Ethiojobs.com

@ethio_jobs_in_ethiopia


If there is Vacant position ይለቀቅሎታል።
Because ስራ ለሰሪው እሾህ ለአጣሪው።
https://t.me/joinchat/AAAAAFCfLsxtzyWjLKNrQw

Ethiojobs.com

01 Oct, 19:35


ከታች የተዘረዘሩትን ዓለም አቀፍ ዲጂታል የገንዘብ መገበያያ መንገዶች በነጻ ወደ ስልኮ በማውረድ ተጨማሪ ቦነስን ያግኙ!

Ethiojobs.com

01 Oct, 03:46


👆👆👆 List ሊደረግ ጥቂት ጊዜ ብቻ ነው የቀረው በነጻ ተመዝገቡና ተጫወቱ። 👆👆👆

Ethiojobs.com

01 Oct, 03:45


t.me/catsgang_bot/join?startapp=sBGTUGsl3iE9iDzDSoLyj
Meow, lets see who is OG 😼

Ethiojobs.com

21 Sep, 11:38


ለVGM አዲስ የኾናችኹ 👇

1. ሰላም
2. እዚህ አዲስ ነኝ
3. እንዴት ነው የሚሰራው
4. እንዴት ኢንቨስት ማድረግ እችላለሁ
5. እንዴት መመዝገብ እችላለሁ
6. እንዴት መሳተፍ እችላለሁ
7. ስለዚህ ጉዳይ የበለጠ ንገረኝ

እያላችኹኝ ነው ፣

ማወቅ ምትፈልጉትን Comment ላይ አሁን መልእክት ላኩልኝ!

ሥራውን ለመጀመር 30$ (~3,800 ብር) ተቀማጭ ያስፈልጋል።

ብሩ ክፍያ ሳይሆን ተቀማጭ ነው።

ካስጀመራችሁ በኋላ ማውጣት መብታችሁ ነው።

Link

https://h5.feigf.com/#/pages/auth/register?code=wsIFw0

Ethiojobs.com

17 Sep, 15:39


https://t.me/Dolarcoinsbot?start=r0162424483

Ethiojobs.com

24 Jul, 20:59


የድሮ ሰው "አሟሟቴን አሳምርልኝ!" ሲል ሞት አማረ አላማረ ያው ሞት ነው እል ነበር ሰሞኑን የምናየውና የምንሰማው ነገር ግን "አሟሟቴን አሳምርልኝ!" ማለት ሞት የማይቀር ነገር ቢሆንም ነገር ግን ትልቅ ጸሎት እንደሆነ እንድናስተውል ያስገድደናል!

አቤቱ በድለናልና ይቅር በለን።

የአደጋው ገፈት ቀማሽ የሆኑትን ቤተሰዎች እግዚአብሔር አጽናኝ መልአክ ያድልልን።

የእኛንም አሟሟታችንን ያሳምርልን።

@Gamel_Media

Ethiojobs.com

03 Nov, 07:11


✔️🔔ማሳሰቢያ

ሰሞኑን ብዙ ሰው የቴሌግራም አካውንቱን እየተዘረፈ ነው።

በተለያዩ የቴሌ ግራም ቻናል ሲዘዋወሩ የምናያቸው አጫጭር ሊንኮች የቴሌግራም አካውንታችሁን ለማበላሸት ስለሚዳርጉት ከወዳጅ ዘመዶቻችሁ እንኳን ቢሆን ሊንኮቹ የተላኩት የሚልኩላችሁ እነርሱ አይደሉምና የሚላከውን ሊንክ አትንኩት።

ምንክያቱም ሊንኮቹን ስትነኩ እናንተ የምታስተዳድሯቸውን
አካውንቶቻችሁን
ግሩፖቻችሁን
ቻናላችሁን
በተጨማሪም ከሰዎች ጋር Text ያደረጋችሁትን ሙሉ በሙሉ ሊያጠፉት እና እንደ አዲስ የቴሌግራም አካውንት እንድትከፍቱ ትዕዛዝ ሊሰጣችሁ ይችላል። 

ስለዚህ ከእነዚህን ጠላፊዎች/ሃከሮች ሴራ ለመዳን የሚላክላችሁን ሊንክ አለመንካት አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው።

በተጨማሪም ከጠላፊዎች  አካውንታችሁን ለማዳን በምታስታውሱት PASSWORD ከቴሌግራም ሴቲንግ ውስጥ "TWO STEP VERIFICATION" የሚለውን ON  አድርጋችሁ አካውንታችሁን ጠብቁ።

https//t.me/Gamel_Media

Ethiojobs.com

14 Oct, 17:18


" ሽበት እና ክህነት የማይከበርበት ዘመን ላይ ደርሰን ለዚህ ኀዘን በቅተናል " - ቅዱስነታቸው

ብፁዕ ወቅዱስ #አቡነ_ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በትግራይ ክልል በተካሔደው ጦርነት ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች እየተከናወነ ያለውን የኀዘን ሥነ ሥርዓት በማስመለክት አባታዊ የማጽናኛ መልእክት አስተላለፉ።

ከቅዱስነታቸው መልዕክት የተወሰደ ፦

" ዛሬ በትግራይ ክልል እየተዘከሩ ስላሉ ወገኖች በእጅጉ ማዘናችንን እንገልጣለን ።

ይህ እንዳይመጣ ብዙ ተማጽኖ ስናቀርብ የነበረ ቢሆንም ሽበት እና ክህነት የማይከበርበት ዘመን ላይ ደርሰን ለዚህ ኀዘን በቅተናል።

ዛሬ በትግራይ ክልል የማይለቀስበት ቤት የለም። የተሰዉት ልጆቻችን በሕይወተ ሥጋ ኖረው ቢሆን ብዙ ታሪክ መሥራት ይችሉ የነበረ ቢሆንም እነዚህ የቤተሰብና የቤተ ክርስቲያን እንዲሁም የሀገር ተስፋዎች በእሸት በመቅረታቸው በኀዘን በተሰበረ ልብ ሁነን ለነፍሳቸው ዕረፍተ መንግሥተ ሰማያትን እንዲሰጥልን እንጸልያለን።

በኀዘን የተጎዳችሁ አባቶችና እናቶችም ይህ ቢሆን ኖሮ እያላችሁ ራሳችሁን እንዳትጎዱ፤ የእናንተ መጎሳቆል የሞቱትን ቀና አያደርግምና ልባችሁን እንድታበረቱ እናሳስባለን ምክንያቱም መቃብር መጨረሻችን ያልሆነ የትንሣኤ ሕዝብ ነን፡፡

በምድር ላይ ስንኖር ማንም ለራሱ መከራን አያቅድምና የታቀዱ ቀኖችንም ለማለፍ ሕገ ተፈጥሮ አይፈቅድልንምና በሆነውና በሚሆነው ነገር ሁሉ ' እንደ ፈቃድህ ይሁን ' እያሉ ልብን ማሳረፍ ይገባል በማለት እንመክራለን፡፡ "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@Gamel_Media

Ethiojobs.com

07 Oct, 11:28


እግዚአብሔር ለምን ይቆጣናል?

እግዚአብሔር የሚቆጣን ስለ ራሱ ክብር ብሎ አይደለም፡፡ ብንሰድበውም ብንክደውም እንኳን የሚቆጣን ስለ ሰደብነው ወይም ስለ ካድነው አይደለም፡፡ ምክንያቱም እኛ ስለ ካድነው እግዚአብሔር ምንም አይጎድልበትም፡፡ እኛ ስለ ሰደብነው እግዚአብሔር ምንም አይጎድልበትም፡፡ ይልቁንም እንዲህ በማድረጋችን የምንጎዳው እኛው ነን፡፡ በመኾኑም የሚቀጣን ለእኛ ካለው ጥልቅ ፍቅር የተነሣ ነው፡፡ የሚቆነጥጠን ለእኛ ካለው ወደርየለሽ ጠብቆቱ የተነሣ ነው፡፡ እርሱን እየናቅነውና እየራቅነው ስንሔድ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን ስንሔድ እንዳንጎዳ ሽቶ ነው፡፡

ብርሃንን የሚጠላ ሰው ብርሃኑን ሊጎዳው አይችልም፤ በጨለማ ውስጥ በመቀመጡ ራሱን ይጎዳል እንጂ፤ በራሱ ላይ የጉዳት ዓይነትን ይከምራል እንጂ፡፡ እኛም እግዚአብሔርን ብንጠላው በእግዚአብሔር ባሕርይ ላይ ምንም ነገር አናጎድልም፤ ምረረ ገሃነምን በራሳችን ላይ እንፈርዳለን እንጂ፡፡

እግዚአብሔር በእኛ እይታ እጅግ ክፉ የሚመስሉ ነገሮች በእኛ ላይ ሲያመጣ እኛን ከመበቀል አንጻር አይደለም፤ ይበልጥ ወደ እርሱ እንድንቀርብ እንጂ፡፡ ሐኪሞች አእምሮአቸውን የሳቱ ሰዎች ቢሰድቡዋቸው አይከፋቸውም፡፡ በዚህ አኩርፈውም መድኃኒት ማድረጋቸውን አያቆሙም፡፡ ሕሙማኑ ለዚህ በሽታ የዳረጋቸውን በሽታ ይፈውሱላቸው ዘንድ ይተጋሉ እንጂ፡፡ የሕሙማኑን ችግር እንጂ የእነርሱ መሰደብ አያሳስባቸውም፡፡ እግዚአብሔር አምላካችንም የሚቆነጥጠን ስለ ሠራነው ኃጢአት አይደለም፤ ኃጢአት ሕመም ነውና ከሕመማችን እንድንፈወስ ሽቶ እንጂ፡፡
ቸር አባት ሆይ! ይህ ከአእምሮ የሚያልፍና የዚህ ዓለም ቋንቋ ሊገልፀው የማይችለው ፍቅርህና ጠብቆትህ ዘወትር እናስበው ዘንድ፣ አስበንም በተግባር እንኖረው ዘንድ አእምሮውን ማስተዋሉን ስጠን፡፡ ለዚህ ግሩም ፍቅርህ ያልተገባንና የዕውቀት ግምጃ ቤት ብቻ ኾነን እንዳንቀር ብርታቱን አድለን፡፡
አሜን!
https://t.me/Gamel_Media

Ethiojobs.com

03 Oct, 07:02


📖 📖 📖
አንዳንድ ሰዎች እጅግ የጠለቀ ኀዘንና መቆርቆር ውስጥ ሲገቡ “እግዚአብሔር ትቶኛል! ፤ የእሥራኤል አምላክ ረስቶኛል!” ብለው ሲያማርሩ እሰማቸዋለሁ፡፡

ዛሬ ነቢዩ እንዲህ ከሚሉ ሰዎች ጋር ክርክር አለው፡፡
“በውኑ ሴት ከማኅፀኗ ለተወለደው ልጅ እስከማትራራ ድረስ ሕፃኗን ልትረሳ ትችላለችን?”
በማለት ይጠይቃቸዋል (ኢሳ.49፡14)፡፡

ይህም ማለት ሴቷ ከማኅፀኗ የተወለደው ልጇን ትረሳ ዘንድ እንደማይቻላት ሁሉ እግዚአብሔርም ሰውን ይረሳ ዘንድ ባሕርይው አይደለም እያላቸው ነው፡፡

         ነቢዩ ይህን ምሳሌና ማነጻጸርያ አንሥቶ ክርክር መግጠም የፈለገው እያንዳንዷ እናት ለልጇ ያላትን ጥልቅ ፍቅር ስለሚያውቅ ነው፡፡

ሆኖም ይህን ያህል የምናንቆለጳጵሰው የእናት ፍቅር ከእግዚአብሔር ፍቅር ጋር ሲነጻጸር ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡

ለዚህም ነው “አዎን እርሷ ልጇን ትረሳ ይሆናል ፤ እኔ ግን አልረሳሽም… ይላል እግዚአብሔር” በማለት የሚቀጥለው፡፡

እንግዲህ የአምላካችን ፍቅር እንደምን የበዛ እንደሆነ ታስተውላላችሁን?
      
እንግዲያውስ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት

“አባት ለልጆቹ እንዲያዝን እንዲራራ እንደዚህም ሁሉ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ለሚያመልኩት ይራራለቸዋል።” ብሎ እንደተናገረ “እግዚአብሔር ረስቶኛል! ፤ የእሥራኤል አምላክ ትቶኛል!” የሚል ማንም አይገኝ። (መዝ.102፡13)፡

ጆሮን የፈጠረ እርሱ ይሰማል ፤ ዐይንን የፈጠረ እርሱ ያያል፡፡

እግዚአብሔር በእጁ መዳፍ የቀረጻቸው ልጆቹን አይረሳም፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

https://t.me/Gamel_Media

Ethiojobs.com

25 Sep, 10:49


በአንድ ወቅት አንድ በእድሜ የገፉ አሮጊት ጠርቀም ያለ ገንዘብ በመያዝ ወደ ባንክ በመሄድ በባንክ አካዉንታቸዉ ላይ እንዲያስገባዉ ለባንኩ ማናጀር የያዙትን ገንዘብ ይሰጡታል።
ሰውየውም የያዙትን ገንዘብ በዚህ እድሜያቸዉ ከየት እንዳመጡት ለማወቅ በመፈለግ ሁኔታ ''ይህን ሁሉ ገንዘብ ከየት ልታመጡ ቻላችሁ?'' ብሎ ይጠይቃቸዋል።

አሮጊቷም ''ልጄ ጎበዝ ቁማርተኛ ነኝ ቁማር እጫወታለሁ እና ሁሌም ነዉ የማሸንፈዉ።'' ይሉታል
ማናጀሩም እንዲያብራሩለት ፈለገና ''እንዴት ሁሌ ያሸንፋሉ? ቁማር ላይ ሁሌ መብላት እኮ ይከብዳል።'' ይላቸዋል።
እሳቸዉም ''አይ ልጄ........ እኔ አሸንፋለሁ!

ለምሳሌ አንተ ነገ ቂጥህን ትነቀሳለህ (tato) ብዬ ካንተ ልወራረድ እችላለሁ።'' ይሉታል።

''እናም ማናጀሩ እኔ እኮ ነገ አልነቀስም ስለዚህ እኔ እበላዎታለሁ።'' ሲላቸዉ ''አይ አትበላኝም ነገ ትነቀሳለህ እኔ እበላለሁ ከፈለክ እንውረድ።'' ይሉትና በ30 ሺ ብር ይወራረዳሉ።

እሳቸዉ ቂጥህን ነገ ትነቀሳለህ ሲሉ እሱ ነገ ቂጤን አልነቀስም ሲል ይወራረዱና ለማግስቱ ይቀጣጠራሉ።

በማግስቱ አሮጊቷ ከሁለት ታዛቢዎች ጋር በመሆን ማናጀሩ ወዳለበት ባንክ ቤት ይመጡና ''የተነቀስከውን ለማየት ሱሪህን አዉልቅ!'' ይሉታል።
ሰውየውም አለመነቀሱን እርግጠኛ ስለሆነ ሱሪውን ዝቅ በማረግ ቂጡን ያሳያቸዋል። ሴትየዋም እሺ በቃ ሱሪህን ልበስ አሸንፈኸኛል ይሉታል። እና የተወራረዱትን 30 ሺ ብር ማናጀሩ በአሸናፊነት ይረከባል።

ማናጀሩም ''ትላንት እኮ ሁሌም አሸንፋለሁ ብለውኝ ነበር።'' ታዲያ እኔ እንዴት አሸነፍኩዎት? ሲላቸዉ
አይ ልጄ አላሸነፍከኝም።
እኔ አሁን ከመጡት ሰዎች ጋር ዛሬ የማናጀሩን ዙሪ አስወልቀዋለሁ ብዬ በመቶ ሺህ ብር ተወራርደን ነዉ የመጣሁት ስና ሱሪህን ስላስወለቅኩህ 100,000 ብር ከእነሱ በልቻለሁ ይሉታል።

ወዳጄ ልትሸነፍበት በምትችልበት ሜዳ በጭራሽ አትጫወት። ሁሌም ማሸነፍያ መንገድህን ቀይስ።

ይቀላቀሉን!
@Gamel_Tube
@Gamel_Tube
@Gamel_Tube

Ethiojobs.com

03 Sep, 02:56


የረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት 45ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እሑድ ነሐሴ 28 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በደማቅ ሁኔታ ያከብራል።

እርስዎም የሰንበት ትምህርት ቤታችንን የምስረታ በዓል አብረውን ያከብሩ ዘንድ ተጋብዘዋል።

አድራሻ: - አዲስ አበባ, ካራ ቆሬ, በረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት እና ስብከተ ወንጌል ሁለገብ አዳራሽ።