Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

@guragez


# ይህ የዘቢዳር ቻናል የሀገራችን ብሎም የጉራጌ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካ፣ ኪነ ጥበብ፣ ታሪክ፣ ርዕዮት እና ሁለንተናዊ መልክ የሚዳሰስበት የመገናኛ የመወያያ እና የመጦመርያ አውድ ነው!

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

22 Oct, 15:15


#የሸማ ተራው #የእሳት ቃጠሎ አደጋ አስመልክቶ የተለያዩ ኃላፊነት የጎደላቸው ፅሁፎችና መልዕክቶች አይተናል።

ህንፃውን ያቃጠለው #መንግስት ከሚለው ጀምሮ እንኳን ተቃጠለ፣ ያቃጠልነው እኛ ነን የሚሉ ግለሰቦች ሳይቀር በአደባባይ ማየት ተችሏል።

ከሁሉም አስገራሚው ግን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ (ኦፌኮ) #ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ግርማ ጉተማ (እራሳቸውን አባ ጨብሳ እያሉ ይጠራሉ) ያሰፈሩት አስተያየት ብዙዎችን ያሳዘነና ያስደነገጠ ሆኗል።

ሰውዬው ያሰፈሩት ሃሳብ ከላይ በምስል ተያይዟል። በዚህ ዙሪያ አቶ ግርማም ሆነ የሚመሩት #ፓርቲ ማብራሪያ ሊሰጡ አይገባም ትላላችሁ?

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

22 Oct, 07:25


አስቸኳይ መልሶ ማቋቋም ለወገኖቻችን!!!

የመርካቶው ውድመት የብዙዎች የህይወት ዘመን ጥሪት ወደ አመድነት የቀየረ ክስተት ነው። በዚህ ሰዓት በርካቶች የሚይዙት የሚጨብጡት አጥተዋል።

አላስፈላጊ ጣት መጠቋቆም ንብረቱ ለወደመበት ወገን የሚፈይደው ነገር የለም። ትኩረታችን ሁሉ መልሶ ማቋቋም ላይ ይሁን። የከተማ አስተዳደሩም አደጋው ያደረሰው ጉዳት መረጃ ከማሰባሰብ ጎን ለጎን የተቀናጀ የመልሶ ማቋቋም ስራ ይጀምር።

የመንግስት ቀና ድጋፍና አመራር ካለ ወገኖቻችንን በአጭር ጊዜ መልሶ ማቋቋም ይቻላል። ባለሃብቱና መላው ህዝብ ቀና ትብብር እንደሚያደርግ አያጠራጥርም። የመንግስት አቅምና ቁርጠኝነትም የሚለካው አደጋው ለመቆጣጠር ካደረገው ጥረት ይልቅ ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም በሚያደርገው ጥረት እና ስኬት ልክ መሆን አለበት።

ትኩረታችን ሁሉ አስቸኳይ መልሶ ማቋቋም ለወገኖቻችን የሚል ይሁን!

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

18 Oct, 14:23


የሚሰሩ እጆችን እናበረታታ!

ይህ ማስታወቂያ በሐዋርያት ከተማ ተደራጅተው በእንጨትና ብረታ ብረት ስራ የተሰማሩ ወጣቶችን ለማበረታታት ያለምንም ክፍያ የተሰራ ነው። እርሶም በማጋራት የበኩሎን አስተዋፅዖ ያድርጉ🙏

በምሁር አክሊል ወረዳ ሀዋርያት ከተማ በፈርኒቸር እና በብረታ ብረት ስራዎች ቀዳሚ የሆነው ይናም ቲናም የቤት እና የቢሮ እቃዎች ማምረቻ ለደንበኞቹ እጅግ ጥራት ያላቸውን የአልጋ፣ ብፌ፣ ቁም ሳጥን፣ የምግብ ጠረጴዛዎችና ወንበሮች፣ የህንፃ በሮች፣ የህንፃ መስኮቶች፣ የህንፃ የውስጥ ለውስጥ ታሙቡራታ በሮች፣ የግቢ ኢሚቴሽን በሮች እንዲሁም ጥራት ያላቸው የቢሮ መደርደሪያ ሼልፎች በጥራት እንሰራለን ይላል።

ይናም ቲናም የቤት እና የቢሮ እቃዎች ማምረቻ ፤ ቤታችንን በምን እናስውበው ብለው እንዳይጨነቁ እኛ እንጠበብበታለን ስራን ማክበር ዋናው መገለጫችን ነው ደንበኞቻችንን በማክበር ፍላጎቶቻቸውን ማሟላት ከምንም ነገር በላይ ትኩረት የምንሰጠው ነገር ነው።

አድራሻ፦ሀዋርያት ከአብይተም ሆቴል ጎን
ስልክ ቁጥር +251911581968/+251943096948
ስራ አስኪያጅ አህመደል ተሰማ

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

18 Oct, 08:08


በምስራቅ ጉራጌ ዞን ጥያ ከተማ 3 ሰዎች ታግተው ሲወሰዱ አንድ የባንክ ጥበቃ በጥይት ተመቶ ቆስሏል።

#ዘቢዳር_ሚዲያ:- ጥቅምት 08/2017

"በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል" በምስራቅ ጉራጌ ዞን በሶዶ ወረዳ #ጥያ #ከተማ ላይ ጥቅምት 05 ቀን 2017 በግምት ከምሽቱ 4:00 ሰዓት አካባቢ ታጣቂዎች የግለሰቦች ቤት በመግባት 3 የአካባቢውን ነዎሪዎች አግተው ወስደዋል።

ታጋቾቹም አንድ #መምህር ፣ አንድ የሃይማኖት አባት እና አንድ መንግስታዊ ባልሆነ በጎ አድራጎት ድርጅት (World Vesion) በጥብቅ ስራ ተቀጥሮ በመስራት ላይ የነበረ ግለሰብ ሲሆኑ በከተማው የሚገኘው የንብ #ባንክ ለመግባት ሞክረው ሳይሳካላቸው ቢቀርም የባንኩን የጥበቃ ሰራተኛ በጥይት አቁስለውት ተሰውረዋል።

በሌላ መረጃ በተመሳሳይ ሰዓት በወረዳው #ሱተን በሚባለው ከተማ ታጣቂዎቹ ጥቃት ለመፈፀም ሞክረው የነበረ ቢሆንም የአካባቢው ነዋሪ አፀፋ በመመለሱ የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ታጣቂዎችን ማባረሩ ታውቋል።

በአካባቢው መከላከያ ሠራዊት እንዲሰፍር ከተደረገ በኃላ በአንጻራዊነት መረጋጋት ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ችግሩ እልባት ሳይሰጠው #መከላከያ ሠራዊት እንዲወጣ መደረጉ ለታጣቂ ቡድኖች መልካም አጋጣሚ ፈጥሮላቸዋል ሲሉ ዘቢዳር ያነጋገረቻቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ገልፀዋል።

ከአምስት ቀን በፊት በዚሁ ወረዳ #አማውቴ ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ አንድ አዛውንትና ለጥየቃ የመጣች ሴት ልጃቸው በእነዚሁ ታጣቂ ቡድኖች መገደላቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

Zebidar Tube/ ዘቢዳር ቲዩብ

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

18 Oct, 08:07


የኢትዮ ቴሌኮም ሼር መግዛት ያዋጣል/አያዋጣም?
/መላኩ ይርዳው/

የኢትዮ ቴሌኮምን ሼር አዋጭነት በተመለከተ አንዳንድ የተሳሳቱ ትንተናዎች እና የተዛቡ ቁጥራዊ መረጃዎች ሲዘዋወሩ አይቻለሁ!

ኢትዮ ቴሌኮም ባለፈው ዓመት (2016) ገቢው 93.7 ቢሊየን የነበረ ሲሆን ከታክስ በፊት የነበረው ትርፍ 90.7 ቢሊየን ነው። በበጀት ዓመቱ ደግሞ 27.2 ቢሊየን ታክስ ከፍሏል። ከታክስ በኋላ ያለው የተጣራ ትርፍ 63.5 ቢሊየን ነው።

ከ93.7 ቢሊየን ገቢው ውስጥ ወጪው 3 ቢሊየን ብቻ የሆነው ተቋሙ ሸቀጥ አምርቶ ወይም ገዝቶ የሚሸጥ ስላልሆነ እና የሚሸጠው አገልግሎት ከዚህ ቀደም በዘረጋው መሰረተ ልማት፣ ቴክኖሎጂና እውቀት በመሆኑ ነው። ይህ የተቋሙ ውጤታማነት (efficiency) ማሳያ ሆኖ ሊቀርብ ይችላል።
***
ለኢንቨስትመንት ውሳኔ የሚረዳውን ስሌት ስናይ -

ዛሬ ላይ ያለው የተቋሙ የተጣራ ሀብት (owner's equity) 113.5 ቢሊየን ነው። ነገር ግን ድርሻውን ለገበያ ሲያቀርብ ተቋሙ ድጋሚ ቢገመት ዋጋው 300 ቢሊየን ይሆናል ብሎ ነው የተነሳው። አንድ ሰው/ድርጅት ንብረቱን ሊሸጥ ገበያ ቢያወጣ ለንብረቱ ዋጋ የሚያወጣው ሻጩ ስለሆነ ኢትዮ ቴሌኮም ራሱ ላይ የፈለገውን ዋጋ የመለጠፍ መብት አለው። ይሄ ዋጋ ተወደደ/አልተወደደም? ዋጋ ያወጠው (የተመነው) በዘፈቀደ ነው ወይስ አስጠንቶ? ያጠናውስ ማን ነው? ያጠናው አካል ሙያዊ መርህን ተከትሎ ነው ወይስ ካይከተል? ... ብሎ መጠየቅ ያለበት ገዢው ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮ ቴሌኮም አሁን ላይ 100.7 ቢሊየን እዳ ስላለበት ሼር ገዢው እዳውንም በድርሻው ልክ አብሮ ይወርሳል ማለት ነው።

ከትርፍ አንጻር
ተቋሙ ለሽያጭ ያቀረበው የሼር ዋጋ የ300 ቢሊየን 10% (30 ቢሊየን) ነው።

ከላይ በገለጽኩት ያለፈው ዓመት ትርፍ መሰረት የሼር ባለቤቶች የሚያገኙት ትርፍ (earning per share) 63.5÷300 = 21.2% ነው። የ1 ሚሊየን ሼር የገዛ ሰው 212,000 ብር ትርፍ (dividend) ያገኛል ማለት ነው። ይህ ትርፍ ለካፒታል ማሳደጊያ ካልዋለ 10% ታክስ ተቆርጦ 190,800 ብር ይከፈለዋል። ትርፍ ከተከፋፈለ 10% ተክስ ስለሚቆረጥበት በባለድርሻው ኪስ የሚገባው ትርፍ ከ21.2% ወደ 19% ዝቅ ይላል። ትርፉ ካልተከፋፈለና ለካፒታል ማሳደጊያ ከዋለ ከሼር ድርሻ የሚገኘው ትርፍ ላይ የሚቆረጠው ታክስ አይቆረጥም።
****
በጥቅሉ ስናየው ከሼር 21.2% ትርፍ ማግነት ትንሽ አይደለም። አንድ ሰው ሳይሰራ ሳይደክም፣ ሳይወጣ ሳይወርድ፣ ቀበሌና ክ/ከተማ ሳይሄድ፣ የሰው ፊት ሳይገርፈው፣ ከሰራተኛ ጋር ሳይጨቃጨቅ በዓመት የኢንቨስትመንቱ 21.2% ትርፍ ካገኘ አዋጭ አይደለም ማለት አይቻልም። ሆኖም በሀገሪቷ ከ35% በላይ ትርፍ የሚያስገኙ ድርጅቶችም አሉ። አንድ ኢንቨስተር 35% ትርፍ የሚያስገኝ ድርጅት እያለ ለምን 21.2% ትርፍ የሚያስገኝ ድርጅት ላይ ኢንቨስት አደርጋለሁ ሊል ይችል።

ነገር ግን ዛሬ 35% ትርፍ የሚያስገኘው ድርጅት የትርፋማነቱ ዘላቂነት እና የህልውናው ቀጣይነት እንዲሁም ዋጋው የማደጉ እድል (appreciation tendency) ከ21.2 ፐርሰንቱ ወይም ከዚያም በታች ከሆነው ድርጅት ሊያንስ ይችላል። ስለዚህ የኢንቨስትመን ውሳኔ ሲወሰን እነዚህ ነገሮች ከግምት ገብተው መሆን አለበት።

ኢትዮ ቴሌኮምን ስናይ ለዘመናት ያካበተው መልካም ስም ያለው ሀገር የምትመካበት ግዙፍ ተቋም ነው። ከቅርብ አመታት ወዲህ በውድድር አልፎ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችልም አሳይቷል። በቅርብ አመታት ያሳየው የአገልግሎት ጥራት እድገት ተቋሙ ብዙ እምቅ አቅም እንዳለው ማሳያ መሆን የሚችል ነው።ከዚህ አንጻር ይህ ተቋም ላይ የሚፈስ ሀብት ከዓመት ትርፍም ባሻገር እንደ አስተማማኝ ጥሪት ሊወሰድ የሚችል ነው።

እንደ ስጋት ሊቀርብ የሚችለው የተቋሙ 50%+1 ባለድርሻ መንግስት እንደ መሆኑ በተቋሙ ላይ ውሳኔ የሚሰጠው መንግስት ነው። አለም ላይ ባለው ተሞክሮ መንግስት የቢዝነስ ተቋማት የመምራት ስኬቱ አናሳ ነው። ሌላው መንግስት የፖለቲካ ተቋም በመሆኑ በዚህ ተቋም ላይ የሚወስናቸው ውሳኔዎች ከbusiness perspective እና ከባለድርሻዎች ጥቅም አንጻር ብቻ የተቃኙ ላይሆኑ ይችላሉ። መንግስት ለፖለቲካዊ አላማ የተቋሙን ዋጋ ባልተገባ መልኩ appreciate ወይም deppreciate ሊያደርገው ይችላል። የተቋሙ ቢዝነስ ስትራቴጂ መንግስት በተቋሙ ላይ ያለው ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ስለሚሆን ያ ስትራቴጂ ተቋሙን በሚገባው ልክ የማያሳድግ ሊሆን ይችላል። ይህ ባለድርሻዎችን ይጎዳል።

በእኛ ሀገር ነባራዊ ሁኔታ ከመንግስት ጋር በሽርክና መስራት አዋጭ ነው? ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ማድረግስ አበረታች ነው? የሚሉትን ጠያቄዎችም ለኢንቨስተሮቹ ውሳኔና ምርጫ የሚተዉ ናቸው።

Zebidar Tube/ ዘቢዳር ቲዩብ

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

12 Oct, 12:38


በታጣቂዎች አባት እና ልጅ ተገደሉ።

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በሶዶ ወረዳ አማውቴ ቀበሌ ልዩ ስሙ ሙራጌ በሚባለው መንደር ታጣቂ ቡድን በአባት እና ልጅ በመግደል ዝርፊያ መፈፀሙ ተሰምቷል።

ታጣቂ ቡድኑ ከዚህ ቀደምም ሶዶ ወረዳዎች ከኦሮምያ ክልል በሚያዋስንባቸው አጎራባች አካባቢዎች ላይ ተደጋጋሚ ሰብአዊና ቁሳዊ ጥቃቶችን እያደረሰ መሆኑን ይታወቃል።

ከዚህ ቀደም "የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር በአካባቢው መንግስት "ኦነግ ሸኔ" እያለ የሚጠራው ቡድን እየተንቀሳቀሰና ጥቃቶችን እየፈፀመ እንደሆነ የገለፁ ቢሆንም እስካሁን ግን ይህ ነው የሚባል እርምጃ በመንግስት በኩል አልተወሰደም።

Zebidar Tube/ ዘቢዳር ቲዩብ

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

11 Oct, 03:39


#እህታችን_ያለችበት_ሁኔታ_ ልብ_ይነካል_ሼር_በማድረግ ተባበሩን

በጭንቅላት ዕጢ ምክንያት ሁለቱም አይኖቼ ማየት አቁመዋል!!

ቤተሰብ ዘመድ አዝማድ የሌላት ገነት ብርሃኔ አይኖቼ ማየት ካቆሙ ሰባት ወራት አስቆጥሯል። ተኝቼ ካለሁበት ክፍል ሰዉ ነዉ ለሽንት የሚያወጣኝ።

በመስተንግዶ ህይወቷን ትመራ የነበረችዉ እቺ ምስኪን ወጣት ዛሬ ላይ አይኖቿ ተይዞ እንደፈለገች ተንቀሳቅሳ መስራት አልቻለችምና ከተኛችበትና ከበሽታዋ ታክማ ትድን ዘንድ የሁላችንም እገዛ ያስፈልጋታል።

የጭንቅላት ዕጢዉን ለመታከም ማንም የሚደግፈኝና የሚረዳኝ ሰዉ የለምና የኢትዮጵያ ህዝብ ይድረስልኝ እያለች ትማጸናለች።

በጭንቅላት እጢ በሽታ የመጣ ሁለቱም አይኖቿ ማየት አቁመዋል።

ታማሚ እህታችን ገነት ብርሃኔ ነዋሪነቷ ወልቂጤ ከተማ ሲሆን አሁን ላይ መስተንግዶ ትሰራበት በነበረዉ ደሴ ሆቴል አንድ ክፍል ማረፊያ ተመቻችቶላት ተኝታ የኢትዮጵያን ህዝብ አድንኙ እያለች ትማጸናለች።

መርዳት ለምትፈልጉ ደጋግ ኢትዮጵያዉያን በራሷ ስም በተከፈተ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካዉንት ድጋፍ እንድታደርጉላት እኔም እማጸናችሁላዉ።

CBE __1000138365477 (ገነት ብርሃኔ)

ስልክ
0965408730 ( ደዉሎ ማናገር ይቻላል)

ሰጪ እጆች በፈጣሪ ዘንድ ትልቅ ቦታ አላቸዉ።

Zebidar Tube/ ዘቢዳር ቲዩብ