በኢየሱስ የሸንጎ አደባባይ የታየው በአንድነት ወንበዴን የመደገፍ ጩኸት፤ ከውስጥ በኩል ያለ የክፉ መናፍስቶች ደጉን የማፍረስ መናበብ ምሳሌ ነው፡፡ አስታውሱ! ጌታ
ለሚጮኹበት ካህናትና አይሁዳውያን አስቀድሞ እንዲህ ብሏቸው ነበረ፤ "እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ" (የዮሐንስ ወንጌል 8፥44)
በነዚህ ሰዎች አድፍጦ ያለው የዲያቢሎስ መንፈስ፤ ዘር ሆኖ እየተወራረሰ አብሮ በመወለድ፤ እንደ አባት እየመራ ለክፋት አሳድጎ ለክፋት በማኖር፤ ምቹ ጊዜና ቦታን ባገኘበት ዕድል ላይ፤ መልካም ክርስቶስን ለማስወገድ በከሳሾቹ ሕሊና እጅ ለእጅ በመያያዝ፤ በአንድ ጫና የተገፋ የአንደበት ድምፅን በሁከት አሰማ፡፡
መናፍስት አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ባልተለየ ጽኑ ሃይማኖታዊ አኗኗር ሲመላለስ፤ ጥብቅ የቅድስና ሰንሰለት ከመለኮት ኃይል ጋር እንደሚኖረው ያውቃሉ፡፡ ስለሆነ ግለሰቡን በግል ፈተና በማሰናከል የጽደቅ ትስስሩን ለመቁረጥ ካልቻሉ፤ በሥጋ ዓለም ባለ የእርስ በእርስ መናበብ አንድ ሆኖ በመምጣት፤ የሰዎችን ብዙ ቁጥርነት ምሽግ ያደረገ መልካሙን አፍራሽ የተንኮል ተኩስ ይተኩሳሉ፡፡ ዲያቢሎስ ላይ ንቃተ ሕሊና አግኝታችሁ በተግባራዊ መረጃ በመታገዝ የእምነት ኃይል ላይ በመቆም፤ ብርቱ የዕለት አምልኮተ እግዚአብሔርን የጀመራችሁ ሰዎች በብዙ የምትቸገሩበት አንደኛው ጉዳይ፤ አስቀድሞ በጌታችን ላይ የደረሰው የክፉ መናፍስት መልካሙን ለመቃወም መናበብ የሚባለው ጉዳይ ነው፡፡
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
ከ መልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ
11/02/2017 ዓ.ም
ከሕይወት ተራራ ላይ መንፈሳዊነት ይብለጥ!
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯