
የበጉን ሥጋ በልተው
የአምላክን ፊቱን አይተው
ከብረው ይቆዩን ከብረው

💚 💚💚💚💚💚💚💚
💛 💛💛💛💛💛💛💛
❤️ ❤️

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

10 Sep, 14:45


#መስከረም_ጠባ

መስከረም ጠባ ኢዮህ አበባ /2/ 
መስከረም ጠባ ኢዮህ አበባዬ 
ኢዮህ መስከረም ጠባ ለእኛ ኢዮህ አበባ 

መስቀል አበራ ኢዮህ አበባ 
ለእኛ ሊሆነን እድገት እና ልማት 
ኢዮህ ኢዮህ አበባዬ ኢዮህ 
መስከረም ጠባ ለኛ ኢዮህ አበባ 

በተዋሕዶ የከበረች እናታችንን 
የጥበብ ልጆቿ እናከብራታለን 
ሃይማኖት ከምግባር ወንጌል መግባ 
ስላሳደገቸን የጥበብ መሠረት
ቤተክርስቲያን እናታችን 

ጥንትም መሪ እና አስተማሪ በመሆኗ 
በዓለም ላይ ታውቋል ዜናዋ 
እየተወሳ በዓለም ዜና ያኮራናል 
መስቀላችን ኢዮህ አበባ 
መስከረም ጠባ ኢዮህ አበባዬ /2/

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

10 Sep, 14:05


#አምላክ_ሆይ_ባርክልን_በዓሉን

አምላክ ሆይ ባርክልን በዓሉን /2/

ባርክልን ኧኸ በዓሉን
ለዛሬ ዓመት ኧኸ አድርሰን
ሠላም ፍቅር ኧኸ አድለን
በዕምነታችን ኧኸ አበርታን
በአንድነት ኧኸ አቁመን

አምላክ ሆይ ባርክልን በዓሉን /2/

ጽኑ ሠላም ኧኸ ለሐገሪቱ
እንዲጦሩ ኧኸ አዛውንቱ
ወጣቱ እና ኧኸ ሕጻናቱ
ያለ ጊዜ ኧኸ እንዳይሞቱ
አንድም ሳይጎድል ኧኸ በመሃላችን
ለዓመት ያብቃን ኧኸ አምላካችን

አምላክ ሆይ ባርክልን በዓሉን /2/

አገልጋዩን ኧኸ ከመቅደሱ
እንዲኖሩ ኧኸ ሲያወድሱ
ታቦቱንም ኧኸ ከመንበሩ
አታናውጠው ኧኸ ከደብሩ
ወታደሩን ኧኸ በድንበሩ
ጠብቅልን ኧኸ በበረከት
ቸሩ ጌታ ኧኸ የፍቅር አባት

ድንግል ሆይ ባርኪልን በዓሉን /2/

ለባርኮ ኧኸ አውደ ዓመት
ንዒ ማርያም ኧኸ በምሕረት
ያዘነው ኧኸ እንዲጽናና
የተከዘው ኧኸ እንዲል ቀና
በሐገር ውስጥ ኧኸ ውጭም ላለው
በበረከት ኧኸ አትለይው

ድንግል ሆይ ባርኪልን በዓሉን /2/

የናቁሽም ኧኸ ጽዮን ብለው
ይሠግዳሉ ኧኸ ፊትሽ ወድቀው
ካኅናቱ ኧኸ በማሕሌቱ
በቅዳሴው ኧኸ በሠዓታቱ
ከልጅሽ ጋር ኧኸ ከዓለም ጌታ
ዘመሩልሽ ኧኸ በዕልልታ

ድንግል ሆይ ባርኪልን በዓሉን /2/
ባርኪልን ኧኸ /4/

💚💚
💛💛
❤️❤️

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

21 Aug, 21:48


ማርያም አርጋለች ወደ ገነት 
ማርያም አርጋለች ወደ ገነት
የሰማይ መላእክት እያረጋጉአት     

አዝማች------  
 
የአባቱዋን ዳዊትን ትንቢት ልትፈፅም
ወርቁን ተጎናፅፋ በቀኙ ልትቆም
ወዳምላክ ማደሪያ ወደ ሰማያት
አረገች በእልልታ ድንግል የእኛ እናት
አርጋለች ማርያም ተነስታለች

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

16 Aug, 23:22


ቡሄ በሉ

ቡሄ በሉ *2* ልጆች ሁሉ የኛማ ጌታ
የዓለም ፈጣሪ የሰላም አምላክ
ትሁት መሀሪ በደብረ ታቦር የተገለጠው
ፊቱ እንደ ፀሐይ በርቶ የታየው
ልብሱ እንደብርሃን ያንፀባረቀው

ድምጽህን ሰማና በብህሩ ደመና *2*
የቡሄው ብርሃን ለኛ መጣልን *2*

ያዕቆብ ዮሐንስ እንዲሁም ጴጥሮስ
አምላክን አዩት ሙሴ ኤልያስ
አባቱም አለ ልጄን ስሙት
ቃሌ ነውና የወለድኩት

ታቦር አርሞንኤም ብርሃን ታየባቸው
ከቅዱስ ተራራ ስምህ ደስ አላቸው
ሰላም ሰላም የታቦር ተራራ
ብርሀነ መለኮት ባንቺ ላይ አበራ

በተዋህዶ ወልድ የከበረው
የእግዚአብሔር አብ ልጅ
ወልደማርያም ነው
ቡሄ በሉ *2* የአዳም ልጆች
ብርሃንን ተቀበሉ

አባቴ ቤት አለኝ ለከት
እናቴ ቤት አለኝ ለከት
አጎቴም ቤት አለኝ ለከት
ተከምሯል እንደ ኩበት

የዓመት ልምዳችን ከጥንት የመጣው
ከተከመረው ከመሶቡ ይውጣ
ከደብረ ታቦር ጌታ ሰለመጣ
የተጋገረው ሙልሙሉ ይምጣ

ኢትዮጵያውያን ታሪክ ያላችሁ
ባህላችሁን ያዙ አጥብቃችሁ
ችቦውን አብሩት እንዳባቶቻችሁ
ምስጢር ስላለው ደስ ይበላችሁ

አባቶቻችን ያወረሱን
የቡሄን ትርጉም ያሳወቁን
እንድንጠብቀው ለእኛ የሰጡን
ይህን ነውና ያስረከቡን

ለድንግል ማርያም አሥራት የሆንሽ
ቅዱሳን ጻድቃን የሞሉብሽ
በረከታቸው ያደረብሽ
ሁሌም እንግዶች የሚያርፉብሽ
ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ነሽ

ለሐዋርያት የላከ መንፈስ
ዛሬም ለኢትዮጵያ ጸጋውን ያፍስስ
በበጎ ምግባር እንድንታነጽ
በቅን ልቦና በጥሩ መንፈስ
በረከተ ቡሄ ለሁላችን ይድረስ

ዓመት ዓውደዓመት ድገም እና ዓመት ድገም እና
በጋሽዬ ቤት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ያውርድ በረከት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ወርቅ ይፍሰስበት ድገም እና ዓመት ድገም እና

በእማምዬ ቤት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ይግባ በረከት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ማርና ወተት ድገም እና ዓመት ድገም እና
ይትረፍረፍ በእውነት ድገም እና ዓመት ድገም እና

እንዲሁ እንዳላችሁ በፍቅር አይለያችሁ
ላመቱ በሰላም በፍቅር ያድርሳችሁ
ክርስቶስ በቀኙ በፍቅር ያቁማችሁ
የመንግስቱ ወራሽ በፍቅር ያድርጋችሁ
እንዲሁ እንዳለን በፍቅር አይለየን
ለዓመቱ በሰላም በፍቅር ያድርሰን
አማኑኤል በቀኙ በፍቅር ያቁመን
የመንግስቱ ወራሽ በፍቅር ያድርገን

የቅዱሳን መላክት የፃድቃን ሰማዕታት
ረድኤት በረከት ይግባ በሁሉም ቤት
በሁሉም ቤት *2* ይግባ በረከት *2*

እንቁም በሃይማኖት ፀንተን በትጋት
የአስራት አገር የአበው ቀደምት
የቅዱሳን አባቶች ትውፊት
ይገባልና ልንጠብቅ በእውነት
ባህላችንን የአባቶች ትውፊት *3*

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

15 Aug, 12:06


✞ገድለ ቅዱሳን✞, [8/7/19, 6:48 PM]
[ Forwarded from ✞ገድለ ቅዱሳን✞ ]
#ነሀሴ_1_ቀን_የምንጀምረው_የፍልሰታ ፆምም የበረከት ማግኛ እንዲሆን በትጋት
ልንፆመው ያስፈልጋል ።
@kegdlat
#የፍልሰታ ፆም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከተደነገጉት
ሰባት አፅዋማት መካከል አንዱ ሲሆን
#ፆመ_ፍልሰታ 👉 የዚህ ፆም ቀን የተወሰነ ሲሆን ከነሀሴ 1 ቀን እስከ ነሀሴ 15 ቀን ያለው ነው ። 👉 ይህ ፆም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መታሰቢያ ነው ። * እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም ለ64 አመት ያህል በምድር ላይ የኖረች ሲሆን... *... ስጋን የለበሰ ሁሉ ሞትን
መቅመስ አለበትና በእስዋና በልጅዋ ፈቃድ አርፋለች። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 👉 የፆመ ፍልሰታ ታሪክም በትንሳኤዋና
በእርገቷ ላይ ያተኩራል። * ይህም ቅዱሳን ሀዋርያት የእመቤታችንን አስከሬን ለመቅበር
እየሄዱ እያሉ ተንኮለኛ የሆኑ አይሁድ አይተው * ..ካሁን በፊት ልጅዋን ተነሳ እያሉ
አገራችንን እየበጠበጡ ይገኛሉ፣ ነገ ደግሞ እሷም ተነሳች ብለው ይረብሹናል *...በማለት በሰይፍ
አባረሯቸው ሲሸሹም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስከሬኗን ወስዶ በአፀ ህይወት ስር አኖረው። 👉ሀዋርያትም ሰዎች ስለ ድንግል ማርያም ቢጠይቁን ምን እንመልሳለን ብለው ተጨነቁ። በኋላም እግዚአብሔር ይህንን ሚስጥር እንዲገልፅላቸው ፆምና ፀሎትን ያዙ። 👉ሀዋርያት ፆምና ፀሎትን ሲጨርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የቅድስት ድንግል ማርያምን አስከሬን ሰጣቸው ። በዚህ ጊዜ ወስደው በጌቴሴማኒ በመቃብር አኖሩት። ++++++++
* በሶስተኛው ቀን በልጅዋ ስልጣን አርጋለች። እመቤታችን ስታርግ ቶማስ ለተልእኮ እንደሄደ ስላልተመለሰ
አልነበረም። * ሆኖም እመቤታችን ከሞት ተነስታ በክብር ስታርግ እሱ ደግሞ በተአምር
ደመና ጠቅሶ ከተልእኮው ሲመለስ ተገናኝተው ሰበን ለበረከት ሰጥታዋለች። * ይህንን የምስራች ለሐዋርያት ነግሯቸው ለማስረጃም ያህል ለበረከት የሰጠችውን ሰበን አሳይቷቸዋል ። * በዚህ ጊዜ የቶማስ እመቤታችንን የማየት እድል እንዲደርሳቸው
በድጋሚ ፆምና ፀሎት በመያዝ ለምነውታል። " * ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።" (የማቴዎስ ወንጌል 7:7) በሚለው አምላካዊ ቃል አምነው ጠየቁ። * የጠየቁትን የማይነሳ እግዚአብሔርም ለጥያቄያቸው መልስ ሰጥቷቸዋል። እመቤታችንንም ለማየት በቅተዋል። ++++++++++++
(ምንጭ ፣ ተአምረ ማርያም) + በመሆኑም ይህንን ድንቅ ነገር ለማሰብና የተሰወረውን ሚስጥር ሁሉ በቸርነቱ ለቤተክርስቲያን የተገለጠ እንዲሆን በማለት ምእመናን በየአመቱ
ፆመ ፍልሰታን ይፆማሉ። + እኛም ይህንን የፍልሰታ ፆም ስንፆም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከት እንዲያድርብን፣ እግዚአብሔር የሚስጥሩን በር እንዲከፍትልን፣ ለምነን እንድናገኝ ፣ + በፆም በፀሎት የሚገኘውን በረከት እንድንቀበል፣ እግዚአብሄር እንዲረዳን፣ መልካምና አስተዋይ ልቡና እንዲኖረን፣ የስጋ ፈቃዳችን እንዲከስም፣ እንዲሁም ****--***** @kegdlat @kegdlat @kegdlat
ስለሀገራችን፣ ስለሰዎች ስለመበለቶች፣ ስለ ድሀ አደጎች፣ ስለታመሙ፣ ስለተጨነቁ፣ + እንዲሁም አገልጋዮች በመልካም እንዲያገለግሉ በትጋት መፆምና መፀለይ ይገባናል። + ስለፅድቃችን አይደለም ስለ እግዚአብሔር ቸርነትና ምህረት ብሎ ይረዳናልና፣ ከኛ የሚጠበቀው
በተሰበረ ልብ ሆኖ መቅረብን ነው ። " +የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።" (መዝሙረ ዳዊት 51:17)
እግዚአብሔር በሰላምና በበረከት ይህንን ፆመ ማርያምን እንድንጠቀምበት ይርዳን። @kegdlat @kegdlat @kegdlat

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት, [8/9/19, 6:16 AM]
✞ ​​ድንግል ትንሳኤሽን

ድንግል ትንሳኤሽን እስከምናይ ድረስ
ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ
ለእኛ እስከሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት
አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምህረት /2/

ሞትን የረገጠ ልጅሽ ካንቺ ጋር ነው
ውጦ የሚያስቀርሽ የቱ መቃብር ነው
የዕርገትሽን ዜና ከቶማስ ሰምተናል
ትንሳኤሽ እውነት ነው ሰበንሽን አይተናል

ሞትማ በሞት ተሽንፏል
ባንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛል /2/

አዝ_______

ልናየው ወደድን የቶማስን ክብር
ለምን ተስወረን የትንሳኤሽ ምስጢር
በራችንን ዘግተን በፀሎት ወድቀናል
ተገልጠሽ አብሪልን ልጆችሽ ናፍቀናል

ሞትማ በሞት ተሽንፏል
ባንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛል/2/

አዝ________

መዝሙረኛ አባትሽ ዳዊት ጽፎልናል
ሞትን የማያይ ስው ማን አለ ብሎናል
ይህ እውነት በዘመን አንቺ ላይ ቢደርስም
በሞት ተሽንፏል መቃብር አይኖርም

ሞትማ በሞት ተሽንፏል
ባንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛል /2/

አዝ_________

ቶማስ ከደመናው ወርዶ ሲያናግረን
ስለ ሆነው ነገር እጅጉን ተመሰጥን
እኛም ይህን ክብር ተመኘን ለማየት
ድንግል አሳስቢልን ኪዳነ ምህረት

ሞትማ በሞት ተሽንፏል
ባንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛል/2/

መዝሙር
በሊቀ መዘምራን ዲ/ን ቴድሮስ ዮሴፍ
@senbetmezmurat

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

15 Aug, 12:04


ድንግል ወላዲተ ቃል

ድንግል ወላዲተ ቃል (፪)

አሟሟትሽ በጥር ነሐሴ መቃብር - - ድንግል
ያንቺ ለብቻ ነው ትንሳኤሽ ሲነገር - - ድንግል
ስጋሽ በምድር ላይ የታለ እንደፍጡር - - ድንግል
አርጓል ወደ ሰማይ ከክርስቶስ መንበር - - ድንግል

ድንግል ወላዲተ ቃል (፪)

ስጋሽን ሲያሳርጉ መላእክት ከሰማይ - - ድንግል
ቶማስ በደመና ሲመጣ መንገድ ላይ - - ድንግል
መግነዝ ተረከበ ለሐዋርያት ሊያሳይ - - ድንግል

ድንግል ወላዲተ ቃል (፪)

ትንሳኤሽን ሽተው ግራ ሲገባቸው - - ድንግል
ሐዋርያት ጾመው ተገልጥሽላቸው - - ድንግል
ተቀብራ አልቀረችም በምድር ከደጅዋ - - ድንግል
ወደላይ አረገች እርሷም እንደልጅዋ - - ድንግል

ድንግል ወላዲተ ቃል (፪)

ለማየት ሲጓጉ የድንግልን ትንሳኤ - - ድንግል
እርገቷን አወቁ በልዩ ሱባኤ - - ድንግል
እኛም እንጸልይ በራችንን እንዝጋ - - ድንግል
ከወላዲተ አምላክ እንድናገኝ ዋጋ - - ድንግል

                በሊቀ መዘምራን
           ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ
<< በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች>>
                መዝ ፵፬ ፥ ፱

💚 💚
💛 💛
❤️ ❤️

የሰንበት ት/ቤት መዝሙራት

25 Jul, 20:38


✞ አብሰራ ገብርኤል

አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
ወይቤላ (2) ትወልዲ ወልድ
ሚካኤል መላዕክ በክነፍ ፆራ
መንጦላዕት ደመና ሰወራ
ንፅህት በድንግልና አልባቲ ሙስና 
ተወልደ ወልድ እምኔሐ
         ትርጉም
ገብርኤል ማርያም አበሰራት አበሰራት
ወንድ ልጅም ትወልጃለሺ አላት
ሚካኤል መላዕክ  በክንፋ ከለላት
የሰማይ መጋረጃውን ሸፈናት
ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና

አዝ

አዳም በጥፋቱ ከገነት ሲባረር
በሚካኤል ክንፎች ቀድሞ አይቶሽ ነበር
ሔዋንን ሲጠራት ሕይወቴ ነሽ አላት
እንደሚድን አውቆ ድንግል በአንች ምክንያት

ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና
 
አዝ


እግዚአብሔር  የላከው የከበረው መላዕክ
ድንግል ሆይ ለክብርሽ ዐየን ሲንበረከክ
በፍቅር በትህትና በፍፁም ሰላምታ
የጌታ ሰው መሆን የነገረሽ በደስታ

ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና

አዝ

ደስተኛዬቷ ሆይ ደስ ይበልሽ ድንግል
የአብ ቃል ክርስቶስ ሥጋሽን ይለብሳል
አንቺም ትይዋለሽ ስሙን ኢየሱስ
መድኋኒት ነውና ለሥጋ ወነፍስ

ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና

አዝ


አንደ ኒቆዲሞስ ሳትከራከሪ
አንደ ዘኬርያስ ሳትጠራጠሪ
ይሁነኒ ብለሽ ቃልን ተቀበልሽ
ከፍጥረት ማነው አንቺ የሚመስልሽ

ንፅህት ናትና በድንግልና (2)
ጥፋት የለባትምና ወንድ ልጅም ወልዳልናለችና