"honestly speaking ያኔ መተው ነበረብኝ" ብላ ፀዴ ፈገግታ ፈገግ አለች ።
"ይብራራ"- አልኮት
ጥቂት ፈገግታ እና ብዙ ጭፍግግታ በተላበሰ ፊቴ ።
"ጭንቅሌህ ሃሳብ አልባ ነበር። የማይጥምህን ሃሳብ ነፍስህ ተረጋግታ አትሰማም ።አንተ ያልፈለከው ካልሆነ ነፍስህ ትቅበዘበዛለች😢ሁሌ ከአንተ የፈለቀ ሃሳብ ትክክለኛ እና አዳኝ ይመስልሃል። soft dictator ነህ። አምባገነንነትህ እንደእኔ አራዳ ያልሆነ ካልሆነ አይባንነውም።ነፍስህ ሊብራል አይደለችም።
ፍቅርህ እጅ መንሻህ ነበር ።
መከራከርያ፤መደራደርያህ፤ማፅናኛህ ፤መፅናኛህ ፍቅር ነበር ። ፍቅር ከእውነት የሚበልጥ ይመስልካል። ቅናትክ ፈጣጣ ነበር ። ስሜትህን አሁንም አሁንም ታንፀባርቃለህ።
emotional intelligence ይጎልሃል ።
የሆነው ሆኖ አሁን ቢሆን ኖሮ አልተውክም ነበር። ያኔ ሙሉ ሰው ፍለጋ ላይ ነበርኩ።
ሙሉ የሚባል concept አለመኖሩን ለመረዳት ብዙ ነፍስ ጋር ተዋሃድኩ ይሁን እንጂ ጉድለት መልክ እና ይዘቱን እየቀያየረ ሁሉም ጋር እንዳለ ተከሰተልኝ።
ጉድለት ይዞ ምሉዕ ፍለጋ መባተል ያለመብሰል ምልክት ነበር።
አለመብሰል ነበር ያዳከረኝ 🚶♀🚶♀🚶♀
ትላንት ካንተ ጋር ለመሆን ፍላጎት አልነበረኝም ፤ ዛሬ ደሞ እድሉ የለኝም ።
ጭንቅላቷ ሰላብኝ። ከነፍስ ነፍስ መባተሏ እንዳበሰላት ገባኝ ።
ማሳሰብያ፦
የመለያየት ምክንያት ፍፁም ነፍስ ፍለጋ መባተል ነው፦
አለመብሰል በረከታችንን ያሳጣናል።
Source: noahbookdelivery