School of ጮራ

@millionsankara


Learning Corners
a special learning activity for primary, Secondary and Preparatory pupils which strongly promotes Independence and Love of Learning.
🦋🦋
#Schoolofጮራ

School of ጮራ

21 Oct, 10:06


የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደረገ።

የ2017 የቴክኒክና ሙያ የመደበኛ ስልጠና ዘመን መቁረጫ ነጥብ ዛሬ ይፋ ተደርጓል።

የመቁረጫ ነጥቡ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia

School of ጮራ

08 Oct, 16:41


#MoE

በ2017 የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም (Remedial Program) ለመከታተል የመቁረጫ ነጥብ ተወስኗል።

በዚህም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የወሰዱና እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 31% ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎች በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የሪሚዲያል ፕሮግራም መከታተል ይችላሉ ተብሏል።

በመንግስት ተቋማት ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ የሪሚዲያል ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

Via @tikvahuniversity

School of ጮራ

06 Oct, 19:35


#ATTENTION🚨

ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ? መደረግ ያለበት ጥንቃቄስ ምንድነው ?

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ምን አሉ ?

" ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ወይ ? የሚባለው ሰሞኑን በሙሉ ይሄን አይነት ንዝረቶች ነበሩ።

መሬት መንቀጥቀጥ መተንበይ የሚባል ነገር የለም ፤ የት አካባቢ እንደሆነ እንጂ መቼ ይከሰታል የሚባለውን መተንበይ አይቻልም።

ስለዚህ ሊከሰት ይችላል ሊመጣ ይችላል። ይሄ ሁል ጊዜ በተለይ አዲስ አበባ የምንኖር ሰዎች ነቅተን የምንጠብቀው ነገር መሆን አለበት።

ስምጥ ሸለቆና የስምጥ ሸለቆ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ነቅተን የምንጠብቀው ነገር ነው መሆን ያለበት።

ለጊዜው መናገር የምችለው ከበድ ያለ ነገር ከመጣ አይመጣም ብለን ነው የምንገምተው ከመጣ ግን ምን መደረግ ስለለበት ጥንቃቄ ነው።

➡️ የቤት ቋሚዎች በተለይ ኮንዶሚኒየም ህንጻ ላይ ያሉ ሰዎች ኮለኖች አካባቢ መጠጋት ለምን መውረድ ሊከብድ ይችላል ቁልፍ ማክፈትም ሊከብድ ይችላል። ስለዚህ ኮለኖች አካባቢ መጠጋት።

➡️ ከተቻለ ጠረጴዛ ስር መግባት።

➡️ ሊፍት አትጠቀሙ። ማንም ሰው በሊፍት ለመውረድ እንዳይሞክር። ያን እንዳትጠቀሙ።

ይሄን ይሄን ጥንቃቄ ማደርግ ያስፈልጋል። ነገር ግን አሁን ባለው እዚህ ደረጃ የሚያደርስ ከባድ ነገር አለ ብለን አንገምትም። "

#Ethiopia #AddisAbaba

@tikvahethiopia

School of ጮራ

06 Oct, 19:25


በመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ምን መደረግ አለበት?

ክፉውን ያርቅልንና ድንገት ከበድ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢከሰት እነዚህን ጠቃሚ መረጃዎች ማወቅ ይበጃል።

- መረጋጋት! ቤት ውስጥ ከሆኑ የመሬት መንቀጥቀጡ እስኪቆም ድረስ በዚያው በቤት ውስጥ ይቆዩ። ውጭ ከሆኑም ወደ ውስጥ ለመግባት አይሞክሩ እዚያው ይቆዩ።

- ቤት ውስጥ ከሆኑ በከባድ የቤት እቃዎች ( ጠንካራ ጠረጴዛ) ስር ይግቡ ያ ከሌለ በቤት ውስጥ በሚገኝ የውስጥ ግድግዳ ኮርነር ላይ ፊቶንና ጭንቅላቶን ሸፍነው ይቁሙ።

- ከመስኮቶች እና ከመሰበሩ መስታወቶች አጠገብ ይራቁ።

- ከቤት ውጭ ከሆኑ ከኤሌክትሪክ መስመሮች ወይም ሊወድቅ ከሚችል ማንኛውም ነገር ርቀው ክፍት ቦታ ላይ ይቆዩ።

- በውጪ የሚገኙ ከሆነ ከህንጻዎች አከባቢ ይራቁ

- ሻማ ወይም ማንኛውንም ተቀጣጣይ ነገር አይጠቀሙ።

- መኪና ውስጥ ከሆኑ መኪናውን ያቁሙ እና የመሬት መንቀጥቀጡ እስኪቆም ድረስ በመኪናው ውስጥ ይቆዩ።

- ሊፍት በፍጹም አይጠቀሙ ወደ ውጪ ለመውጣት ደረጃን ይጠቀሙ።

በቤታችን ለዚህ ብቻ ሳይሆን ለሌላም አደጋ የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ መስጫ ኪት ቢኖር ይመረጣል። እንዲሁም ስለመጀመሪያ የህክምና አሰጣጥ መሰረታዊ እውቀት መያዙም ይመከራል።

@tikvahethmagazine

School of ጮራ

15 Aug, 19:44


የ2017 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 18 እስከ ሰኔ 27 ድረስ ይሰጣል:- ትምህርት ሚኒስቴር



(ነሀሴ 9/2016 ዓ.ም ) ትምህርት ሚኒስቴር ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወጥ የሆነ የአካዳሚክ ካላንደር መተግባር እንደሚጀምር አሳወቀ።



በትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን ሐምሌ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተፃፈ ደብዳቤ ያመለክታል።



ደብዳቤው ከ2017 ትምህርት ዘመን ጀምሮ ወጥ የሆነ የአካዳሚክ ካላንደር በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መተግባር እንደሚጀምር ይገልፃል።


በዚህም፦


- የ1ኛ ዓመት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ፦ መስከረም 7 እና 8/2017 ዓ.ም


- የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ሁሉም መርሐግብር ተማሪዎች ምዝገባ፦ መስከረም 9 እና 10/2017 ዓ.ም


- የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ሁሉም መርሐግብር የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት መስከረም 13/2017 ዓ.ም ይጀመራል።


የ2017 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 18 እስከ ሰኔ 27 ድረስ ይሰጣል።




መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

School of ጮራ

12 Jul, 07:47


ማስታወቂያ

ለ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ/ Social ተማሪዎች

የተለያየ ንብረት( ሽቶ፣ ሎሽን፣ ሃብል፣ ጥላ ሰዓት፣ ቀለበት፣ የእጅ ጌጥ፣ ለውዝ ቅቤ፣ ቻፕስቲክ፣ እና የመሳሰሉትን) ት/ቤት አስቀምጣችሁ በዩኒቨርስቲ ፈተና በመውሰድ ላይ ለምትገኙት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ/ Social ተማሪዎች ንብረቶቻችሁን መውሰድ የምትችሉት ነገ ቅዳሜ ሀምሌ 6/2016 ዓ ም ጠዋት ከ 3:00 እስከ 4:00 ሰዓት ባለው ጊዜ ብቻ ይሆናል። በዚሁ አጋጣሚ የተፈጥሮ ሳይንስ / Natural Science/ ተማሪዎች እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩትን ነገሮች እንዳትይዙዋቸው ይሁን

https://t.me/millionsankara

School of ጮራ

10 Jul, 20:49


ውድ የተፈጥሮ ሳይንስ / Natural Science/ ተማሪዎች እነዚህን በደንብ አስተውሉ

~

🗝የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሐምሌ 6 እስከ 7 ቀን 2016 ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚገቡ ተገልጿል። የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 9 እስከ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናውን ይወስዳሉ። ት/ቤታችሁ መች እና ስንት ሰዓት ላይ እንደምትገቡ ይነግራችኋል።

🗝 የማህበራዊ ሳይንስ/ Social ተማሪዎች ከፈተና ሲመለሱ በደንብ መረጃ ጠይቃችሁ የሚያስፈልጉትን በሙሉ መያዝ ነው።

ናቹራሎች መልካም እድል ይሁንላችሁ። ምንም ነገር እንዳትረሱ አደራ🙏🙏👏

እናስታውሳችሁ👇

#መያዝ #የተፈቀደላችሁ

✡️አንሶላ፣ ብርድ ልብስ
✡️ትራስ ጨርቅ፣
✡️የማታ ልብስ፣
✡️ደረቅ ምግብ፣ በሶ፣ ቆሎ፣ ዳቦቆሎ፣ ኩኪስ
✡️ልብስ፣ቦርሳ፣
✡️የመፈተኛ Admission Card 
✡️ መታወቂያ ካርድ፣እርሳስ፣ላጲስ፣መቅረጫ
ባዶ ወረቀት፤መጽሐፍ
✡️ ዩኒፎርም ፣ ጫማ፣ 
✡️ የንፅህና መጠበቂያ፣ ሳሙና፣ የጥርስ ሳሙና፣ ብሩሽ እና ቅባት

❷፣
#መያዝ #የተከለከሉ

☸️ ማንኛውም የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ
☸️ የተፃፈበት ደብተር፣ ሃንዳውት እና አጠሬራ
✡️ የዕምነት መፅሃፍት
✡️ ቀለበቶች፣ ሀብሎች ፣ የጆሮ ጌጦች፣ የጸጉር ጌጦች
✡️ ሰዓት፣ የእጅ ጌጦች
✡️ ሽቶ፣ ሎሽን፣ ኩል፣ ሊፕስቲክ

እስቲ  አንዴ ከላይ ያሉትን መያዛችንን እና አለመያዛችንን ቼክ እናድርግ 👏👏👏👏👏

https://t.me/millionsankara

School of ጮራ

04 Jun, 15:13


ተማሪዎች በበይነ መረብ መፈተናቸው ስህተትን መቀነስን ጨምሮ በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ።

የበይነ መረብ ፈተና ለስህተት በር አይከፍትም

የበይነ መረብ ፈተና አንድ ጥያቄ ሳይመልሱ ወደ ፈለጉት ጥያቄ በአንድ Click የመሔድ እንዲሁም ተመልሰው መስራት የሚፈልጉትን ጥያቄ Flag በማድረግ ተመልሶ የመስራት ዕድልን ይሰጣል።

ጊዜ ቆጣቢ ነው

በአንድ Click የፈተና ጥያቄን መልስ ለመስጠት ያስችላል። እንዲሁም ምን ያህል ደቂቃ እንደተጠቀሙ ከመፈተኛ ስክሪን ላይ ማየት ስለሚቻል ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም ያስችላል።

የተሻሻለ የመረጃ ቋት አለው

የበይነ መረብ ፈተናዎች በቂ የፈተና መረጃዎችን ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በማከማቸት ለተፈታኞች አመጣጥኖ ያቀርባል፡፡

የተሰሩ ጥያቄዎችን መልስ በፍጥነት በራሱ ይልካል

በፈተና ወቅት ጥያቄዎቹን ሰርተው ሳያጠናቀቁ የተሰጠው ደቂቃ ካለቀ የሰሩትን በጠቅላላ በራሱ በፍጥነት ይልካል።

ፈጣን ግብረ መልስ ይሰጣል

በበይነ መረብ ፈተናዎች ሲሰጡ ውጤታቸው ከሌላው ጊዜ በተለየ ፈጥኖ የመታወቅ ዕድል ይሰጣል።

ተማሪዎች በቤታቸው እያደሩ እንዲፈተኑ ዕድል ይሰጣል

ትምህርት ቤቶች የተደራጀ የኮምፒውተር ቤተሙከራ ካላቸውና የመፈተኛ ክላስተር ለመሆን አስፈላጊውን መስፈርቶች ማሟላታቸው ከተረጋገጠ ተማሪዎች በተማሩበት ትምህርት ቤት ሆነው እንዲፈተኑ ዕድል ይፈጥራል። #MoE

@tikvahuniversity

School of ጮራ

29 Apr, 13:47


#Update

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።

የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።

በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል። 

መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።

@tikvahethiopia

1,382

subscribers

603

photos

1

videos