የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

@ethzema


ኢዜማ ኢትዮጵያ የሁሉም ዜጎች መብት የተከበረባት፣ ማኅበራዊ ፍትህ የሰፈነባት ሰላማዊ እና የበለፀገች ሀገር እንድትሆን የሚሠራ ሀገር አቀፍ ፓርቲ ነው።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

21 Oct, 04:35


የ #ኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐላፊ ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ በተለያዩ ወቅታዊ እና የፓርቲው ጉዳዮች ላይ ከአሻም ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ አድርገዋል፤ የተያያዘውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ይመልከቱ

https://youtu.be/T17lZVp8Oec

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

18 Oct, 15:00


የ #ኢዜማ ም/መሪ ዮሐንስ መኮንን ሀገራችን በማካሔድ ላይ በምትገኘው የሀገራዊ ምክክር ሒደት ላይ ከኢሳት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ይመልከቱ

https://youtu.be/HG8tLhJHE3s?si=z8oEvoX8HqoQZ-Dቆይታን

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

04 Oct, 15:16


የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የኢሬቻ በዓልን ለምታከብሩ በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም እና የፍቅር እንዲሆን ይመኛል።

partiin lammiilee itiyophiyaa haqaa hawaasummaaf lammiilee ayyaana irrechaa kabajaan hundaaf baga nagaan geessan jechaa ayyaanni kun kan nagaaf jalaala akka isiniif ta'u hawwina.

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

02 Oct, 08:42


ህዝባዊ በዓላት የፖለቲካ መድረክ ሊሆኑ አይገባም!

ፓርቲያችን #ኢዜማ በመርኆዎቹ ካስቀመጣቸው መሠረታዊ ሐሳቦች መካከል አንዱ “ኢትዮጵያ ልንንከባከበው የሚገባን ባለ ብዙ ባሕል፣ ታሪክ እና ቅርስ ባለቤት የሆነች ሀገር መሆኗን ከልብ እናምናለን” የሚል ነው። እነዚሕን ባሕል፣ ታሪክ እና ቅርሶች በተሻለ ደረጃ ለመጠበቅ ለማቆየት እና ለማጎልበት የመንግሥት፣ የማኅበረሠቡ እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት መሆኑን እና እነዚህም የጋራ ማንነት ለመፍጠር ያላቸውን አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ አንዳች ጥርጥር የለውም።

እነዚህ የጋራ ማንነትን በመፍጠር ሚናቸው ከፍተኛ የሆኑ ባሕሎችን በእኩል መንከባከብ እና ማሳደግ ተገቢ እና የሚበረታታ ነው። ነገር ግን ሀገራችን ባላት ስሁት ፌደራላዊ የመንግሥት ስሪትን በመንተራስ መሠል ባህሎችን የጋራ ማንነት ማጠንከሪያ ምሰሶዎች ከማድረግ ይልቅ የፖለቲካ ውግንና እና ትርፍ መሸቀጫነት ለማድረግ ሲሞከሩ ማየት የሚያሳዝን ነው፡፡ ልንከባከባቸው ልናሣድጋቸው እና በደማቅ ሁኔታ ልናከብራቸው ከሚገቡ ባሕሎች መካከል አንዱ በቅርብ ቀን የሚከበረው ኢሬቻ መሆኑን ኢዜማ ያምናል።

መንግሥት ከባሕል፣ ታሪክ እና ቅርሶች ጉዳይ ጋር በተያያዘ ዋነኛ ኃላፊነቱ የሆነውን እነኚህን ለማሳደግ፣ ለመጠበቅ እና ለማጎልበት የሚረዱ የሕግ ማዕቀፎችን እና ፖሊሲዎችን ማውጣትና መተግበር፣ ግንዛቤ መፍጠር እና ለቅርሶቹ አስፈላጊውን ጥበቃ ማድረግ እንዲሁም ባሕሎቹ ሲከበሩ ያለምንም ስጋት ተከብረው እንዲጠናቀቁ የጸጥታ እና ደኅንነት ሥራን መሥራት ብቻ ነው። ሆኖም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለይም ኢሬቻን በማክበር ሒደት በመንግሥት መዋቅሮች እና በመንግሥታዊ ኃላፊነት ቦታ ላይ የተቀመጡ ባለሥልጣናት ባሕሉ ካለው ሕዝባዊ እሴት ባፈነገጠ መልኩ ባሕሉን ከሕዝቡ ባለቤትነት ነጥቆ ፖለቲከኞቹ ዋነኛ አጋፋሪ ሆነው መምጣታቸው በሌሎች ዘንድ የመገለል እና የስጋት ስሜት ይፈጥራል። ገዢው ፓርቲም በዚህ መልኩ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት በሚመስል መልኩ መንቀሳቀሱ ተገቢ አይደለም ብለን እናምናለን።

በተለይ ለባሕሉ ተብሎ በተለያዩ አካባቢዎች ከተቋማት እና ከንግዱ ማኅበረሠብ በድጋፍ ስም በመንግስት መስሪያ ቤቶች ደብዳቤ የንግድ ማኅበረሠቡን በሚያስጨንቅ እና ከአቅም በላይ የሆነ ከፍተኛ አስገዳጅ የገንዘብ መዋጮ መጠየቅ ማኅበረሠቡን ከፍተኛ ምሬት ውስጥ በመክተት ባሕሉን በስጋት እንዲመለከተው እያደረገ ይገኛል።

የባሕሉ ባለቤት የሆነው ሕዝብም ተቋማትን እና ግለሰቦችን አስጨንቃችሁ መዋጮ በመሰብሰብ በዓሉን አድምቁልኝ አይልም፤ ይህንንም ሕገወጥ ተግባር የሚጠየፈው መሆኑን አንዳች ጥርጥር የለንም። በመሆኑም የየትኛውንም ማኅበረሠብ ባሕላዊም ሆነ ሃይማኖታዊ በዓል ለፖለቲካ ፍጆታ ማዋል ባሕሉን መበረዝ እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል። ይህን መሰል የአደባባይ ክብረ በዓላት ለየትኛውም አይነት የፖለቲካ አጀንዳ ማራመጃነት መጠቀምን ፓርቲያችን ፍፁም የሚያወግዘው ነው።

በመሆኑም በንግዱ ማኅበረሠብ ላይ እየተደረገ ያለውን ተጠያቂነት የሌለበት ሕገወጥ ጫናን ጨምሮ ሌሎች አስገዳጅ ድርጊቶችን መንግሥት በቶሎ እንዲያቆም እያሳሰብን መንግሥት ባሕሎችን ጠንቅቆ ለሚያውቀው ማኅበረሠብ በመመለስ መሠረታዊ ስንል ከላይ የጠቀስናቸውን ኃላፊነቶቹን ብቻ በቅጡ እንዲወጣ እንጠይቃለን።

መስከረም 22/2017 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

28 Sep, 06:17


የመርኃግብር ማሥታወሻ!

"የኮሪደር ልማቱ ከከተማ ልማት እና ከሕግ አንፃር ሲዳሰስ"


👉 አቅራቢዎች:

ዮሐንስ መኮንን (የ #ኢዜማ ም/መሪ)

እዮዔል ሰለሞን (የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት ፅ/ቤት ኃላፊ)

👉 ቀን: ዛሬ ቅዳሜ መስከረም 18/2017 ዓ.ም.

👉 ሰዓት: ከቀኑ 8:00

👉 ቦታ: ስታዲየም አከባቢ በሚገኘው የኢዜማ ዋና ጽ/ቤት

👉 አዘጋጅ: የኢዜማ ትይዩ ካቢኔ

👉 ለሁሉም ዜጋ ክፍት የሆነ መድረክ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

27 Sep, 14:15


የመርኃግብር ማሥታወሻ!

"የኮሪደር ልማቱ ከከተማ ልማት እና ከሕግ አንፃር ሲዳሰስ"


👉 አቅራቢዎች:

ዮሐንስ መኮንን (የ #ኢዜማ ም/መሪ)

እዮዔል ሰለሞን (የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት ፅ/ቤት ኃላፊ)

👉 ቀን: ነገ ቅዳሜ መስከረም 18/2017 ዓ.ም.

👉 ሰዓት: ከቀኑ 8:00

👉 ቦታ: ስታዲየም አከባቢ በሚገኘው የኢዜማ ዋና ጽ/ቤት

👉 አዘጋጅ: የኢዜማ ትይዩ ካቢኔ

👉 ለሁሉም ዜጋ ክፍት የሆነ መድረክ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

26 Sep, 15:11


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (#ኢዜማ)

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

25 Sep, 08:33


"የኮሪደር ልማቱ ከከተማ ልማት እና ከሕግ አንፃር ሲዳሰስ"


👉 አቅራቢዎች:

ዮሐንስ መኮንን (የ #ኢዜማ ም/መሪ)

እዮዔል ሰለሞን (የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት ፅ/ቤት ኃላፊ)

👉 ቀን: ቅዳሜ መስከረም 18/2017 ዓ.ም.

👉 ሰዓት: ከቀኑ 8:00

👉 አዘጋጅ: የኢዜማ ትይዩ ካቢኔ

👉 ለሁሉም ዜጋ ክፍት የሆነ መድረክ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

17 Sep, 07:40


የሐዘን መግለጫ

በፖለቲካው ዓለም እና በመምሕርነት ሙያ ለሀገራቸው አዎንታዊ አስተዋፅዖ በማድረግ የሚታወቁት የኢትዮጵያ ሶሻል ዴማክራቲክ ፓርቲ ሊ/መንበር ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ በዛሬው ዕለት መስከረም 07/2017 ዓ.ም. በሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ሰምተናል።

ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ሀገር በጽኑ በምትፈልጋቸው ጊዜ ምሁራን እምብዛም በማይደፍሩት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እስከመጨረሻው ሕቅታ ሀገራቸውን እና ሕዝባቸውን በሚያምኑበት አስተሳሰብ ያገለገሉ ጉምቱ ፖለቲከኛ ነበሩ።

ፓቲርያችን #ኢዜማ በፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ሞት የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለትግል አጋሮቻቸው በቶሎ መጽናናትን ይመኛል።

የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

3,461

subscribers

3,446

photos

212

videos