ብሩህ ተስፋ

@bruh_tesfa


Gefa ወደላይ

ብሩህ ተስፋ

19 Oct, 19:01


የት ትቀበራለህ ወይስ የት ታርፋለህ

ከሞት በኋላ ቀባሪዎች የሚጠይቁት የተለመደ ጥያቄ ነው። ኦርቶዶክስ፣ ሙስሊም፣ ወንጌላውያን፣ ካቶሊክ ወዘተ በየስማቸው በተዘጋጀ መቃብር በሃይማኖቱ ስርዓት ለመሸኘት ይሯሯጣሉ። ነገር ግን አሸኛኘት ምን ቢለያየም ዘላለም ግን አንድ ነው፤ የዘላለም ህይወት ወይንም ሞት።

ታዲያ ለሰዎች ከዘላለም ርዕሰ ጉዳይ በላይ ምን የከበደ ነገር ሊኖር ይችላል? የምድሩ ቆይታማ ከአንቀልባ እስከ ሽምግልና ዕድሜ እንዴት ባለ ፍጥነት እንደሚንደረደር ትላንት የአራስ መጠየቂያ ይዘን የሄድንበትን ህጻን ዛሬ አንቱ ተብሎ ሲጠራ ማየት በራሱ በቂ ማስረጃ ነው።

ስለዚህም የቀበር ሽኝትህ እንዴትም ያለ ቢሆን ዋናው ጥያቄ ነፍስህ የት ታርፋለች የሚለው ነው። ምክንያቱም ሰው ሁሉ 'የዘላለም አምላክ' ተብሎ በተጠራው አንድ አምላክ ፊት ይቆማል እንጂ ስንሞት እንደየእምነታችን የሚቀበሉን የተለያየ እምነት ያላቸው አምላኮች የሉም።
"ሰው አንድ ጊዜ ሊሞት ከዚያም በኋላ በፍርድ ፊት ሊቆም ተወስኖበታል።" ዕብራውያን 9:27

እናም የእርስዎ ተራ መቼ እንደሚሆን ባይታወቅም በዘመንዎ ፍጻሜ ማወቅ የሚፈልጉት ዋና ጉዳይ የትና እንዴት ባለ ስርዓት እንደሚቀበሩ ሳይሆን ነፍስዎ የትኛው ዘላለም እንደምታርፍ ነው።
"እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።" ዮሐንስ ወን 17:3

ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!
Share @Bruh_Tesfa

ብሩህ ተስፋ

07 Oct, 05:53


ያለ አስተማሪ!

"መጽሐፍ ቅዱስ አነባለሁ ግን ብዙም አይገባኝም። ወይንም ደግሞ ማንበብ እጀምርና ስለማልረዳው ጨምሬ ለማንበብ ፍላጎት አጣለሁ" ብለው ያውቃሉ?

ይህ ከሆነ ልክ እንደርሶ ተመሳሳይ ስሜት ስለነበረውና በመጽሐፍ ቅዱስ ሐዋ. ሥራ 8:26 ላይ ታሪኩ ስለተዘገበልን አንድ ኢትዮጵያዊ ልንገርዎ።

ይህ ኢትዮጵያዊ የተማረ፣ በገንዘብ ሚኒስቴር ደረጃ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ደግሞም ሃይማኖተኛ የነበረ ሰው እንደሆነ ተጽፎለታል (ሙሉ ታሪኩን ያንብቡ)። ኢየሩሳሌም ሊሰግድ ሄዶ ሲመለስ በሠረገላ ውስጥ ሆኖ ነብዩ ኢሳያስ ስለ ኢየሱስ የፃፈውን የትንቢት መጽሐፍ እያነበበ ወደ አገሩ እየተመለሰ ሳለ ፊሊጶስ የተባለ የጌታ ተከታይ ወደ ሰረገላው ቀርቦ የምታነበውን ታስተውላለህ ወይ ብሎ ሲጠይቀው "የሚያስረዳኝ ሳይኖር እንዴት" የሚል ቅንና እውነተኛ መልስ ሰጠ። ይገርማል! ያነባል ነገር ግን አይረዳውም።

ይህ የሆነበት ምክንያት የእግዚአብሔርን ቃል ለመረዳት የቃሉ ባለቤት የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስ እርዳታ የግድ ስለሆነ ነው። በዮሐንስ ወንጌል 14:26 "...መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።" ተብለናልና ያለ አስተማሪው መንፈስ ቃሉን ብናነብ፣ ብንማርና ብንመራመር ከቶ አይገባንም ወይንም ህይወት አይሆንልንም።

ስለዚህም ያ ኢትዮጵያዊ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ወደ እርሱ የመጣውን ፊሊጶስን ወደ ሰረገላው ወጥቶ እንዲያስረዳው እንደጋበዘው ሁሉ እኛም ቃሉን ስናነብ እንዲያስተምረን መንፈስ ቅዱስን ወደ ህይወታችን እየጋበዝን ቢሆን እውነቱ ይበራልናል፣ ለእኛም አዲስና ልዩ መገለጥ ይሆንልናል።

መንፈስ ቅዱስን መጋበዝ እንዴት ይቻላል የሚል ጥያቄ ቢኖርዎ ይጻፉልን።

ብሩህ ተስፋ

29 Sep, 14:43


https://youtu.be/DEH1SbCFKLo

ብሩህ ተስፋ

19 Sep, 03:53


የእግዜር ቤት

ሰዎች ያለ መጠለያ መኖር አይሆንላቸውም። እናም የሚሰሩትን ቤት ቁመትና ስፋት በሰው ልጆች ልክና ሚዛን ሰፍረው እነርሱን የሚያክል ቤት ይሠራሉ። የዱር እንስሳትና አእዋፋትም እንዲሁ በእነርሱ ቁመት ልክ የሆነውን ቀልሰው ወይንም አፈላልገው በዚያ ይጠለላሉ።

ከዚህ በእጅጉ በተለየ በአንድ ወቅት ሰዎች ለሰማይና ለምድር ዳርቻ ፈጣሪ እግዚአብሔር ቤት እንስራ ብለው ሲያስቡ እግዚአብሔር ቀድሞ አንድ ጥያቄ ጠየቃቸው።
"ለኔ ምን ዓይነት ቤት ትሰራላችሁ?" አላቸው። ምክንያቱንም ሰው በሚገባው ቋንቋ ልኩን ሲያስረዳ፣ እኔ "ሰማይ ዙፋኔ ምድር ደግሞ የእግሬ መረገጫ ናት" አላቸው። ሐዋ 7:48 በእርግጥም ለዚህ ከምድር እስከ ሰማይ ለተዘረጋ እጅግ ታላቅ አምላክ፣ ሰው ምን ዓይነት ቤት ሊሰራለት ይችላል?

ሆኖም እግዚአብሔር ሰውን በመውደዱ በሰዎች መካከል ማደርን ደግሞ ፈልጓል። ስለዚህም እርሱ የሚፈልገውን ዓይነት የማያረጅ እና የማይፈርስ ህያው ቤት እንድንሰራለት የቤቱን ዓይነትና ፕላን በዝርዝር ነግሮናል። ከብዙ በጥቂቱ፡-

1. 1ኛ ዮሐንስ 4:15 "ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።"

2. ዮሐንስ ወንጌል 14:23
"ኢየሱስም መለሰ፡ አለውም፦ “የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል፡ ወደ እርሱም እንመጣለን፡ በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።"

እግዚአብሔር እንዴት በሰው ውስጥ መኖር ይችላል? እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሆኖ ይመራናል፣ ይመክረናል፣ ይገስጸናል፣ ያስተምረናል...

ስለዚህም ትልቁ እግዚአብሔር በውስጥህ ሊኖር ወዷልና እባክህ መኖሪያው ቤት ሁንለት።

ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!

ብሩህ ተስፋ

11 Sep, 02:13


እንቁጣጣሽ

ብሩህ ተስፋ

03 Sep, 06:15


አይምጣብህ!

ከዓለም ህዝብ 72% ምዕመናንን የያዙት 3ቱም ዋና ዋና ሃይማኖቶች (ክርስትና፣ እስልምናና ሂንዱይዝም) ወደፊት ይመጣል ብለው የሚጠብቁት መሲህ አላቸው። የመሲሁ አመጣጥና ከመጣም በኋላ ያደርጋል በሚሉት ላይ ልዩነት ቢኖራቸውም 3ቱም ሊመጣ ያለው መሲህ ግን ኢየሱስ መሆኑ ላይ ይስማማሉ።

ኢየሱስ ዳግም በሚመጣበት ዓላማ ዙሪያ ሃይማኖቶቹ የሰፋ ልዩነት ስላላቸው የጠራውን እውነት ለማወቅ ኢየሱስ ራሱ ስለ ዳግም መምጣቱ ምን አለ የሚለውን ከራሱ መስማት የግድ ይሆናል።

በመጽ/ቅ ስለ ኢየሱስ ዳግም ምጽአት ከተፃፉት 67 ጥቅሶች ውስጥ ኢየሱስ ራሱ እኔ እያለ የተናገረው ይህ ጥቅስ ይገኝበታል:-

"በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ ይህ ባይሆንማ ኖሮ እነግራችሁ ነበር፤ የምሄደውም ስፍራ ላዘጋጅላችሁ ነው። ሄጄም ስፍራ ካዘጋጀሁላችሁ በኋላ፣ እኔ ባለሁበት እናንተም ከእኔ ጋር እንድትሆኑ ልወስዳችሁ ዳግመኛ እመጣለሁ።" ዮሐንስ 14:2-3

ዋናው ቁምነገር ጌታ የሚመጣላቸው እንዳሉ ሁሉ ሳይዘጋጁ እንደ ሌባ ድንገት የሚመጣባቸውም አሉና ኢየሱስ መጥቶ ከሚወስዳቸው እንጂ ከሚቀሩት አለመሆንዎን እርግጠኛ ይሁኑ።

ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን!

Share @Bruh_Tesfa

ብሩህ ተስፋ

26 Aug, 05:12


ማወቅ እንጂ ማየት ማመን አይደለም!

በበረሃ ላይ ውሃ የሚመስል ነጸብራቅ (mirage) ስናይ ውሃ ነው ብለን በደስታ የማንፈነጥዘው አሸዋ መሆኑን ስለምናውቅ ነው። ስለዚህም የዕውቀታችን ደረጃ የዕይታችንን ልክ ይወስናል ማለት ነው።

በዕለተ እሁድ በጠዋቱ ወደ መቃብር የሄዱት 3ቱ ሰዎች ስለ ኢየሱስ ሞትና ትንሳዔ በነበራቸው ዕውቀት ማነስ ምክንያት ያዩትን በተሳሳተ መንገድ ነበር የተረዱት።

መግደላዊት ማርያም የመቃብሩ ግጣም ድንጋይ ተንከባሎ ስታይ ሰዎች በሌሊት የጌታን አካል ከመቃብር አውጥተው ለመውሰዳቸው ማሰረጃ ሆኖ ታያት። አብሮአት የነበረው ዮሐንስ ወደ መቃብሩ ሳይገባ ዝቅ ብሎ ሲያይ ከፈን በማየቱ የማርያምን ሀሳብ በግማሽ ተቀበለ። በኋላም ጴጥሮስ ወደ መቃብሩ ገብቶ ከፈኑና የራሱ ጥምጣም ብቻ እንዳለ ሲነግረው እሱም ገብቶ አይቶ መሰረቁን አመነ።

የ3ቱም ዕይታ የተሳሳተበትን ምክንያት መጽ/ቅ ሲነግረን "ከሙታን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው የሚለውን የመጽሐፉን ቃል ገና አላወቁም ነበር" ይላል። ቃሉን አለማወቃቸው አሳሳታቸው። ዮሐንስ ወንጌል ምዕ20

ስለዚህም አንተም ስለ ኢየሱስ የሰማኸውን አምነህ ለመቀበል መነሻ ያደረግከው በቃሉ ዕውቀት ላይ ሳይሆን አንተ ከቆምክበት ጠርዝ (ሃይማኖትህ፣ ከልጅነት እስከ ዕውቀት የሰማኸው ወዘተ) ብቻ ከሆነ ሙሉውን እውነት ማየት አትችልም።

እግዚአብሔርን ራሱን ለሰዎች ይገልጣል፣ ቃሉን በግልህ አጥና፣ ፈልገው ይገኝልሃል። "እናንተ ትሹኛላችሁ፥ በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ" ኤርምያስ 13:29

ጥያቄ ቢኖርዎ ይላኩልን።

Share @Bruh_Tesfa

ብሩህ ተስፋ

16 Aug, 19:11


ስስ ብልት

ችግር የማይቋቋሙና በቀላሉ ሊጎዱ የሚችሉ የአካላችን ክፍሎች በውስጣችን በብዙ አጀብ ተከልለዋል። ለምሳሌ ልብ ከፊት እና ከኋላ በጎድን አጥንቶች ታጥራ፣ በደረትና ጀርባ ጡንቻዎች ተከልላ፣ ያም ሳያንሳት ከላስላሳው ሳምባ ስር ተሸጉጣ ወሳኝ ስራዋን ያለማቋረጥ ትሰራለች።

ግና ምን ተሰውራ ያለች ቢሆንም ጆሮ በሚሰማው በሚሆንና በማይሆነው ወሬ ደግሞ በቀላሉ የምትናወጥ ነች። በቀላሉ ትናወጣለች እንጂ በቀላሉ አትረጋጋም። ዛሬ ያስጨንቃታል፣ ስለ ነገ ትታወካለች፣ ምኞትና ህልሟ ሲሳካም አታርፍም፣ አስተማማኝና የፀና ተስፋ እስክታገኝ አይዞሽ ብትባልም አትሰማም።

"ልባችሁ አይታወክ" ኢየሱስ ነገአቸው ላስጨነቃቸው ደቀመዛሙርት የነገራቸው ቃል ነበር። ይህ ተራ አይዟችሁ ማጽናኛ ቃል ሳይሆን ልብን ከጭንቀት የሚታደቁ 2 መልህቅ እውነቶችን ቀጥሎ ነገራቸው።

1. በእግዚአብሔር እመኑ፣ በእኔም ደግሞ እመኑ።

2. በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ... ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁ። ዮሐንስ ወንጌል 4: 1-3

ልብን ለዘለቄታ የሚያረጋጋው ዓለም የምትሰጠው ገንዘብና ክብር አይደለም፤ ምክንያቱም ገንዘብና ክብር የራሳቸውን ሌሎች ጭንቀቶችን ይዘው ይመጣሉና።

ለነገ ዋስትና ከሌለ በእርግጥም ነገ ያስጨንቃል። ስለዚህ እርስዎ ዘላቂ የልብ ሰላምና እረፍት ይሻሉ?

ከሆነ የሚያስፈልግዎ:-
1ኛው እምነት፤ ማለትም እግዚአብሔር በላከው በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ ማመን። ሰው ከሰራው ጌታ ጋር ሳይታረቅ ሰላም ሊኖረው አይችልምና።

2ኛው ዕውቀት፤ በልጁ ያመኑ የዘላለም ህይወት እንዳላቸውና የተዘጋጀላቸው መኖሪያ እንዳለ ማወቅ። መንገድ ሲሄዱ ውለው ቀኑ ሲመሽ የትና ማን ቤት እንደሚያርፉ ማወቅ ሰላምን ይሰጣልና የህይወትዎ ቀን ሲመሽ የት ቤት እንደሚያርፉ ያውቃሉ?

ጥያቄ ወይንም አስተያየት ካለዎ ይላኩልን

ብሩህ ተስፋ

04 Aug, 15:23


እግዚአብሄር መታወቂያ አይጠይቅም።

በኪሳችን ያለው መታወቂያ ፎቶአችንን፣ አድራሻችንንና የትውልድ ቀን መረጃዎችን ይይዛል እንጂ በልባችን የተሰወረውን ማንነታችንን አይገልጽም።

እግዚአብሔር ደግሞ ሰውን የሚያውቀው ወደ ምድር ለላከልን ልጁ በሰጠነው ምላሽ ልክ ነው። በመጽ/ቅ ማርያም ተብለው የሚጠሩ ብዙ ሴቶች ቢኖሩም የአልአዛርን እህት ማርያምን ሲገልጻት "ጌታን ሽቶ የቀባችው፣ እግሩንም በጠጉሩዋ ያበሰችው ማርያም" በማለት ለኢየሱስ በሰጠችው የፍቅር ምላሽ ልክ ያውቃታል።

እንዲሁም በዘመኑ ከነበሩት ብዙ ይሁዳዎች ውስጥ "አሳልፎ የሰጠው አስቆሮቱ ይሁዳ" በማለት ይሁዳ ለኢየሱስ በሰጠው የክህደት ምላሽ ይታወቃል።

ወንድሜ/እህቴ እግዚአብሔር በምን ያውቅህ/ሽ ይሆን? በመስቀል ሞቶ እንዲያድነው የላኩለትን ልጄን መድሃኒት አድርጎ የተቀበለና እርሱንም በዘመኑ ሁሉ ያገለገለ ይላል ወይንስ የልጄን ደም የረገጠ?

ምክንያቱም "ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ የአባቴ ፈቃድ ይህ ነው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።” እንደሚል የእግዚአብሔር አብ ፈቃድ ልጁን አምነን በመቀበል ከዘላለሞት ሞት መዳናችን ነው። ዮሐንስ 6:40

Share @Bruh_Tesfa

ብሩህ ተስፋ

04 Aug, 15:00


ቻነሉን share እያደረጋችሁ ያላችሁትን እያመሰገንን እስከሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት share አድርጋችሁ subscribe ያደረጉትን ስም ዝርዝር በውስጥ መስመር ላኩልን። ማበረታቻ እንልካለን።

ብሩህ ተስፋ

01 Aug, 04:49


እነዚህን ጠቃሚ ሰባት ሀሳቦች ስለ እግዚአብሔር ቃል በጥያቄ መልክ አካፈልናችሁ። እናንተ ደግሞ ሌሎች እንዲያውቁ ሊንኩን ለምታውቋቸው በመላክ አካፍሉ። ቻነሉ ብዙ የሚነበብ ስላለው ሊንኩን ቢያንስ ለ10 ሰው ላጋራና ስማቸውን በsubscription ዝርዝር ማየት ከቻልን የማበረታቻ ሽልማት እንልካለን።
@Bruh_Tesfa

ብሩህ ተስፋ

21 Jul, 16:19


የዳቦ ሃሳብ

የሰይጣን ፈተና ቁጥር 1 ምን እንደሆነ ያውቃሉ? ኢየሱስ 40 ቀናት ከጾመ በኋላ እንደተራበ አውቆ ሰይጣን ያቀረበለት የመጀመሪያው ፈተና የዳቦ ሃሳብ ነው። ዳቦ ሳይሆን የዳቦ ሃሳብ። ምክንያቱም መጀመሪያ በተራበ ሆድህ የዳቦ ሃሳብ ያስገባብህና አንተም በምናብህ ጥጋብን ስትጎመዥ፣ ዳቦውንም ሳታገኝ ሃሳብህንና ፈቃድህን ከቁጥጥሩ ስር ማስገባት ቀላል እንደሆነ ስለሚያውቅ ነው።

በዚህ የዳቦ ሃሳብ አልሸነፍ ሲለው የሰይጣን ፈተና በዛ ብቻ አልቆመም። ስገድልኝና ክቡር፣ ሀብታም፣ ታዋቂና ዝነኛ መሆንን እሰጥሃለሁ አለው። ይህ ፈተና የክብር፣ የገንዘብና የዝና ሃሳብ ስላለበት ሰዎች በቀላሉ የሚወድቁበት ፈተና ነው። አሁንም ግብዣው የሃሳብ ነው።

በመጨረሻም ለኢየሱስ የቀረበለት "እስኪ እራስህን ቁልቁል ወርውር" የሚል የነፍስ ግድያ ጥያቄ ነበር። ሉቃስ 4:1-13

የመጨረሻው ጥያቄ የሰይጣንን የመጨረሻ ፍላጎቱን በግልጽ ያሳየናል፣ ነፍሳችንን ማጥፋት።

ሰይጣን በጥጋብ እና በገንዘብ ሃሳብ ምኞት እያስዋኘ ያማልልሃል እንጂ ነፍስህን ካልሰጠኸው ምንም እንደማይሰጥህ እወቅ። ነፍስን የሚያህል ክቡር ነገር በገንዘብ መለወጥ ደግሞ የመጨረሻ አላዋቂነት ነው።

በተቃራኒው "ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል" እንደሚል እግዚአብሔር ልጁን ሰጥቶ ፍቅሩን የገለጠልን ገና ያኔ ኃጢአተኞች ሳለን ነው እንጅ ይህንንና ያንን አድርግና ጻድቅ ሆነህ ስትገኝ ህይወትን እሰጥሃለሁ አላለም። ሮሜ 5:8

የእግዚአብሔር ዓላማ ህይወት ስለሆነ የዘላለም ህይወትን በኢየሱስ ተሰጥቶናል። እርሱን በማመን የሚገኘውን ህይወት መቀበልና አለመቀበል ግን የእኛ ፈንታ ነው።

ብሩህ ተስፋ

15 Jul, 05:43


ባይታይም ይታያል!

ምን አለበት 'አንድ ጊዜ እግዚአብሔርን ባየውና እውነተኛ አምላክ እንደሆነ ባውቅ' ብለው አስበው ያውቃሉ?

በአንድ ወቅት ከ12ቱ አንዱ "አብን አሳየንና ይበቃናል" ብሎ ኢየሱስን ጠይቆ "እኔን ያየ አብን አይቷል።" የሚል መልስ ተሰጥቶታልና ይህን ጥያቄ ለመጠየቅ አንተ የመጀመሪያው አይደለህም። ዮሐንስ 14:9

በተፈጥሮው የሰው ልጅ ለማመን ማየት ይፈልጋል፣ ችግሩ ግን ያላየነው ካየነው፣ የምናውቀው ከማናውቀው እጅግ የሚበልጥ በመሆኑ እምነታችንን በዓይናችን ብቃት ላይ መመሥረት አያዋጣንም። ያም ብቻ ሳይሆን መጽ/ቅ "የሚታየው የጊዜው፣ የማይታየው የዘላለም ነው" ስለሚል አይተን የተቀበልነው ዕውቀት ከሞት ወዲያ ማዶ ወዳለው ዘላለም የሚሻገር አይደለም። 2ኛ ቆሮንቶስ 4:18

ሰው በተፈጥሮ በሚያየው ነገር ልክ የተወሰነ እንደሆነ የሚያውቅ አምላክ የማይታየው እግዚአብሔር ሰው ሊያየው በሚችል መልክ ሥጋ ለብሶ መጣ፣ እርሱም ኢየሱስ ነው። ኢየሱስ "የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው (image of the invisible God)" ይለናል ቆላስይስ 1:15።

ያላመንኩት ስላላየሁት ነው እንዳትል የማይታየው አምላክ የሚታይና የሚዳሰስ ሰው ሆኖ መጥቷልና ላለማመን ምንም ሰበብ የለም። አምነህ እንድትድን እግዚአብሄር ይርዳህ።

10,145

subscribers

57

photos

1

videos