በወሎና በጎንደር ቀጠና በተካሄዱ ውጊያዎች ፋኖ በአገዛዙ ጦር ላይ ከባድ ኪሳራ ማድረሱ ተገለጸ
በዋርካዉ ምሬ ወዳጆ የሚመራዉ የአማራ ፋኖ በወሎ በትላንትናው እለት ከጧቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ምሽት 4:00 ሰዓት በተደረገ አውደ ውጊያ በባለ ሽርጡ ክ/ጦር ዋና አዛዥ እንድሪስ ጉደሌ እየተመራ
ጊራና ከተማ ፣ፋፍም፣ ጊዶ በር፣ ጉቤ ፣ ውረኔ በተባሉ አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ ጀብዱ ፈፅሟል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ ገልጿል።
በዚህ በጊራና በነበረው ውጊያ በሻለቃ ደምሌ እና በፋኖ ሰለሞን ሞላ እየተመራ የልጅ እያሱ ክ/ር ጦርም ተሳትፎ ማድረጉ ታውቋል፡፡
የብልጽግናን ሃይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ከተማውን ተቆጣጥረን በዚህ ሰዓት አሰሳ በማድረግ ላይ እንገኛለን ያለው ድርጅቱ በተጨማሪም ከሌሊት 6:00 ሰዓት ጀምሮ የአገዛዙ ቁልፍ ቦታዎች መሀል አምባ፣ሊብሶና ውርጌሳንም በመቆጣጠር እያስጨነቅነው እንገኛለን ብሏል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአገዛዙ ሠራዊት ተጨማሪ ኃይል ከባሕር ዳር ወደ ደብረ ታቦር ከተማ ለማስገባት በምድር ዙ- 23፣ BM-107፣ ዲሽቃና ሞርታርን እንዲሁም በሠማይ በሄሊኮፍተር የታገዘ ጉዞን ሢያደርግ መዋሉን የአማራ ፋኖ በጎንደር አሳውቋል።
በተመሣሣይ ከባሕር ዳር የተነሳውን ጦር ለመቀበል ከደብረ ታቦር ወደ አለም በር የአገዛዙ ጦር በከባድ መሣሪያ ታግዞ ዘምቷል።
ሆኖም ድልን እሥትንፋሳቸው ያደረጉ የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር እና የጉና ክፍለ ጦር አካል የሆነችው ጣይቱ ሻለቃ በጥምረት የአገዛዙን ጦር የተለያዬ ቦታ ላይ ደፈጣ ጥለውበታል።
በደፈጣ የታጨደው የአገዛዙ ጦር ወደ ሁለቱም አቅጣጫ እግሬ አውጭኝ ካለ በኋላ ራሱን አደራጅቶ ተመልሷል። ድንጋጤን መለያው ያደረገው የአቢይ ጦር በምድር ውጊያ እንደተሸነፈ ሢያረጋግጥ በሠማይ በሄሊኮፍተር ታግዞ ከእንደገና ውጊያን አድርጓል።
ነገር ግን አሸናፊነት ከአባቶቻቸው የወረሱት፣ ሥነ ልቦናቸው በዕውነት የጸናው፣ ትግላቸው ሕልውናን ማሥቀጠል እንደሆነ ያመኑት የአሥቻለው ደሤ ቀኝ እጆች፣ የውባንተ አባተ ልጆችና የናሁሰናይ ወንድሞች በአገዛዙ የጦር ጋጋታ አልተረበሹም።
የአማራ ፋኖ በአለም በር ላይ የልብ ትጥቅን በደምብ ታጥቆ በውሥን ጦር አገዛዙን ሢለበልብ ውሏል። አለም በርና ዙሪያ ገባው ላይ በነበረው ውጊያ የአገዛዙ አመራሮችም ጭምር ሢደመሰሱ ደብረ ታቦር ሆሥፒታል በዚህ ሠዓት በአገዛዙ ቁሥለኞች ተሞልቷል። የአገዛዙ ከፍተኛ የጦር መሪም እንደቆሰለና ታቦር ሆሥፒታል እንደገባ አረጋግጠናል ብሏል በአርበኛ ባዬ ቀናው የሚመራው የአማራ ፋኖ በጎንደር
ድል ለአማራ ፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!