ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

@poeteyobzmariam


...Poet, writer & film maker🎬🎥

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

18 Sep, 05:17


Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

11 Sep, 05:08


ጥሩ አመት አልነበረም ለኔ…

ድሮ “በጣም የምትፈራው?” ነገር ተብዬ ስጠየቅ “እናቴን ማጣት” የሚል ነበር መልሴ! የፈራሁት ነገር ደረሰብኝ!…እናቴን አጣሁ!

“አቢዬ በቅርብ እመጣለሁ አብረን እንኖረለን” ብላኝ ነበር እናቴ! እንደ እሷ ሀሳብ ቢሆን ኖሮ 2017ትን አብረን ነበርን! ግን አልሆነም!…2016 ላይ ቀረች! እግዚአብሔር የፈቀደው ሆነ!

ህይወትን ያለ እናቴ ተጋፍጫት አላውቅም!…አሁን ግን ልጋፈጣት ነው!…እንደማትመለስ ቁርጤን አውቅያለሁ!…ለበዓል “እንኳን አደረሰህ አቢዬ” እንደማትለኝ አውቅያለሁ!…”ፀጉርህን ስትስተካከል በጣም አስገብቶ ቅርፅ እንዳያወጣብህ” እንደማትለኝ አውቅያለሁ!…ለልደቴ “እንኳን ተወለድክ የኔ ልጅ” እንደማትለኝ አውቅያለሁ!”አንተ ብቻ ጠንክረህ ተማር እንጂ እኔ እናትህ እያለሁ ስለምንም ነገር እንዳትጨነቅ” እንደማትለኝ አውቅያለሁ ”ወድሀለሁ” እንደማትለኝ አውቅያለሁ! ካሁን በኋላ ምንም እንደማትለኝ አውቅያለሁ!

“ Nothing in life is promised except death” ይላል ካንዬ ዌስት! ትክክል ነው! እዚህ ምድር ላይ ከሞት በስተቀር ቃል የተገባልን ነገር የለም! ሞት ደግሞ መች እንደሚመጣ አይታወቅም!…በህይወት ሳላችሁ ተዋደዱ! በህይወት ሳላችሁ ተፋቀሩ! እናታችሁን እንደ ምትወዷት በየደቂቃው ንገሯት! ምንም ከምታደርጉላቸው በላይ ደስታቸው ለነሱ ይሄ ነው!

ሰማይ ቤት ባለሽበት መልካም አዲስ አመት እናቴ! ለራሴ ነው እንጂ ማዝነው ከዚህ ክፉ አለም ላንቺ የእመብርሀን እቅፍ እንደሚሻልሽ ጠፍቶኝ አይደለም!

ልቤ ውስጥ አይደል የቀበርኩሽ? መቸም አትበሰብሽም!!!

ወድሻለሁ!

ላማርር ፈልጌ አይደለም! እንዲሁ ልቤ ውስጥ ያለውን ላውጣው ብዬ ነው!

ነገር ሁሉ ለበጎ ነው!…ስለ ሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!!

መልካም አዲስ አመት🌼

©[Eyob Z Mariam]

@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

09 Sep, 06:35


🩸

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

31 Aug, 19:42


Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

30 Aug, 05:25


💧
Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

24 Aug, 02:34


Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

22 Aug, 19:38


Join

@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

01 Jun, 17:11


አመሰግናለሁ!

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

12 May, 18:50


Dear MAMA🖤

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

09 May, 12:56


🖤

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

08 May, 20:24


🦅

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

05 May, 04:34


ተነስቷል!!

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

04 May, 07:57


[በስቅለት ቀን ያጋጠመኝ አስገራሚ ክስተት]
:
መስገጃ ቦታ እንዳላጣ ብዬ በግዜ ብሄድም አልተሳካልኝም ነበር! የቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በሰው ተሞልቶ ጠበቀኝ! ምንጣፌን ይዤ በአይኔ ክፍት ቦታ ስቃኝ ያየኝ አንድ አስተባባሪ "ና ቦታ ልስጥህ" ብሎ ወደ አንድ ቦታ መራኝና "እዚህ ጋ ተቀመጥ" ብሎ በእጁ ጠቆመኝ! ልጁን አመስግኜ ምንጣፌን አንጠፍሁና የአቅሜን ከሰገድሁ በኋላ ትንሽ ረፍት ለመውሰድ ተቀመጥሁ!

ድንገት አንዲት ሴት አጠገቤ መጥታ ቆመች!ዕድሜዋ በሀያዎቹ አጋማሽ ላይ ነው!...በእጇ መስገጃ የሚሆናት ምንጣፍም ሆነ ምንም ነገር አልያዘችም!..ያደረገችውን ክፍት ጫማ አወለቀችና ጠጠሩ ላይ መስገድ ጀመረች!...የያዝኩት ምንጣፍ ሰፊ በመሆኑ ምንጣፉ ላይ ሆና እንድትሰግድ ነገርኳት!.."እሺ" ብላ አመስግናኝ ወደ ምንጣፉ ተጠጋች!...ፊቷን አየሁት!...ጉንጮቿ ደም መስለዋል..ሁለቱም አይኖቿ በዕንባ ብዛት በሚመስል መልኩ ቀልተዋል!...ደነገጥኩ!..."ምን ሆነሽ ነው?" ብዬ ልጠይቃት አልኩና "እኔ ማነኝ?" ብዬ መልሼ ተውኩት!...ተነሳሁና መስገድ ጀመርኩ!...ጎን ለጎን ሆነን መስገድ ጀመርን!...ብዙ ከሰገድኩ በኋላ ደከመኝና ተቀመጥሁ!...ልጅቷ ከገባች ጀምሮ አላረፈችም!...እየሰገደች ነው!...ድንገት ጎንበስ ስትል ዕንባዋ ምንጣፉ ላይ ጠብ ሲል ተመለከትሁ!...ድጋሚ ዝም ማለት አልቻልኩም!...እጇን ያዝ አደረኳትና "እህቴ እስቲ ትንሽ አረፍ በይ" አልኳት ዕንባዋን በነጠላዋ ጫፍ ጠራረገችና ተቀመጠች!..."ምን ሆነሽ ነው የኔ እህት...ምን ሆነሽ ነው ምታለቅሺው?" አልኳት!...ስጠይቃት ይበልጥ አለቀሰች!..."ማንም ምን ሆነሽ ነው ብሎ ጠይቆኝ አያውቅም እኮ" አለችኝ!..."እንዴት"? አልኳት...ረጅም አመት የምታውቀኝ ያህል አወራችልኝ!...ከእናቷ በቀር ምድር ላይ ማንም ዘመድ እንደ ሌላት አወራችልኝ!...እናቷ በጣም ሀብታም እንደ ነበረች አወራችልኝ!...እናቷ ከ 5 ወር በፊት እንደ ሞተች አወራችልኝ!...እናቷ ስትሞት የመኖር ትርጉም እንደ ጠፋትና ሱስ ውስጥ እንደ ተዘፈቀች አወራችልኝ!...በዕንባ ብዙ ብዙ ነገር አወራችልኝ!...ላቋርጣት አልፈለግሁም!...ዝም ብዬ ሰማኋት!...መጨረሻ ላይ ዕንባዋን ጠራረገችና ፈገግ ብላ..."ታውቃለህ" አለችኝ..."ታውቃለህ እናቴ ከሞተች በኋላ መጀመሪያ ግዜዬ ነው ቤተክርስቲያን ስመጣ!...በእርግጥ የመጨረሻዬም ነው!...የመጨረሻዬ ስግደትም ስለሆነ ነው ያለማቋረጥ ስሰግድ የነበረው ምን አልባት ቢምረኝ ብዬ!"...ብላ ትንሽ ዝም አለችና!..."ይቅርታ በማያገባህ ብዙ ጨቀጨኩህ!...አመሰግናለሁ ቻው በቃ" ብላኝ ተነስታ ሄደች!...ከሄደች በኋላ ስታወራቸው የነበረችው ነገሮች አይምሮዬ ላይ ማቃጨል ጀመሩ...

"ታውቃለህ እናቴ ከሞተች በኋላ መጀመሪያ ግዜዬ ነው ቤተክርስቲያን ስመጣ!...በእርግጥ የመጨረሻዬም ነው"

"የመጨረሻዬ ስግደትም ስለሆነ ነው ያለማቋረጥ ስሰግድ የነበረው.... ምን አልባት ቢምረኝ ብዬ!"

በድንጋጤ ከተቀመጥሁበት ተነሳሁ!...ከህዝብ መሀል በአይኔ ፈለኳት...በሩ አከባቢ ስትወጣ ተመለከትኩ...ጫማዬን እንኳ ሳላደርግ በፍጥነት ሄድኩ!
:
:
የመኪናዋን በር ከፍታ ልትገባ ስትል ደረስኩባት!...እጇን ይዤ አስቆምኳት...ወደ ኋላ ዞራ አየችኝ...

"እራስሽን ልታጠፊ ነው አይደል?" አልኳት!

ምንም ሳትናገር እጇን አስለቀቀችና መኪናዋ ውስጥ ገባች...ምንም ብናገር...ምንም ባወራ በዚህ ስሜት ሆና ማድረግ ከፈለገችው ነገር እንደማትመለስ አውቃለሁ...ብቻ ግን እግዚአብሔር አንደበቴ ላይ ቃላቶችን አስቀመጠ..

"እግዚአብሔር ከ እናትም ከ አባትም በላይ እንደ ሆነ አታውቂም?...ተስፋን የሰጠን የታመነ እንደሆነ አታውቂም?....ክርስቶስ ተሰቅሎ አለምን ባዳነበት ዕለት አንቺ ትሞቻለሽ?"...አልኳት!....ተንሰቅስቃ አለቀሰች!
:
:
መርሀ ግብሩ ካለቀ በኋላ ከማውቃቸው ደግ እማሆይ ጋ አገናኘኋት!...ፀለዩላት!...አረጋጓት!...እንደ እናት አቀፏት!...አባበሏት!..አይዞሽ አሏት!...

ዲያቢሎስ አስቦባት የነበረውን የሞትን ደብዳቤ ክርስቶስ ኢየሱስ በስቅለቱ ዕለት ሰቀለው!....ስሟን ጠየኳት!...ሩት አለችኝ....
:
ሩት!....በእግዚአብሔር ምህረት ከሞት እና ከዘላለማዊ እሳት ያመለጠች ነፍስ!

[እዮብ ዘ ማርያም]

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

24 Apr, 20:34


አይመስለኝም ነበር የምንረሳሳ
አይመስለኝም ነበር...
ልብሽና ልቤ በወረት ሚበሳ

ሁሉም ከንቱ ቀረ ተረሳሳን በቃ
የዘመናት ፍቅር ጠፋ በደቂቃ

እኔም ዘነጋሁሽ አንቺም ዘነጋሺኝ
በሌላ ተካሁሽ በሌላ ተካሺኝ

ያ ሁሉ መገዘት ያ ሁሉ መሀላ
ያ ሁሉ ቃል ማብዛት ሁሉ ሽንገላ
በቃ ለዚሁ ነበር?
ልብሽ ሊኮበልል እኔም ላቅፍ ሌላ?

የሚያስቀናው ፍቅር...
ሲታይ የሚመስለው ማይገኝለት አቻ
እዚህ ጋ ተቋጨ ሳይደርስ ዳርቻ
የኔና አንቺ ነገር ያሳዝናል ብቻ!

[Eyob  Z Mariam]

@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

12 Apr, 11:33


እንኳንም ኖርሺኝ🖤

join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

17 Mar, 19:37


(እንዲህ ናት የኔ ሴት)

ጾሜን አስገድፋ፣
አንጀቴን ስትበላ እሮብ አርብ የማትል
ሆዴን ምታላውስ ገብታ ልክ እንደ ትል
ቀጥ የምታደርገኝ...
ጉንጩን ዳበስ አርጋ "ወድሀለሁ" ስትል!

እንዲህ ናት የኔ ሴት...

ሀዘን ቅስሜን ሰብሮ ለፀፀት ሲሰጠኝ
መሰንበት ጠልቼ ትካዜ ሲንጠኝ
ፀጉሬን ደባብሳ...
የመኖርን ተስፋ ዳግም ምትሰጠኝ!

እንዲህ ናት የኔ ሴት...

በጠመመ ግዜ ጨርቄን ጥዬ ባብድም
የማደርገው ጠፍቶኝ በራሴ ላይ ባድም
መሰልቸት ደባብሷት፣
ትታኝ የማትሄድ አብራኝ ምትወድም!

እንዲህ ናት የኔ ሴት...

በማላቀው ጥፋት በስሜ ቢነገድ
ሊያጠፋኝ ቢነሳ አንድ ሙሉ ነገድ
ፈፅሞ ማትከዳኝ...
በሄድኩበት ሁሉ አብራኝ ምትሰደድ!

እንዲህ ናት የኔ ሴት..!!

እቴ የኔ አበባ፣
ዘመድ አዝማዶቼ መኖሬን ሳይሰሙት
ጠላቶቼ ሁሉ...
የኔን ደስታ ማግኘት ጭራሽ ሳይተልሙት
ፍቀጂልኝና፣
ካንቺ ጋራ ኖሬ ካንቺ ጋራ ልሙት!

(እዮብ ዘ ማርያም)

join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

10 Mar, 20:01


ለ እናቴ!

ይመስለኝ ነበረ፣
የልብ ሀሳብ ሁሉ በቃል የሚወጣ
አንቺ ጋር ስደርስ፣
ቃል ወዴት ገደመ ቃል ከወዴት ላምጣ?

ትሰቂያለሽ እኮ ልብሽ እያነባ
ህመምሽን አይቶ፣
ልጅሽ እንዳያዝን ሆዱ እንዳይባባ

ትስቂያለሽ እኮ፣
ሆድሽ እየራበው ጉሮሮሽ ተጠምቶ
ልጅሽ እንዲጠግብ፣
ልጅሽ እንዲረካ ያንቺ አካል ሳስቶ

ሰው ወረተኛ ነው ግብሩ ያስታውቃል
ቀን ሲጥል ይሸሻል ከሌላ ይጠጋል
በመዓልት አብርቶ ሌት ይጠወልጋል

ሰላም ላካላትሽ፣
ቀንን ተከትለው ወረት ለማያውቁ
ሰላም ለጥርሶችሽ፣
ስሜትን ሸሽገው ዘወትር ለሚስቁ

እማ ያንቺ ፍቅር፣
ከሀሳብ የሰፋ~ከጠፈር እርቀት እጅጉን የራቀ
ማይገቡት ጥልቅ ነው
ማይፈቱት ቅኔ ነው እጅግ የረቀቀ

አንቺ የገነት ቁልፍ፣
የእውነት መወጣጫ የህይወት መሰላል
ምድር ተዘቅዝቃ፣
ጉያዋ ቢፈተሽ አንቺን ማን ይመስላል?

የመኖር ፍቺ ነሽ፣
የህይወቴ ዝማሬ የነፍሴ በገና
እማ ክፉሽ ይራቅ፣
ግዜሽ ሁሌም ይኑር ሞት ባንቺ ይቅርና!

(እዮብ ዘ ማርያም)

Join
@Poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

04 Mar, 18:59


(መነሻ ሀሳብ …)

“You left and I cried tears of blood. My sorrow grows. Its not just that You left. But when You left my eyes went with You. Now, how will I cry? “
-Rumi -

(መልሽልኝ አይኔን)

ዛሬ ስትለዪኝ...
ልብሽ ከኔ ርቆ፥ ወደ ሌላ ሲበር
ማድረግ የፈለኩት...
አብሮ መብረር ሳይሆን፥ ማልቀስ ብቻ ነበር::

የልቤን አውጥቼ...
ግን እንደምን ላልቅስ፥ ዕንባ እንደምን ልዝራ
ማለቅስበት አይኔ...
ከኔ ተለይቶ ሄዶ ካንቺ ጋራ::

አላሳዝንሽም ?
ይዤ አልታይሽም ? ብሶት ሰቀቀኔን
እንዳለቅስ እንኳን መልሺልኝ አይኔን !

( እዮብ ዘ ማርያም )

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

02 Feb, 18:50


YOU ARE NOTHING WITH OUT ME🙂

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam

ግጥምና ወግ Eyob Z Mariam

31 Jan, 18:37


🗒🙂

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam