Latest Posts from ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" (@wahidcom) on Telegram

ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" Telegram Posts

ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
42,420 Subscribers
68 Photos
60 Videos
Last Updated 01.03.2025 13:22

The latest content shared by ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" on Telegram


አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ያ ጀመዓህ ይህንን ቻናል የዲኑል ኢሥላም የብርሃን አድማስ ለማስፋት እና ለኩፋሮች ተደራሽነት እንዲሆን ሊንኩን በየቻናሉ፣ በየግሩፑ፣ በየኮሜንት መስጫ እንድታጋሩልን ከታላቅ ትህትና ጋር እንደጠቃለን። ኢንሻላህ
https://t.me/Wahidcom

የቫላንታይን ቀን

አሏህ ሁሉን ዐዋቂ ነው!

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

65፥11 "አሏህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው"፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ

አምላካችን አሏህ ሁሉንም "ነገር" ዐዋቂ ነው፥ "ሸይእ" شَيْء ማለት "ነገር" ማለት ሲሆን ይህም ነገር አጠቃላይ ፍጥረትን ሁሉ ያጠቃልላል፦
65፥11 "አሏህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው"፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ

ይህ ሆኖ ሳለ ሚሽነሪዎች "ዐሊመሏህ" عَلِمَ اللَّه የሚለው ቃል ወስደው "አሏህ ሁሉን ዐዋቂ ነውን? ብለው ይጠይቃሉ፦
2፥235 አሏህ እናንተ በእርግጥ የምታስታውሷቸው መኾናችሁን ዐወቀ፡፡ عَلِمَ اللَّهُ أَنَّكُمْ سَتَذْكُرُونَهُنَّ
2፥187 አሏህ እናንተ ነፍሶቻችሁን የምትበድሉ መኾናችሁን ዐወቀ፡፡ عَلِمَ اللَّهُ أَنَّكُمْ كُنتُمْ تَخْتَانُونَ أَنفُسَكُمْ

"አል ማዲ" الْمَاضِي ማለት "አላፊ"Past" ማለት ሲሆን "ዐሊመ" عَلِمَ አላፊ ግሥ ነው፥ አሏህ ቀድሞ ማወቁ ችግሩ ምንድን ነው? "አሏህ ዐወቀ" ማለት ጥንቱንም ማወቁን ያሳያል እንጂ በዐማርኛ "ዐወቀ" ማለት ያላወቀውን ዐወቀ ማለት አይደለም። ተመሳሳይ የሰዋስው አወቃቀር ከባይብል በንጽጽር እንመልከት! "የደ ኤሎሂም" יֵּ֖דַע אֱלֹהִֽים ማለት በአላፊ ግሥ "አምላክ አወቀ" ማለት ነው፦
ዘጸአት 2፥25 አምላክ የእስራኤልን ልጆች አየ፥ አምላክ በእነርሱ ያለውን ነገር "አወቀ"። וירא אלהים את בני ישראל וידע אלהים׃

"የደ" יֵּ֖דַע ማለት "አወቀ" ማለት ሲሆን አላፊ ግሥ ነው፥ "አምላክ ቀድሞ ማወቁ ችግሩ ምንድን ነው? "አምላክ ዐወቀ" ማለት ጥንቱንም ማወቁን ያሳያል እንጂ በዐማርኛ "ዐወቀ" ማለት ያላወቀውን ዐወቀ ማለት አይደለም" ካላችሁ ይበል የሚያስብል እና ይሁን የሚያሰኝ ነው፥ እንግዲያውስ የቁርኣኑን አናቅጽ በዚህ መልክ እና ልክ ተረዱት! በሰፈሩት ቁና መሰፈር ይሉካል እንደዚህ ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

ያ ጀመዓህ አሠላሙ ዐለይኩም

የኡሥታዛችን አቡ ሀይደር "ቀዷ ወል ቀደር" የሚለው መጽሐፉ ሰውዲ 550 ፍሬ አለ። የምትፈልጉ ልጀች እኅት ፎዚያን 009660507751537 አግኛት!
ሌሎቻችን ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን።

የተሰደሩ መጣጥፋት
ክፍል አንድ
ክፍል ሁለት
ክፍል ሦስት
ክፍል አራት
ክፍል አምስት
ክፍል ስድስት
ክፍል ሰባት

ለሌሎች ሠበቡል ሂዳያህ ይሆን ዘንድ ኢንሻላህ ሼር አርጉት!

ጌታ ነኝ?

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

6፥164 በላቸው «እርሱ አሏህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአሏህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጂ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

"ረብ" رَبّ ማለት "ጌታ" "አስተናባሪ" "ባለቤት" ማለት ሲሆን ሁሉን የሚገዛ ጌታ አምላክ አንድ ጌታ አምላክ ነው፦
ማርቆስ 12፥29 እስራኤል ሆይ ስማ! ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው። اسْمَعْ يَا إِسْرَائِيلُ. الرَّبُّ إِلَهُنَا رَبٌّ وَاحِدٌ.

በዐረቢኛው ባይብል እዚህ አንቀጽ ላይ "ጌታ" ለሚለው የገባው ቃል "ረብ" رَبّ እንደሆነ ልብ አድርግ! ነገር ግን ኢየሱስ ለሐዋርያቱ "እንዲሁ ነኝና" ብሎ ለመለሰበት የገባው ቃል "ረብ" رَبّ ሳይሆን "ሠይድ" سَيِّد ነው፦
ዮሐንስ 13፥13 እናንተ መምህር እና ጌታ ትሉኛላችሁ፥ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። أَنْتُمْ تَدْعُونَنِي مُعَلِّماً وَسَيِّداً وَحَسَناً تَقُولُونَ لأَنِّي أَنَا كَذَلِكَ

እዚህ አንቀጽ ላይ ሐዋርያት "ጌታ" ላሉት የገባው ቃል "ሠይድ" سَيِّد እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል። "ሠይድ" سَيِّد በስም መደብ "አለቃ" "አውራ" "ራስ" "የበላይ" "ጌታ" ማለት ነው፥ "ሠይድ" سَيِّد በቅጽል መደብ "ለዘብተኛ" "ደግ" "ንዑድ" "ስቡት" "ሕሩይ" "ጥበበኛ" ማለት ነው። ስለዚህ ኢየሱስ "እንዲሁ ነኝና" ያለው ሐዋርያት "ሠይድ" سَيِّد ስላሉት እንጂ "ረብ" رَبّ ስላሉት አይደለም፥ በተመሳሳይ ሣራ ለአብርሃም፦ "ሠይዲ" سَيِّدِي ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት
1ኛ ጴጥሮስ 3፥6 እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ “ጌታዬ” ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት። وَهَكَذَا كَانَتْ سَارَةُ تُطِيعُ إبْرَاهِيمَ وَتُنَادِيهِ «سَيِّدِي.»

ስለዚህ "ጌታ" ማለት እልቅና እና ክብርን፣ ሥልጣን እና ሹመትን፣ አለቅነትን እና መሪነትን ለማመልከት ይመጣል። "እኔ ጌታ ነኝ" ለማለትማ ተወዳጁ ነቢያችንም"ﷺ"፦ "እኔ ጌታ ነኝ" ብለዋል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 209
አቢ ሠዒድ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እኔ የአደም ልጆች ጌታ ነኝ"። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ أَنَا سَيِّدُ وَلَدِ آدَمَ
ሢልሢለቱ አስ ሶሒሕ መጽሐፍ 4, ሐዲስ 100
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "እኔ በትንሣኤ ቀን የሰዎች ጌታ ነኝ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ أنا سَيِّدُ الناس يوم القيامة

ቅሉ እና ጥቅሉ እነዚህ ሐዲሳት ላይ "ጌታ" ለሚለው የገባው ቃል "ሠይድ" سَيِّد እንጂ "ረብ" رَبّ አይደለም፥ ነቢዩላህ የሕያ "ሠይድ" سَيِّد ተብሎአል፦
3፥39 እርሱም በጸሎት ማድረሻው ክፍል ቆሞ ሲጸልይ መላእክት፦ «አሏህ በየሕያ ከአሏህ በኾነ ቃል የሚያረጋግጥ ጌታ፣ ድንግል እና ከደጋጎቹ ነቢይም ሲኾን ያበስርሃል» በማለት ጠሩት። فَنَادَتْهُ ٱلْمَلَٰٓئِكَةُ وَهُوَ قَآئِمٌۭ يُصَلِّى فِى ٱلْمِحْرَابِ أَنَّ ٱللَّهَ يُبَشِّرُكَ بِيَحْيَىٰ مُصَدِّقًۢا بِكَلِمَةٍۢ مِّنَ ٱللَّهِ وَسَيِّدًۭا وَحَصُورًۭا وَنَبِيًّۭا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ

የትንሣኤ ቀን ሰዎች አሏህን "ጌታችን" ሲሉ እና መሪዎቻቸው "ጌቶቻችን" ሲሉ ይለያያል፦
33፥67 ይላሉም "ጌታችን" ሆይ! እኛ "ጌቶቻችንን" እና ታላላቆቻችንን ታዘዝን፡፡ መንገዱንም አሳሳቱን። وَقَالُوا۟ رَبَّنَآ إِنَّآ أَطَعْنَا سَادَتَنَا وَكُبَرَآءَنَا فَأَضَلُّونَا ٱلسَّبِيلَا۠

ልብ አድርጉ! ሰዎቹ የትንሳኤ ቀን ሰዎችን “ሣደተና” سَادَتَنَا ሲሉ አሏህን ግን “ረበና” رَبَّنَا ብለው ተጠቅመዋል። በኢሥላም ሸሪዓህ "ሠይዲ" سَيِّدِي አክብሮትን ለማሳየት ለሰዎች ብንጠቀምበትም "ረቢ" رَبِّي ማለት ግን አይቻልም፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 40, ሐዲስ 14
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ መካከል ማንም ባሪያዬ አይበል፥ ሁላችሁም የአሏህ ባሮች ናችሁ። ነገር ግን ሎሌዬ ይበል! "ረቢ" አይበል አይበል፥ ነገር ግን "ሠይዲ" ይበል። عَنْ أَبِي، هُرَيْرَةَ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ لاَ يَقُولَنَّ أَحَدُكُمْ عَبْدِي ‏.‏ فَكُلُّكُمْ عَبِيدُ اللَّهِ وَلَكِنْ لِيَقُلْ فَتَاىَ ‏.‏ وَلاَ يَقُلِ الْعَبْدُ رَبِّي ‏.‏ وَلَكِنْ لِيَقُلْ سَيِّدِي ‏"‏ ‏.‏

አምላካችን አሏህ የሁሉ ነገር ረብ ሲሆን ከአሏህ በቀር ሌላን ረብ እፈልጋለሁን? እረ በፍጹም፦
6፥164 በላቸው «እርሱ አሏህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአሏህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጂ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

ሥሉሳውያን ክርስቲያኖች ሆይ! ኢየሱስ እራሱ "ጌታ ፈጠረኝ" የሚለው ጌታውን፣ "ጌታዬ" የሚለው ጌታውን፣ ጌታው ኢየሱስን "ባሪያዬ" የሚለውን፣ ጌታው ኢየሱስ በማዕረግ ጌታ ያደረገውን አንዱን ጌታ አምላክ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

ይህ ቻናል የተለያዩ ኢሥላማዊ መጽሐፍቶችን እና ሌሎች አገልግሎቶችን የምታገኙበት ነው፦
https://t.me/merkatobusiness

"ዘር" ፍጡር እንጂ ፈጣሪ እንዳልሆነ እሙን እና ቅቡል ነው። ማኅፀን ውስጥ ያለውን ሽል ያለ ዘርአ ብእሲ ያስገኘው አንዱ አምላክ "አብ" ሲባል የተገኘው ሰው ደግሞ "ወልድ" ተባለ፦
ሉቃስ 1፥35 "ከ-አንቺ" የሚወለደው ቅዱስ የአምላክ ልጅ ይባላል። διὸ καὶ τὸ γεννώμενον ἅγιον κληθήσεται Υἱὸς Θεοῦ.

"የሚወለደው" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ጌኖሜኖን" γεννώμενον ሲሆን "ጊኖማይ" γίνομαι ማለትም "ሆነ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "የሚሆነው” ማለት ነው፥ "ከ" የሚለው መስተዋድድ "አንቺ" በሚለው ቃል ላይ መነሻ ሆኖ መግባቱ በራሱ ኢየሱስ ከማርያም መገኘቱን ያሳያል። ያለ ወንድ ዘር በሴት ብቻ የተገኘ ብቸኛ ልጅ ስለሆነ "ሞኖጌኔስ ሁዮስ" μονογενὴς υἱός ተብሏል፦
1ኛ ዮሐንስ 4፥9 አምላክ አንድያ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና። ὅτι τὸν Υἱὸν αὐτοῦ τὸν μονογενῆ ἀπέσταλκεν ὁ Θεὸς εἰς τὸν κόσμον.

"ሞኖጌኔስ" μονογενὴς የሚለው ቃል  "ሞኖስ" μόνος እና "ጌኑስ" γένος ከሚል ሁለት ቃላት ውቅር ነው፥ "ሞኖስ" μόνος ማለት "ብቸኛ" ማለት ሲሆን "ጌኑስ" γένος ማለት ደግሞ "የተወለደ" ማለት ነው። እንደ በጥቅሉ "ሞኖጌኔስ ሁዮስ" μονογενὴς υἱός ማለት "የተወለደ ብቸኛ ልጅ"only begotten son" ማለት ነው። አምላክ ፆታ የለውም፥ አይባዛም አይከፋፈልም። ተራሮች የተፈጠሩ ቢሆንም በፍካሬአዊ እንደተወለዱ ይናገራል፦
አሞፅ 4፥13 እነሆ ተራሮችን "የሠራ"፥
መዝሙር 89(90)፥2 ተራሮች "ሳይወለዱ"፥ πρὸ τοῦ ὄρη γενηθῆναι

"ሳይወለዱ" ማለት "ሳይሠሩ" "ሳይፈጠሩ" ማለት ከሆነ እንግዲያውስ "ወልጄሃለሁ" ሲል "ፈጥሬካለው" ማለት ነው። ዓለም ሳይፈጠር በመለኮታዊ ዕቅድ ውስጥ "የወለደው" ማለት "የፈጠረው" ከማርያም ማኅፀን ነው፦
መዝሙር 109(110)፥3 ከአጥቢያ ኮከብ አስቀድሞ ከማኅፀን "ወለድኩህ"። ἐκ γαστρὸς πρὸ ἑωσφόρου ἐγέννησά σε.

"ጋስትሮስ" γαστρὸς ማለት "ማኅፀን" ማለት ሲሆን ፈጣሪ ከአጥቢያ ኮከብ አስቀድሞ በመለኮታዊ ዕቅድ ከማርያም ማኅፀን እንደፈጠረው ያሳያል። ግዕዙ "ከርሥ" ሲለው "ማኅፀን" ማለት ነው፥ ማኅፀን ውስጥ "የሚያስሆን" አምላክ ሲሆን "የሚሆን" ደግሞ ሰው ነው። "ወለደ" ማለት "ፈጠረ" በሚል የመጣ ነው፦
ዘዳግም 32፥15 የፈጠረውንም አምላክ ተወ። וַיִּטֹּשׁ֙ אֱלֹ֣והַ עָשָׂ֔הוּ
ዘዳግም 32፥18 የወለደህን አምላክ ተውህ። וַתִּשְׁכַּ֖ח אֵ֥ל מְחֹלְלֶֽךָ

ዐውዱ ላይ መወለድ መፈጠርን ለማመልከት ከመግለጽም በተጨማሪ አንዱ አምላክ ለእስራኤል "አባት" የተባለው "ፈጣሪ" የሚለው ቃል ለማሳየት ነው፦
ዘዳግም 32፥6 የገዛህ አባትህ አይደለምን? የፈጠረህ እና የመሠረተህ እርሱ ነው። הֲלוֹא־ הוּא֙ אָבִ֣יךָ קָּנֶ֔ךָ ה֥וּא עָֽשְׂךָ֖ וַֽיְכֹנְנֶֽךָ׃

በዕብራይስጥ "አብ" אָב ማለት በተመሳሳይ "አባት" ማለት ሲሆን "የፈጠረህ" የሚለው የግሥ መደብ በራሱ አምላክ "አባት" የተባለው ስለፈጠረ መሆኑን በግልጽ ተቀምጧል፦
ኢሳይያስ 1፥2 ልጆችን "ወለድሁ" አሳደግሁም፥ እነርሱም አመጹብኝ። υἱοὺς ἐγέννησα καὶ ὕψωσα, αὐτοὶ δέ με ἠθέτησαν.

"ወለድሁ" ለሚለው የገባው ቃል "ኤጌኒሳ" ἐγέννησα ሲሆን መፈጠርን የሚያሳይ ነው፥ እስራኤል "አንድያ ልጅ" የተባለው ለዚያ ነው፦
ዕዝራ ሱቱኤል 4፥58 "የምወደው የበኵር አንድያ ልጄ" ያልኸን እኛ ወገኖችህ ግን በአሕዛብ እጅ ገባን።

እዚህ ድረስ ከተግባባን መርየም፦ "ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? ስትል አሏህ በጂብሪል "አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል" አላት፦
3፥47 ፡-"ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? አለች፡፡ ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል" አላት፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ ۖ قَالَ كَذَٰلِكِ اللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ

ይህንን በቀላሉ ከተረዳችሁ ወደ ዲኑል ኢሥላም እንድትመጡ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

ሞኖጌኔስ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥47 ፡-"ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? አለች፡፡ ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል" አላት፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ ۖ قَالَ كَذَٰلِكِ اللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ

"ዘ" ማለት በግዕዝ "የ" ማለት ሲሆን "ዘ-"ፍጥረት" ማለት "የ-ፍጥረት" እንዲሁ "ዘ-"ልደት" ማለት "የ-ልደት" ማለት ነው። ኦሪት ዘፍጥረት በግዕዙ "ዘልደት" ሲባል፣ በእንግሊዝኛ "Genesis" ሲባል፣ በግሪክ ሰፕቱአጀንት "ጌነሲስ" Γένεσις ይባላል፥ ትርጉሙ "ልደት" ማለት ነው። ሰማይ እና ምድር ደግሞ የተፈጠሩ እንጂ በእማሬአዊ የተወለዱ አይደሉም፥ ልደቱ በፍካሬአዊ ፍጥረቱን የሚያሳይ ነው፦
ዘፍጥረት 2፥4 የሰማይ እና የምድር "ልደት" መጽሐፍ ይህ ነው። Αὕτη ἡ βίβλος γενέσεως οὐρανοῦ καὶ γῆς,

"ጌኔሲስ" γένεσις የሚለው ቃል "ጊኖማይ" γίνομαι ማለትም "የሆነ" ማለት ሲሆን "ልደት" ማለት ነው። ኢየሱስ "ልደት" ያለው ፍጡር ሲሆን ይህ ልደቱ እናቱ ማርያም ማኅፀን ውስጥ ከመንፈስ ቅዱስ መፀነሱ ነው፦
ማቴዎስ 1፥18 የኢየሱስ ክርስቶስም ልደት እንዲህ ነበረ። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች። Τοῦ δὲ Ἰησοῦ Χριστοῦ ἡ γένεσις οὕτως ἦν. μνηστευθείσης τῆς μητρὸς αὐτοῦ Μαρίας τῷ Ἰωσήφ, πρὶν ἢ συνελθεῖν αὐτοὺς εὑρέθη ἐν γαστρὶ ἔχουσα ἐκ πνεύματος ἁγίου.

በተመሳሳይ እዚህ አንቀጽ ላይ "ልደት" ለሚለው የገባው ቃል "ጌኔሲስ" γένεσις ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ጊኖማይ" γίνομαι ማለትም "የሆነ" ማለት ነው፥ ኢየሱስ ያለ ወንድ ዘር ከማርያም የማኅፀን ፍሬ "የሆነ" ተአምር ነው፦
ማቴዎስ 1፥20 ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና። τὸ γὰρ ἐν αὐτῇ γεννηθὲν ἐκ Πνεύματός ἐστιν Ἁγίου·

"የተፀነሰው" ለሚለው የገባው ቃል "ጌኔቴን" γεννηθὲν ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ጌናኦ" γεννάω ነው፥ የቀጥታ ትርጉም የሚባሉት "Literal Standard Version" እና "Young's Literal Translation" በግልጽ "begotten" ብለው አስቀምጠውታል። "የተወለደው" ከመንፈስ ቅዱስ አሠራር ስለሆነ አምላክ ያ የተወለደውን ሰው "ወልጄሃለሁ" ብሎታል፦
ዕብራውያን 1፥5  እኔ ዛሬ "ወልጄሃለሁ"። ἐγὼ σήμερον γεγέννηκά σε;

እዚህ አንቀጽ ላይ "ወልጄሃለሁ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ጌኔካ" γεγέννηκά ሲሆን ሥርወ ቃሉ በተመሳሳይ "ጌናኦ" γεννάω ነው፦
"ጌታም አለኝ፦ "አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁ" መዝሙር 2፥7 ምንም እንኳን ያ ቀን በትንቢት የተነገረ ቢመስልም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ ተወለደ በእርሱም ይነገር ዘንድ ነው"።
Expositions on the Psalms (Augustine)  Psalm Chapter 2 Number 7

"እኔ ዛሬ ወለድሁ" የሚለው እምቅድመ ዓለም ሳይሆን ከድንግል መፈጠሩን ካሳየ ዘንዳ አምላክ "አባት" ሰው "ልጅ" የተባለበት ከዚህ አንጻር ነው፦
ዕብራውያን 1፥5 እኔ አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል። καὶ πάλιν Ἐγὼ ἔσομαι αὐτῷ εἰς Πατέρα, καὶ αὐτὸς ἔσται μοι εἰς Υἱόν;

"ፓቴራ" Πατέρα ማለት "አባት" ማለት ሲሆን "ሁዮን" Υἱόν ማለት "ልጅ" ማለት ነው፥ በግዕዝ አባት "አብ" ሲባል ልጅ "ወልድ" ይባላል። አምላክ አባት የሚሆነው ከዳዊት ወገብ ለሚወጣ ዘር እንጂ ለመለኮት በፍጹም አይደለም፦
2ኛ ሳሙኤል 7፥12 ከወገብህ የሚወጣውን ዘርህን ከአንተ በኋላ አስነሣለሁ፥
2ኛ ሳሙኤል 7፥14 እኔም አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል።

"ኑ በጨለማ ተመላለሱ የጥላቻን ሕይወት እንድትቀምሱ"
ቃሉ ኡመቱል ኦርቶዶክሲያህ