ቬኒሲያ @vensi Channel on Telegram

ቬኒሲያ

@vensi


" ኵሉ ጽድቅ ወኵሉ ጥበብ እምኀበ እግዚአብሔር ውእቱ"

ይህ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጣፋጭ ታሪኮች ሚቀርቡበት ቻናል ነው ። @Venisiya21 አዲሱ ቬኒሲያን በዚህ ተቀላቀሉን

ለአስተያየትዎ @Get_loza ላይ ያድርሱን

ቬኒሲያ (Amharic)

ቬኒሲያ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጣፋጭ ታሪኮች እና እምኀበ እግዚአብሔር ተግባራትን አብራራል። ይህ ቻናል በ @Venisiya21 ማህበረሰብ አዲሱ ቬኒሲያ የሚቀርቡበትን መንገድን በቀላሉ እንዲሁም መነሻቸውን ለአስተያየትዎ @Get_loza የሚረዳበትን መረጃ ለመረጃ።

ቬኒሲያ

25 Oct, 05:23


ተጠንቀቁ እንጂ አትፍሩ!

አንድ ጊዜ አንድ ንጉስ ከጦር አጃቢዎቹ ጋር ሆኖ ወደ ሌላ ሃገር ጉዞ ሲደርግ አንድ እጅግ አጥፊ የሆነ አውሎ ነፋስ ወደ እሱ አገር አቅጣጫ በመገስገስ ላይ እንዳለ ተመለከተና ባለው የጦር ኃይል አውሎ ነፋሱን አስቁሞ፣ “ወደ እኔ ሃገር አቅጣጫ በመሄድ ላይ ነህ፡፡ ከእኔ ሃገር ሰው ማንንም እንዳማታጠፋ ቃል ካልገባህ አታልፍም አለው” አውሎ ነፋሱም፣ “በእርግጥ ነው ወደዚያ አቅጠጫ ነው የምሄደው፤ ነገር ግን የአንተን ሃገር ሕዝብ በፍጹም እንደማልነካ ቃል እገባልሃለሁ” አለው፡፡

ንጉሱ ከጉዞው ሲመለስ ከሃገሩ ሰዎች በርካታዎቹ እንደሞቱ ሰማ፡፡ በጣም በመቆጣት አውሎ ነፋሱን ተከታትሎ ደረሰበትና፣ “ማንንም እንደማትነካ ቃል ገብተህልኝ ለምንድን ነው ብዙ ሰው የገደልከው?” አለው፡፡ አውሎ ነፋሱም እዲህ ሲል መለሰ፣ “እኔ በሃገርህ አጠገብ አለፍኩኝ እንጂ የሃገርህን ህዝብ አንዱንም አልነካሁም፡፡ እንደሰማሁት ከሆነ ግን ከባድ አውሎ ነፋስ መጣ የሚል ወሬ ተወርቶ በፍርሃትና በድንጋጤ አንዳንዱ በልብ ድካም፣ አንዳንዱ ሲሯሯጥ እርስ በርሱ ተረጋግጦ ነው የሞተው”፡፡

አንዳንዴ በሃገራችን ከሚከሰተው ችግር ይልቅ በችግሩ ላይ ያለን አመለካከት፣ የሚወርሰን ፍርሃት፣ የምንሰጠው ተገቢ ያልሆነ ምላሽና የፍርሃትና የድንጋጤ ስሜታችን ከማየሉ የተነሳ አዋቂዎቹ የሚነግሩንን መመሪያ በአአምሯችን አስበን አለመከተላችን ነው የሚያጠፋን፡፡

አንባቢዎቼ በወቅቱ በደረሰብን አስጊ ሁኔታ ስለራሳችንና ስለቤተሰቦቻችን የማሰባችን ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በምክንያት የለሽ ፍርሃት ከመተራመስና ራስን ለከፋ ነገር ከማጋለጥ እንጠበቅ፡፡

በዚሁ አጋጣሚ ንስሐ ገብተን ፣ ቅዱስ ቁርባንን ተቀብለን እንዘጋጅ

ፈጣሪ እናንተንና የእናንተ የሆኑትን ሁሉ ይጠብቅላችሁ፡፡

╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Venisiya21 @Venisiya21
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯

ቬኒሲያ

16 May, 12:43


https://t.me/joinchat/BQ0olWHCdkE5NmE0

ቬኒሲያ

09 Mar, 17:51


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን #አብይ ፆም

ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡ ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡-

ሀ. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ
ለ. በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ
ሐ. ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ ነዋይ' ድል የተመቱበት ስለሆነ ነው፡፡

በቤተክርስቲያን ስያሜ መሰረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፡-

1. ዘወረደ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡

2. ቅድስት
ይህ የሁለተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን የተባለበትም ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ ዕለት ዕለተ እግዚአብሔር የተባለች የሰንበት ክርስቲያን ቅድስናን ያመለክታል ምክንያቱም የዚች ዕለት ጌታ እርሱ ቅዱስ እግዚአብሔር ነውና ስለዚህም ዕለተ ሰንበት ቅድስት ተብላለች፡፡

3. ምኩራብ
ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ይህች ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ምኩራብ ማለት የቤተ አይሁዳውያን የጸሎት ቤት ነው፡፡

4. መጻጉዕ
ይህ የአራተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ እውራንን ማብራቱ ለምጻምን ማንጻቱ ሽባዎችን መተርተሩ የሚያነሳ መዝሙር የሚዘመርበት እንዲሁም እነዚህ ሁሉ ድንቅ ገቢራተ ታምራቶች የሚዘከሩበት ዕለት ነው፡፡

5. ደብረ ዘይት
ይህ የአምስተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚወሳበት ሰንበት ነው፡፡ ደብረ ዘይት ማለት ወይራ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡

6. ገብርኄር
ይህ የስድስተኛው ሳምንት ሰንበት ስያሜ ሲሆን ይህም ዕለት ለጌታው ታማኝና በጎ የሆነው ባርያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ተብሎ እንደተመሰገነ የሚነገርበት ዕለት ነው፡፡

7. ኒቆዲሞስ
ይህ የሰባተኛው ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ይህም ዕለት ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር በሌሊት ወደ ጌታው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እየመጣ ይማር እንደነበረ ይታሰብበታል በዚም ዕለት የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡

8. ሆሳዕና
ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡ ሆሳዕና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::
ጾሙን የበረከት ጾም ያድርግልን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን

ቬኒሲያ

21 Feb, 19:50


ጾም መድኃኒት ናት፡፡ አወሳሰድዋን በትክክል ላላወቁ ግን ጥቅም የላትም፡፡ ይህችን መድኃኒት የሚወስድ ሰው በየስንት ሰዓቱና በምን ያህል መጠን እንደምትወሰድ፣ ለምን ዓይነት በሽታ እንደምትጠቅም፣ በየትኛው አከባቢና የአየር ኹናቴ እንደምትወሰድ፣ ከእርሷ ጋር የሚኼዱና የማይኼዱ ምግቦችን እንዲሁም ከእርሷ ጋር የማይስማሙ ሌሎች ነገሮችን ለይቶ ማወቅ አለበት፡፡ እነዚህን ግምት ውስጥ አስገብቶ የማይወስዳት ሰው ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ታመዝንበታለች፡፡ አንድ በሐኪም የታዘዘልንን የደዌ ዘሥጋ መድኃኒት እንዲያሽለን ስንፈልግ በጥንቃቄ ልንወስደው ያስፈልጋል፤ የነፍሳችንን ደዌና በአእምሮአችን ውስጥ ያሉ ቁስሎችን ለመፈወስ ብለን በምንወስደው መድኃኒት ደግሞ ከዚህ የበለጠ መጠንቀቅ ይገባናል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ቬኒሲያ

01 Jan, 19:56


የግዝት በሃላት ስንት ናቸው ?
በግዝት ቀናት ይሰገዳሎይ ?
የትኛው ስግደት እንስገድ ?
ሥንታይነት ስግደት አለ ?
እነማናቸው የሚለው የብዙሆቻችን ጥያቄ ነው ?

ቬኒሲያ

01 Jan, 13:57


ስደተኞች ክፍል 8
የቆርኔሌዎስ ሚት ኔርያ ንጭንጯ ብሶበታል፡፡ ሄለንን ቁም ስቅሏን ታሳየታለች፡፡ ለአንድ ሰሞን አዛዡ ባልዋ ለግዳጅ ከወጣ ጦሟን አውላ ታሳድራት ነበር፡፡ ሄለን ከጸሎት በቀር ውላ ስታነብ ታድራለች፡፡ አንደበትዋ ዝምታን እንጂ መናገርን አልለመደውም፡፡ በኋ ግን ቆርኔሌዎስ ሁኔታውን እየተረዳው በመምጣቱ ወደ ግዳጅ ሲጣ የሚበላ ነገር መኝታ ቤቷ ውስጥ ደብቆ ያስቀመጥላት ጀመር፡፡ ነገር ግን የኔርያን ጠባይ የሄለን ደግና የዋህ ልቡና ሊቋቋመው አልቻለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ክርስቲያን መሆንዋ ምርር ያስብላታል፡፡ መልሳ ደግሞ የወንድምዋን ምክሮች ስታስባቸው ትጽጽናናለች፣ ትጸናለችም፡፡ አንድ ቀን ከዚህ አስከፊ ኑሮ ወጥታ ወደ ኢየሩሳሌም እንደምትጓዝ በዚያም ወንድሟን እንደምታገኘው ስታሰብ ደግሞ ብሩህ ተስፋ ይታያታል፡፡

መቼም በክርስትና ጉዞ ተስፋ ከሌለ የሚጣፍጥ ነገር ባልኖረም ነበር፡፡ ሕይወት የጨለመ ኑሮ የመረረ ሲመስል ፊት ለፊት የሚጠብቀንን የአባታችንን የእግዚአብሔርን በረከት ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት ባናስብ ኖሮ ሁላችንም ራሳችንን ባጠፋን ነበር፡፡ ነገ የኛ በእግዚአብሔር እጅ መሆንዋን ባንረዳ እግዚአብሔር ሁሉን ለበጎ እንደሚያደርገው ባናምን ኖሮ መንፈሳችን ተሠብሮ ስብእናችን ይሞት ነበር፡፡ ነገር ግን ተስፋ አለን፡፡ ተስፋ ኑሮን የሚያለመልም የመንፈስ ውኃ ነው፡፡

ቆርኔሌዎስ ወደ ጎረቤት ሀገር ሰው ልኮ ማርቆስን አስፈልጎት ነበር፡፡ ነገር ግን ከጥቂት ቀናት ጀምሮ የት እንደሄደ አለመታወቁን ነገሩት፡፡ ይህን ለሄለን አልነገራትም፡፡ ተስፋ ትቆርጣለች ብሎ ፈራ፡፡ሄለንን ምን እንደሚደርጋት ዘወትር ያሥጨንቀዋል፡፡ በእንዲህ አይነት ኑሮ እርሷን ሆነች እርሱ እስከ መቼ ለመዝለቅ እንደሚችሉ ሲያስበው ዙርያው ገደል ይሆንበታል፡፡ እርስዋ ኢየሩሳሌም ሆይ የሚለውን መዝሙር መኝታ ቤቷ ውስጥ ሆና ዝቅ ባለ ድምጽ ስትዘመር በሰማ ቁጥር ልቡን ይበላዋል፡፡ ላይ ላዩን ሳይሆን ውስጥ ውስጡን ያነባል፡፡ በመጨረሻ የተደገሰልትን የሞት ድግስ ያላወቀው ቆርኔሌውስ ይህን ጭንቀቱን ጨዋ እየሆነ በመምጣቱ ለወደደው ለአኒባል ሊያየው ፈለገ፡፡ አኒባል ደግሞ መርዙን ጨብጦ ቆርኔሌዎስን ለውይይት ሳይሆን ለግድያ እየጠበቀው ነው፡፡

ለኔርያ የባልዋ ሄለንን መቅረብ፣ ወደ መኝታ ቤቷ ገብቶ “ኢየሩሳሌም የሚለውን መዝሙር መዘመርና ጸጉሯን እየደባበሰ ሲያወራት መመልከት ቅናቷ ያባብስባታል፡፡ በመጥረቢያ በያቸው በያቸው የሚል ስሜት ፈጥሮባታል፡፡ ባልዋን የተነጠቀች እየመሰላት፡፡ ቆርኔሌስ ደግሞ ደጋግሞ ይህን ክፉ ዐመሏን እንድትተው ቢነገራትም የምትሰማ አልሆነችም፡፡ እንዲያውም እየደለላት መሰላት፡፡ አንድ ቀን ኔርያ ቤቷን ስታጸዳዳ በጨርቅ የተጠቀለለ የሚሰነፍጥ ነገር አገኘች፡፡ እየፈራች በእንጨት ጎልጉላ ፈታችው፡፡ የተቀበረባት መተት ስለመሰላት ድንጋጤና ንዴት ወሯታል፡፡ በመጨረሻም በአጠገብዋ በሚገኘው መንደር ወዳለው መድኃኒት ዐዋቂ በምሽ ገስግሳ ወፈር ያለ ጉርሻ በማስታቀፍ ምንነቱን ጠየቀችው፡፡ ያን ጊዜ ነበር ገዳይ መርዝ መሆኑን የተረዳችው፡፡
“የነዚያ እባቦች መርዝ ነው! እኔን ኔርያን በመርዝ ሊገድሉ ከዚያ እነርሱ ሊምነሸንሹበት” ከት ብላ ሳቀች፡፡ “እኔ ልጅት ልኳን እሰጣታለሁ፡፡” እየተስፈነጠረች ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡ ያን መርዝ የደበቀው ግን አኒባል ነበር፡፡ ካመጣው መካከል ግማሹን ቀንሶ ካዘጋጀ በኋላ የቀረውን ለመጠባበቂያ ደበቀው፡፡ ነገረኛ የማይጎለጉለው የለምና ኔርያ አገኘችው፡፡ ያ ቤት የሞት ጥላ አጠላበት፡፡ ኔርያ ለሄለን አኒባል ለቆርኔሌዎስ፡፡
አንድ ቀን ኔርያ በቤትዋ ግብዣ አደረገችና ቆርኔሌዎስን አኒባልንና ሌሎች ጓደኞቹን እንዲጋብዝ ነገረችው፡፡ ቆርኔሌዎስ ሄለን ከመጣች ጊዜ ጀምሮ የቀረ ግብዣ ዛሬ እንዴት ትዝ እንዳላት ገርሞት በደስታ ተቀበለው፡፡ አኒባል ደግሞ ይቺን መሰልዋን አጋጣሚ በጉጉት ይጠብቃት ነበር፡፡ ስለዚህም ሲመጣ ባዶውን አልነበረም፡፡ መርዙን ሰልቆ እንጂ፡፡ ኔርያ በጓዳዋ ጉድጉድ ስትል አኒባል ሊረዳት ገባ፡፡ የተጠሩት መኳንንት ስለነበሩ በማስተናገዱ ቢሳተፍ ጥያቄ ውስጥ እንደማይጥለው አውቋል፡፡ ኔርያም ለተንኮሏ መንገድ እንደሚከፍትላት ስለተረዳች ተቀብላዋላች፡፡

መጠጡን ከቀንድ ወደ ተሰሩት ዋንጫዎች እየቀዳች የማን እንደሆኑ ለይታ ሰጠችው በመጀመሪያዎቹ ዋንጫዎች ላይ ሁለቱም ምህረት አድርገዋል፡፡ ግን አልተነጋገሩበትም፡፡ ሁለተኞቹ ዋንጫዎች ጓዳውን ሲለቁ ግን አስቀድሞ የኔርያ መርዝ በሄለን ዋንጫ ላይ ተሞጅሮ ነበር፡፡ አኒባል ደግሞ ልቡ ዘዴ እያውጠነጠነ ነው፡፡
“እስቲ እርስዎ ብቅ ይበሉና ብሉ ጠጡ ይበሉ” አላት የተፈለገች አስመስሎ፡፡ “እንግዳ ጋብዘው ጓዳ ሲቀመጡ ዛሬ የመጀመሪያዎ እኮ ነው ኔርያ እውነቱን መሆኑ ገባት፡፡ ከዚህ በፊት ፈገግታ እየጋበዘች ታስተናግዳለች እንጂ ጓዳ ተቀብራ አታመሽም ነበር፡፡ “አንተ መጠጡን ይዘኸው ና!” አለችና ልብስዋን አስተካክላ ወደ እልፍኙ ብቅ ስትል አኒባል መርዙን በቆርኔሌዎስ ዋንጫ ላይ ዶለው፡፡

ይቀጥላል…..


ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Vensi @Vensi @Vensi
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯

ቬኒሲያ

31 Dec, 17:43


ወንድ የሆነ ይቀንሰው

አሁን ያለንበት ወቅት ጾመ ነቢያት ማለትም የገና ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ከገባ ሳምንታት ቢልፈውም አንገታቸው ላይ ማተብ ያሰሩ ሁለት ባልንጀራሞች ከአንድ ሥጋ ቤት በረንዳ ላይ ሆነው ይህን ጥሬ ሥጋ በወግ በወጉ እየቆረጡ ወደ ሆዳቸው ይልኩታል፡፡ በመሐል አንደኛው የፕቴስታንታዊ ተሐድሶ አራማጆች ጾም ይቀነስ እያሉ በየመንደሩ የሚያስወሩትን ወሬ ሰምቶ ኖሮ “ጾም ሊቀነስ መሆኑን ሰምተሃል እንዴ? ሲል ባልንጀራውን ይጠይቀዋል፡፡ ባልንጀራውም የጎረሰውን ጥሬ ሥጋ እያኘከ በእጁ በያዘው ቢላ ደግሞ በቀጣይ የሚጎርሰውን እየቆረጠ “ማነው እሱ ቀናሹ?” ሲል ይጠይቃል፡፡ ባልንጀራውም “እኔ ምን አውቄ ያው ቄሶቹ ይሆናሉ፤ ሌላማ ማን ሊሆን ይችላል” ሲል ይመልሳል፡፡ በዚህ ጊዜ ባልንጀራው በስጨት እንደማለት ካደረገው በኋላ በእጁ ላይ ያለውን ቁራጭ ሥጋ በእንጀራ ጠቅልሎ በአዋዜ እያጠቀሰ “ይህማ አይደረግም፤ እስኪ ወንድ የሆነ ይቀንሰውና እንተያያለን፡፡ አለ ይባላል፡፡

ይገርማል አንዳንድ ሰው ክርስትናውን የሚኖረው አምኖበት ሳይሆን በስሜት ነው፡፡ እሱ ራሱ የሚቀንሳቸውና የሚሽራቸው በርካታ የቤተክርስቲያን ሥርዓቶች እያሉ ስለ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ህልውና የሚከራከርን ሰው ምን ትሉታላችሁ?በዚህ ታሪክ መነጽርነት ሁላችንም ወደ ራሳችን እንመልከት፡፡ እውነት ለመናገር ከሰባቱ አጽዋማት በትክክል እየጾምን ያለነው ስንቱን ነው፡፡

እስኪ እውነት እንነጋገር ያለ ቤተክርስቲያን ውሳኔና ቀኖና ማንም ሳያሰናብተን በራሳችን ስልጣን የሻርናቸውና የማንጾማቸው ሌሎችም እንዳይጾሙአቸው የምናከላክላቸው አጽዋማት የሉምን ስለምን ይህንን እናደርጋለን?እኛ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጪ ሆነን ሌላውን ወደ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ማምጣት እንዴት እንችላለን?

ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Vensi @Vensi @Vensi
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯

ቬኒሲያ

31 Dec, 16:50


ጸበል የቅድስት ቤተ-ክርስትያናችን መንፈሳዊ ሕክምና ነው፡፡ ቤተ-ክርስትያንን መንፈሳዊ ሆስፒታል ናት ።

‹‹ሂድና በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠብ አለው፡፡ ስለዚህ ሄዶ ታጠበ/ተጠመቀ/ እያየም መጣ›› ዮሐ 9÷7

ቬኒሲያ

30 Dec, 18:09


💡💡💡 ያጣ ለማኝ 💡💡💡
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯


ቀበሮዋ አንድ የበሰለ የወይን ዛላ ተንጠልጥሎ ለመብላትም አስጎምጅቶ ታገኛለች፤ በመሆኑም በጣም ካልዘለለች በስተቀር እንደማታገኘው ስለታወቃት እንጣጥ እያለች ብዙ ሞከረች። ይሁን እንጂ ወይኑ እንዳሰበችው በቀላሉ የምትደርስበት አልሆነም። ወደኋላ ተንደርድራ በጣም ዘለለችና የመጨረሻ ሙከራ አደረገች። ይሁን እንጂ ፈጽሞ ልትደርስበት አልቻለችም። ወይኑ በአለባበሱ በጣም ልዩ ነው፤ ለዐይን የሚያምር ለመብላትም የሚያስጎመጅ ነው። ወይኑን ትታ እንዳትሄድ ያስጎመጃል እንዳትበላው ደግሞ ስትዝል ብትውልም አልደረሰችበትም። ስለዚህ ''እንደውም ይኼ ወይን አልበሰለም'' ብላ ትታው ሔደች።

🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟

"ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሔዳል'' የሚባለው ለእንደዚህ ዐይነቱ ነው። የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለመናፍቃን ያልተመቸችው አላዋቂ ወገኖቻችን እንደሚሉት የዶግማና የቀኖና ችግር ኖሮባት ሳይሆን ይህንን መኖርና መፈጸም ስላቃታቸው ብቻ ነው። መጾም ያቃታቸው ጾምን አያስፈልግም ሲሉ ንጽሕናቸውን ያጎደፉና ቆባቸውን የጣሉት ደግሞ ምንኩስና አያስፈልግም ይላሉ። ያቃተንንና ያልተደረሰበትን ነገር ሁሉ አያስፈልግም ብሎ መንቀፍ የቀበሮ ጠባይ ነው። የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሥጋዊ ዕውቀት የማትመረመር ብትሆንም ትምህርቷ ግልጽ፤ ተልኮዋም የታወቀ ነው "ወንጌላችን የተከደነ ቢሆንም እንኳ የተከደነባቸው ለሚጠፉት ነው" እንዲል 1ኛቆሮ 4፥3

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Vensi @Vensi @Vensi
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯

ቬኒሲያ

29 Dec, 18:21


የማይበድል ባርያ
የማይምር ጌታ የለም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እብሉይ የተባለ በግ ጠባቂ ነበር ከኃጥያት ስራ የቀረው የለም። ያመነዝራል፣ ይሰርቃል ይገድላል በዚህም የሰይጣንን ሥራ እየፈጸመ ፵(40) ዓመት ኖረ።

በአንዲት ዕለትም ከቀኑ እኩሌታ የመውለጃዋ ጊዜ የደረሰ እርጉዝ ሴትን አየ ሰይጣንም በልቡ ክፉ ሃሳብን ጨመረበት እንዲህም አለ ሆዷን ሰንጥቄ ህጻኑ እንዴት እንደሚተኛ ማየት አለብኝ ብሎ ጸጉሯንም ጎትቶ ከመሬት ጣላት ሆዷንም በቢላ ሰንጥቆ ልጁንም እናቱንም ገደላቸው።

በግ አርቢውም የሰራውንም ኃጥያት ተመልክቶ እጅግ አዘነ የማይበድል ባርያ የማይምር ጌታ የለም ብሎ አምርሮም እያለቀሰ ወደ በረሀ ሄዶ ፵(40) ዓመት ስለበደሉ አለቀሰ አጋንንትም ተገልጸው ከአንተ ዲያቢሎስ አባታችን ይሻላል እያሉ ያፌዙበት ነበር።እሱ ግን በተጋድሎ በረታ።

የእግአብሔር መልአክም ተገልጾ ስለ ሴቲቱ ደም ጌታ ይቅር ብሎሃል ስለ ልጁ ግን ይቅር አላለህም አለው አባ እብሉይም ተጨማሪ ፵(40) ዓመት ተጋደለ ጌታም ይቅር አለው።(ስንክሳር የካቲት ፭)
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ክርስቲያን ሆይ እግዚአብሔር ይቅር ባይ መሐሪ አምላክ ነው እንደ ቸርነቱ ነው እንጅ እንደኛ በደልማ በጠፋን ነበር።ስለዚህ ንስሐ ከመግባት አንቦዝን
@Vensi @Vensi @Vensi

ቬኒሲያ

28 Dec, 19:03


በተለያየ ሰንበት ት/ቤት ውስጥ በስነ ፅሁፍና ኪነ ጥበባዊ ክፍል የምታገለግሉ ሰዎች 👉 @Sentsehuf_hibert በዚ ሊንክ ተቀላቀሉን በጋራ የምንሰራው ስራ አለ

ቬኒሲያ

28 Dec, 17:29


አንድ ሰው ነበር በባህር ብቻውን በመርከብ እየተጓዘ በመአበል አደጋ ተመታና መርከቡ ተሰባብራ ባህሩ ውስጥ ሰመጠች ሰውዬው እንደምንም እራሱን አድኖ አንድ ደሴት ላይ ያርፋል። እዚያም ደሴት ላይ ትንሽዬ ጎጆ ነገር ሰርቶ
ለቀናት ለብቻው እዛች ደሴት ላይ ይኖራል።

:ምግቡንም ዓሳ አያጠመደ እየተመገበ ቆየ አንድ ቀን ዓሳ ሊያጠምድ ወደ ባህሩ በሄደበት ቅፅበት እዛች ደሴት ላይ ጭስ ለቀናት ዞር ብሎ ሲያይ ያቺ
ጎጆው እየነደደች ነው …… እየሮጠ ቢመለስም ጎጆዋን ሊያድናት አልቻለም ለካ ዓሳ ለመጥበስ ያቀጣጠለው እሳት ተያይዞ ጎጆውን አንድዷታል፣ አለቀሰ ፈጣሪውን ወቀሰ እንዴት እዚህ ባህር ላይ ብቻዬን ጥለኸኝእያለ ከቤተሰቦቼ ነጥለኸኝ ስታበቃ በስንት ልፋት የሰራኋትን ጎጆ
ታቃጥልብኛለህ ብሎ አለቀሰ ። አማረረ ፤ በዚህ ሁኔታ ላይ አንድ ድምፅ ሰማ ወደ ድምፁ ፊቱን ሲያዞር አንድ ትልቅ መርከብ ወደሱ አቅጣጫ እየመጣ ተመለከተ በሁኔታው እጅግ በጣም ተደሰተ …… የመርከቡ ሰዎች መጥተውም ጭነው ወሰዱት፣ ከዚያም ለመርከቡ ሰዎች ጥያቄ አቀረበላቸው ! እንዴት አገኛቹኝ እዚህ አካባቢ
እዚህ ባህር ላይ ማንም አይመጣም እኮ እናንተ እንዴት
አገኛችሁኝ ?

: መርከበኞቹም እኛማ በዛኛው በኩል ዞረን እየሄድን ነበር በዚህ በኩል ጭስ አየንና እዚህ ሰው
ይኖራል ብለን መጣን አንተ አገኘንህ አሉት ።

አቤቱ ጌታዬ ለካ ከዚህ ከስቃዬ ልታውጣኝ ፈልገህ ነው ትንሿንጎጆዬን ያፈረስካትና ወደ ትልቁ ቤቴ ልትወስደኝ ፈቃድህ የሆነው አለ።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
እኛ ክርስቲያኖች ሁሉም ነገር ለበጎ እንደሆነ እናምናለን .....እግዚአብሔር የሚያስብልንን ይሰጠናል።

@Vensi @Vensi @Vensi
⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️⭕️

ቬኒሲያ

27 Dec, 14:38


ይህን መንፈሳዊ ቻናል ምን ያህል ትከታተሉታላችሁ?
public poll

በደንብ እከታተላለሁ ተለውጬበታለሁ – 157
👍👍👍👍👍👍👍 91%

አልከታተልም – 15
👍 9%

👥 172 people voted so far.

ቬኒሲያ

27 Dec, 12:33


በጥንት ዘመን አንድ ንጉሥ በሁለት ሰዎች ላይ ሞት ፈርዶ ሲያበቃ ለመጨረሻ ጊዜ የምትናገሩት ሐሳብ ካለ ይዛችሁት ከምትሞቱ ሐሳባችሁን ግለጹ አላቸው። አንደኛው የሞት ፍርዱ ላይነሳልኝ ምን አደከመኝ ብሎ ያስብና ምንም የምናገረው ነገር የለኝም የለኝም ይላል።

ሌላኛው ግን ዝም ብዬ ከምሞት ብሎ ያስብና አንድ መላ ያመጣል። ንጉሱ አንድ በጣም የሚወዳት ምርጥ ፈረስ እንዳላቸው ስለሚያውቅ "ንጉስ ሆይ ሺ ዓመት ይንገሡ! እኔ የሚወዱትን ፈረስዎ ለአንድ ዓመት መብረር ላለማምውደ እችላለሁ" ይህ የሚሆነው ግን የአንድ ዓመት ዕድሜ ከተሰጠኝ ብቻ ነው ይላል።

ንጉሡም አባባሉ ቢያስገርመውም "የሚበር ፈረስ ያለው በዓለም ላይ ብቸኛ ንጉሥ" መባሉን ውስጡ ስለወደደው በነገሩ ተስማምቶ የአንድ ዓመት ዕድሜ እንዲሰጠው ፈቀደ ።

ከችሎቱ መልስ ያ ዝም ያለው ባልንጀራው በዚህኛው ላይ ስላቅ ተናገረበት "ወፈፍ ያረግሃል ልበል? አሁን በየት ሀገር ነው ፈረስ የሚበረው? አንድ ዓመት ረዥም መስሎህ ነው ይህን የማይሆን ነገር የምትናገረው? ምናለ ጣርህን ባታበዛው" አለው።

ብልሁ ሰው ግን ተኩራርቶ እኔ እንዳንተ ዝም ብዬ አልሞትም ይህን ሃሳብ ሳቀርብ ነጻ ለመውጣት አራት አማራጮች አሉኝ እነርሱም፡-
፩ኛ. #በዚህ #አንድ #ዓመት #ንጉስ #ሊሞቱ #ይችላሉ

፪ኛ. #እኔ #እራሴ #ልሞት #እችላለሁ

፫ኛ. #ፈረሱ #ሊሞት #ይችላል

፬ኛ. #ማን #ያውቃል #ምንአልባት #ፈረሱን #መብረር #አስተምረው #ይሆናል። አለው ይባላል።።።።።
🌀🌀🌀🌀🌀🌀🌀🌀🌀🌀
እኛም ዝም ብለን ከነኃጥያታችን ልንሞት አይገባም ንስሐ ገብተን ሥጋ ወደሙን ተቀብለን ነጻ ወጥተን ብንሞት ይሻለናል
❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️
👇👇👇👇👇
👉 @Vensi 👈
👉 @Vensi 👈
👉 @Vensi 👈
👆👆👆👆👆

ቬኒሲያ

26 Dec, 17:41


ድሮ ነው በአንድ ሀገር ሰው የመብላት እርኩስ ግብር የተወሐደው አንድ ሰው ነበር። ከእለታት አንድ ቀን አንድ ክርስቲያን እሱ ባለበት ጎዳና አቋርጦ ሲያልፍ አንቆ ይይዘውና እያጣደፈ ወደ ጎጆው ያስገባዋል።

ምንድነህ ብሎ ሲጠይቀው ክርስቲያን መሆኑን ሳይደብቅና ሳያፍር ይገልጽለታል። እስኪ ያንተን ክርስትና አየዋለሁ ይልና ተቆራርጦ የተቀቀለ የሰው ሥጋ ከእነንፋሎቱ ያቀርብለታል። በመቀጠልም ሰይፍ ቃጥቶበት "ብላ" ይለዋል።

ያ የጨነቀው ግብ መለኛ ክርስቲያን አልበላም ቢል ይሞታል ልብላ ቢልም እርም ነው። ስለዚህ ዘየደና "እሺ" እበላለሁ ግን ይብረድ ይለዋል ...

" ይብረድና ትበላታለህ" ብሎ ይቆማል። ይቺን ክፍተት ያገኘው ታማኙ ክርስቲያን ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል ከገባበት ፈተና እንድታወጣው እመቤታችንንም ይማጸናታል። በመጨረሻም ውጤቱ ተቀየረ ያ ጨካኙ ሰው መናገር ጀመረ።

ወንድሜ ሄይ አንተ ታላቅ ሰው ነህ ይብረድ በማለትህ የእኔንም ልብ አበረድከው። ይህን ክፉ ነገር ላደርግብህ አልፈልግም በሰላም ሂድ ብሎ አሰናበተው።

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ዛሬም የሁለትና ከዚያም ያነሰ ደቂቃና ሰከንድ ትዕግስት እያጣን ነገር ናብረድ እየተሳነን የማይተካው ሕይወት ሲያልፍ ፣ ትዳር ሲፈታ ፣ልጆች ሲበተኑ እናያለን።
ክርስቲያን ሆደ ሰፊ ነገር አላፊ ነው።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@Vensi @Vensi @Vensi
👆👆👆👆👆👆👆👆👆

ቬኒሲያ

26 Dec, 07:45


ባሏ በህመም ምክንያት ከስራ የተሰናበተባት እና 7 ልጆች ያሏት አንዲት እናት ቤት ውስጥ ምንም የሚላስ የሚቀመስ ነገር ባለመኖሩ ከሰፈሯ ራቅ ብሎ ወደሚገኘው ሱቅ በመሄድ በብድር አስቤዛ እንዲሰጣት ባለሱቁን ትጠይቀዋለች።
ባለሱቁም ሂጂ ከዚህ አልሰጥሽም ይላታል። ነገር ግን ባዶ የሆነባት እናት አጥብቃ ትለምነው ጀመር። ገንዘብ እንዳገኘሁ ወዲያውኑ ነው የምከፍለው ብትለውም እኔ ለማላውቀው ሰው ብድር አልሰጥም በማለት ይመልስላታል። ነገር ግን ሴትየዋ አጥብቃ በምትለምንበት ጊዜ ከሱቁ እቃ ሊገዛ የመጣ አንድ ደንበኛ ንግግራቸውን ሲያደምጥ ቆይቶ ነበርና ለባለሱቁ እኔ ዋስ እሆናለው የምትፈልገውን ስጣት ቢለውም በእምቢታው ቀጠለ።
ባለሱቁ እንደገና በማፌዝ የምትፈልጊውን አስቤዛ በሙሉ በወረቀትሽ ላይ ፅፈሽ ወረቀቱን ሚዛኑ ላይ አስቀምጪ በሱ ክብደት ልክ የምትፈልጊውን እሰጥሻለው ሲላት ለጥቂት ጊዜ ዝም ብላ ስታስብ ቆየችና ወረቀት ተቀብላ የሆነ ነገር ፅፋ ሚዛኑ ላይ ጣል ስታደርገው ሚዛኑ ድንጋይ የተጣለበት ያክል ወደ ታች ወደቀ።
ባለሱቁና የሴየዋን ሁኔታዋን ይከታተል የነበረው ደንበኛ ሚዛኑን በማየት ይገረሙ ነበር። ባለሱቁ ባንደኛው ሚዛን ላይ የሚያስቀምጠው የሴትየዋን አስቤዛ በሌላኛው ጎን ያለውን ወረቀት ከፍ አድርጎ ሁለቱ የሚዛኑ አካሎች መመጣጠን አልቻሉም። እናም መጨመር መጨመር ሆነ ስራው። በስተመጨረሻም ምን አይነት ስልት ነው የተጠቀምሽው ብሎ ወረቀቱን አንስቶ ማንበብ ጀመረ።
ከዛም እጅግ በጣም ተገረመ ውስጡ ያለውም ፅሁፍ የምትገዛቸው ነገሮች ዝርዝር ሳይሆን "ፈጣሪዬ ሆይ የሚያስፈልገኝን አንተ ታውቃለህና ያለህበትን ሁኔታዬን ላንተ ሰጥቻለው" የሚል ነበር። ባለሱቁም ሚዛኑ ላይ የተቆለለውን ሁሉን አስቤዛ ከሰጣት በዋላ ወደ ቤቷ ስትመለስ በዝምታና በግርምት ያያት ነበር።
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
አዎ የሚያስፈልገንን ነገር ሁሉ ፈጣሪ ከኛ ቀድሞ ያውቃል እኛ ልምድ ሆኖብን ብንናገርም እሱ ሁሉን ያውቀዋል። እንዲሁም ደሞ ምንም ነገር ከፈጣሪ አይበልጥምና ከልባችን ቅን ምኞትን በፈጣሪ ወይም በቅዱስ እግዚአብሔር ላይ ጥልቅ እምነት ታክሎበት ምኞታችን በእግዚአብሔር ላይ ከሆነ ሚዛን ይደፋል ድልም እናደርጋለን።
የቅዱስ እግዚአብሔር ምህረትና ቸርነት አይለየን።
🙏🙏🙏አሜን🙏🙏🙏

ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Vensi @Vensi @Vensi
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯

ቬኒሲያ

25 Dec, 19:32


💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢
ሰውየው አስር ክፍል ቤት ሠርቶ ብቻውን ሲኖር አንድ ቀን በሩ ተንኳኳ ሲከፍት ጌታ ነው፡፡ "ውይ አምላኬ
ጌታዬ አንተ እኔ ቤት መጣህ?" ብሎ በደስታ ተቀብሎት አንድ ክፍል ቤት ሰጥቶት መኖር ጀመሩ፡፡ በሌላ ጊዜ በሩ ተንኳኳ፣ ሲከፍት ሰይጣን 😈 ነው፡፡
ተበሳጭቶ ይዘጋና "ጌታዬ ሆይ አንተ እኔ ቤት እያለህ ሰይጣን የእኔን ቤት እንዴት ያንኳኳል?" አለው፡፡ ጌታም "ቤቱ የአንተ እንጂ የእኔ አይደለም " አለው፡፡ ሰውየውም ተሰምቶት ሁለት ክፍል ቤት ለጌታ ጨምሮለት እርሱ ሰባት ክፍል ይዞ
መኖር ቀጠሉ፡፡ በሩ ተንኳኳ ሲከፈት ሰይጣን 😈 ነው፡፡ ተበሳጭቶ ይዘጋና "ጌታዬ ሆይ አንተ እኔ ቤት እያለህ
ሰይጣን የእኔን ቤት እንዴት ያንኳኳል? " አለው፡፡ ጌታም " ቤቱ የአንተ እንጂ የእኔ አይደለም " አለው፡፡ ሰውየውም ተሰምቶት ከጌታ ጋር እኩል ለእኩል ተካፈለ፡፡ ነገር ግን ቤቱ ከቀድሞ ይልቅ ተንኳኳ ፡፡ አዝኖም ይዘጋና ጌታ ሆይ አለው፡፡ ጌታም የቀድሞውን መልስ ሰጠው፡፡ በዚህ ጊዜ ሰውየው ለራሱ አንድ ክፍል ቤት ይዞ ዘጠኙን ክፍል ቤት ለጌታ ሰጠው፡፡ ነገር ግን ከቀድሞው ይልቅ በጣም ተንኳኳ፡፡ ቢከፈት ሰይጣን
ነው። በሩን ይዘጋና ወደ ጌታ ሄዶ " ጌታ ሆይ ምሥጢሩ ምንድን ነው? " አለው፡፡ "ጌታ ግን ቤቱ የአንተ እንጂ የእኔ አይደለም "አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ዐሥሩንም ክፍል ለጌታ አስረከበ፡፡ ጌታም
አንድ ክፍል ቤት ለሰውየው ሰጠው፡፡ በሩም ተንኳኳ፡፡ ጌታም ሊከፍት ተነሣ፡፡ ሲከፍት ሰይጣን ነው፡፡ ሰይጣንም " ይቅርታ የአንተ ቤት መሆኑን አላወቅሁም
" ብሎ ሄደ፡፡ ከዚያን ቀን ጀምሮ መንኳኳት ቆመ፡፡
😇😇😇😇😇😇😇😇😇😇
ሁሉንም የሕይወታችንን ክፍል ለጌታ እግዚአብሔር ካላስረከብነው ሰይጣን ማንኳኳት አያቆምም፡፡ 1ዐ% ስንሰጥ
ይንኳኳል፡፡ 30% ስንሰጥ ይንኳኳል፡፡ 50% ስንሰጥ ይንኳኳል፡፡ 99% ስንሰጥ ይበልጥ ይንኳኳል፡፡ 100% ስንሰጥ መንኳኳት ይቆማል፡፡ እኛ ከከፈትን ሰይጣን ይገዳደረናል፡፡ ጌታ ሲከፍት ሰይጣን " ይቅርታ የአንተ
ቤት መሆኑን አላወቅሁም " ብሎ ይሄዳል፡፡ ጌታ ሰማይን የደስታ አገር ያደረጋት ሙሉ በሙሉ የፈጣሪ ፈቃድ የጸናባት በመሆኗ ነው፡፡ በእኛም ሕይወት የሰማይ ደስታ የሚመጣው የፈጣሪ ፈቃድ በሕይወታችን ሙሉ በሙሉ
ሲፈጸም ነው፡፡ ስለዚህ፡-
ፈጣሪን እረኛችን እናድርገው፡፡
በፍጹም ልባችን እንከተለው፡፡
የሚያስፈልጉን ነገሮችም እኛን ይከተሉናል፡፡

🌻ሙሉ ሕይወታችንን ለእግዚአብሔር እንድናስረክብ ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን አሜን🌻
🙏🙏🙏አሜን🙏🙏🙏
🙏🙏🙏
ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Vensi @Vensi @Vensi
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯

ቬኒሲያ

25 Dec, 11:07


ስደተኞቹ ክፍል 8
“እሺ” አለች ትንፋሽ በተቀላቀለበት ድምጽ፡፡ አዛዡ ቤቱ ሳይገባ ቅናት ገብቶ ጠበቀው፡፡ ሚስቱ እሳት ልሳ እሳት ጎርሳለች፡፡ የአዣዡ ሚስት “ባልሽ ውብ ልጃገረድ ይዞ መጥቶልሻል እንግዲህ አንቺ የጓዳዋ እመቤት መሆንሽ ነው” እያሉ ጎረቤቶቿ ሁሉ በአሽሙር ሲነግሯት ነበር፡፡ ቅናትዋን መቻል አቅቷትገና ሳይመጣ ቤቱን ማተራመስ የጀመረችው፡፡ የዚያች ውብ ልጃገረድ ጉዳይ አልጣማትም፡፡ ግቢውን እየበጠበጠች በሩን እያላጋች አሽከሮቿ እያንቆራጠጠች ባሏን ጠበቀችው፡፡

ወደ ቤት ሲገቡ በግልምጫ አንስታ አፍረጠረጠቻቸው፡፡ ዓይን በመሆኑ አልተጎዱም፡፡ ሄለን ግን ደንጣለች፡፡ “ብቻ እንኳ ቤቴ መጣሽ ልክሽን እሰጥሻለሁ” ከቅናትዋ ማየል የተነሳ የምታደርገውን አታውቀውም “ወይ አንቺ ወይ እኔ እንኖራታለን” በልብዋ እየዛተች ቀድማቸው ገባች፡፡ አዛዡ ሔለንን ዝቅ ብሎ ተመለከታት ንዴትዋ ከፊቷ ላይ ይነበባል፡፡ ከወደ ጓዳ ሚስቱ እቃውን ስትገለባብጠው ይሰማል፡፡

የሄለን ወደዚህች ከተማ መምጣት ብዙ ነገሮችን ቀያይሯል፡፡ የከተማ ሕዝብ የዕለት ተዕለት የጨዋታው አፍ መፍቻ የጦር አዛዡ ቆርኔሌዎስ ያቺን ነዝናዛና ቀናተኛ ሚስቱን አባሮ ይህቺን ለጋና ውብ ልጃገረድ ያገባ ይሆን? የሚለው ጥያቄ ሆኗል፡፡ አብዛኛው በነገሩ ሲስማና ሚስቱን በጠባይዋ እያናናቀ ሲፈርድባት አንዳንዱ ግን በዝምታ አልፎ አልፎም በተቃውሞው አምባ ይሰለፍ ነበር፡፡

አኒባል የተባለው የንጉሥ አማካሪ ሄለን ያቺን ከረገጠችበት ዕለት ጀምሮ በልቡ ለቆርኔሌዎስ የነበረው ጥላቻ ብሶበታል፡፡ ይሁን እንጂ አጅሬ ፊት ለፊት አይቃወምም፡፡ እንዲያውም ከሕዝቡ በላይ በአፉ ለሄለንና ለቆርኔሌዎስ ተሟጋች ሆኗ፡፡ ልቡ ግን አንገቱን ደብቆ መርዝ እንዳዘገጀ እባብ የመንደፊያውን ጊዜ ይጠብቃል፡፡

አኒባል አስቀድሞም ቢሆን ቆርኔሌዎስን አይወደውም፡፡ጠባዩ በቅናት የተመረዘ ነው፡፡ ነገር ግን ችምችም ያሉት ጥርሶቹና አባባይ አይኖቹ ከመልካም ፈገግታ ጋር ሲዋሐዱ በልቡ ያለውን ተንኮል ለጊዜው ስለሚጋርዱለት ጨዋና ደግ ሰው ተደርጎ ይነገርለታል፡፡የአኒባል የእባብነት ተፈጥሮ የሚያውት አብረውት የኖሩት አብረውት የሠሩት አልያም ደግሞ በመርዙ ተነድፈው የቁም ሞት የሞቱት ብቻ ነው፡፡ ሊነድፈው የሚፈልገውን ሰው ከሌላው ጊዜ በተለየ ከሁሉም ሰው በበለጠ ይቀርበዋል፡፡ ደግነት ያበዛበታል፡፡ ቤተኛ ይሆነዋል፡፡ የንጉሥ አማካሪ ነውና ባለው ተሰሚነት ተጠቅሞ ዝናውን ይናኝለታል፡፡ ከዚያ እንዳይነሳ አድርጎ በቁሙ ይገለዋል፡፡

ዛሬም ያ ጠባዩ ሥራውን ጀምሯል፡፡ ቆርኔሌዎስን ባገኘው ቁጥር ከወገቡ ጎንበስ እያለ ሰላምታ ይሰጠዋል፡፡ በከተማው የሚራውን ወሬ ያስለቃቅምና “እንዲህ ተብለህ ነበር፤ እኔ ያንተ ወንድም እንዲህ አድርጌ መለስኩልህ” ማለት የዘወትር ግብዣው አድርጓታል፡፡ ቆርኔሌዎስ አኒባልን በነገረ ሥራው ባይወደውም ሕይወቱ ግን ያሳዝነው ነበር፡፡ ኑሮው የተዘበራረቀ ነው፡፡ በቤተመንግስቱ አካባቢ ወጣ ገባ በሚሉ ሴቶች ይታማል፡፡አባቱ ለሀገራቸው ታላቅ ተግባር የፈጸሙ ጀግና ስለነበሩ ንጉሡ የአባቱን ውለታ ለመክፈል ሥልጣናቸውን ያውርሱት እንጂ ኃላፊነቱን መሸከም እንዳልቻለ በውሽክሽክ ሥራው ስለሚያውቁ ይበሳጩበታል፡፡ ኮስታራና ቆፍጣና ሰው እንጂ ሳቂታና ፌዘኛን የማያቀርቡት ንጉሥ “አንተ ሰው ብትፈልግ አቴና ሂድ እዚያ ነው የሳቅ አምባ አለ የሚባለው” እያሉ ደጋግመው ዘልፈውታል፡፡ ግን አልጨከኑበትም፡፡

ቆርኔሌዎስ ይህንን የአኒባልን ጠባይ ስለሚያው በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ምክሩን ሳይለግሰው አያልፍም፡፡እናም ያሳዝነዋል፡፡ በተለይ ሰሞኑ፡፡ አኒባል በጣም እየቀረበው ስለሄደ ቆርኔሌውስ ያንን አስቀያሚ ጠባዩን እየተወው የመጣ መስሎት እርሱም ይበልጡኑ ቀረበው፡፡ አንድ ቀን ንጉሡ እየተመረሩበት መሆኑን ገልጦ እንደሚፈልጉት ዓይነት ሰው እንዲሆንላቸው እየመከረው ወደ ቤት ወሰደው፡፡ ያን ቀን ነበር ከሄለን ጋር የተዋወቀው፡፡

ለአኒባል ያቺ ቀን በቆርኔሌዎስ ዘንድ ቤተኛ እንዲሆን በር ከፍታ ብቻ አልቀረችም፡፡ ለሄለን ያለውንም ሥጋዊ ፍቅር የበለጠ በልቡ እንዲሰርጽበትም አድርጋለች፡፡ በበዓል ቀን እንደ ሀገሩ ባሕል መሠረት መኳንንቱ ሲጠያይቁ ይውላሉ፡፡ ከዚያች ቀን በፊት አኒባል የቆርኔሌዎስን ቤት የሚያውቃት እንዲህ ባለው አጋጣሚ ብቻ ነበር፡፡ ዛሬ ግን በቀን አንዴ ብቅ ማለቱ አይቀርም፡፡

አኒባል ቤቱን እየተላመደ ሲመጣ እባብነቱም ከተቀበረበት ብቅ ማለት ጀመረ፡፡ ቤቱ ውስጥ የቀመመውን መርዝ አምጥቶ በቆርኔሌዎስ ቤት አሳቻ ቦታ አስቀምጦታል፡፡ ይህንን አደገኛ መርዝ ለቆርኔሌዎስ አግቶ ዘመድ አልባ የሆነችውን ሄለንን ለመቅለብ፡፡ አኒባል ከተዋወቃት ጊዜ ጀምሮ ሄለን ከቆርኔሌዎስ ቀጥሎ የቀረባት ሰው እርሱ መሆኑን አምና ተቀብላለች፡፡ ስለዚህ ቆርኔሌዎስ ከሞተ ሄለን የት ታመልጠዋለች፡፡

ይቀጥላል፡፡

ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Vensi @Vensi @Vensi
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯

ቬኒሲያ

23 Dec, 18:12


ውድ ታዳሚዎቻችን ስደተኞቹን እየተከታተላችሁ ነው? ምን ይጨመር ምን ይቀነስ?

ቬኒሲያ

23 Dec, 08:36


ስደተኞቹ ክፍል 7


በክርስትና ጉዞ ሁልጊዜ ያሰብነው ብቻ አይገጥመንም ያልታሰበና ያልተጠበቀ ነገርም ይከሰታል፡፡ ያ ማለት እኛ ያላሰብነው እንጂ እግዚብሔር ያላሰበው ማለት አይደለም፡፡ እኛ የማናውቀው እንጂ እግዚአብሔር የማያውቀው ማለት አይደለም፡፡ አባታችን መንገድ ሲያስጀምረን ላያስፈጽመን አይደለም፡፡

ልክ አጠገብዋ ሆኖ የሚመክራት ያህል ይሰማታል፡፡ በተለይም በዚያች የመገንጠያ መንገድ ላይ ሲለያት፡፡ “እመቤቴ ካንቺ ጋር ናት” ያላት ድምጹ በአካባቢዋ የሞላና ከየማዕዘናት ሁሉ እየወጣ ናት-ናት-ናት የሚል ይመስላት ነበር፡፡ አዛዡ ከተጓዘበት የሃሳብ ጎዳና መለስ ያለው ሄለን በኅሊናዋ የሚያስተጋባውን ድምጽ እርስዋ ተቀብላ “ናት” ብላ በደገመችው ጊዜ ነበር፡፡
“የምሥራቅ መንገደኞች” አዛዡ የማርቆስ መልክ ትውስ አለው፡፡ “ለምን አልጠይቃትም” አንድ የተጠራጠረው ነገር ነበር፡፡ ከራሱ ሕይወት አንጻር፡፡
“ምንድን ነበር ያልሽው?” አላት ዘወር ብሎ፡፡ ሄለን ትኩር ብላ እያየቸው “እመቤቴ ከኔ ጋር ናት” አለችው ድፍረቷ ለእራስዎ አስገርሟታል፡፡ ፈገግ አለ፡፡ ሰውነቱ በደስታ ተሞላ፡፡ እጁን ወደ ብብቱ ሰደደና መልሶ አወጣ፡፡ ከዚያ በቀኝ እጁ አንድ ነገር አሳያት የእመቤታችንን ሥዕል፡፡
ሄለን ምን እንደምታይ ግራ ገባት፡፡ አልጠበቀችም፡፡ አላሳበችም፡፡ አልገመተችም፡፡ “እመቤቴ” ብላ ጮኻ እንዴት እንደነጠቀችው ሳታውቅ ዘግይታ ሥዕሉን ከደረትዋ ላይ፣ ከሥዕሉ ላይ ደግሞ ዕንባዋን አገኘችው፡፡ ይህን ሥዕል ቅዱስ ሉቃስ ከሳለውና በኢየሩሳሌም የዴር ሱልጣን ገዳም ከሚገኘው ሥዕል ቀድሮ ሥሎ ያመጣለት አንድ የቀሬና ሰው ነበር፡፡ ሥዕሏን ከተቀበለ ጊዜ ጀምሮ ከደረቱ ኪስ ለይቷት አያውቅም፡፡ ጥንት እንዲህ በኪሱ የሚይዘው የደራጎንን ምሥል ነበር፡፡ ይህ በሰሜን አፍሪካ ወታደሮች የተለመደ ነው፡፡ ድል ያስገኛል ይባላል፡፡
ቀና ብላ ወደ ኋላዋ ዞረች “ማርቆስ እመቤታችን አልተለየችኝም” አለችው ልክ ይሰማት ይመስል፡፡
“ክርስቲያን ነህ?” ሄለን ጠየቀችው
“አዎ”
“የወታደር ክርስቲያን አለ እንዴ?”
“አለ የእኔ እህት! ክርስቲያን የሆንኩት የዛሬ ሦስት ዓመት ነው፡፡ የሃገሬ ሰዎች ግን እጅግ ጣዖት አምላክያን ናቸው ስለዚህ ክርስትናየን ለማንም መግለጥ አልቻልኩም፡፡ አንገቱን ደፍቶ ትክዝ ብሎ ቆየና “ያለሰማዕትነት እኮ ክርስቲያን መሆን ያስቸግራል፡፡ ከክርስትና የምንፈልገውን ለማግኘት ከዓለም የምንወደውን ማጣት አለብን፡፡
“እንዴት?” ንግግሩ አልገባትም
“ባለትዳር ነኝ የአንድ ልጅ አባት፡፡ ቤቴን ለማን ልተወው? ልጄንስ? ይጨንቀኛል፡፡ ስለዚህ ለብቻዬ እጸልያለሁ፡፡ ተደብቄ የምችለውን ሁሉ እንደ እግዚአብሔር ቃል እፈጽማለሁ፡፡
“የእኔ ክርስቲያን መሆን በሀገሬ ቢታወቅ መከራዬ ይበዛል፡፡ ልጄና ባለቤቴ ይሰቃያሉ ይህን ፈራሁና ተደበቅሁ፡፡ አሁን ግን አንቺን አገኘሁ፡፡
መንገዱ ለሁለቱም የደስታ ሆነላቸው፡፡ እጅግ ብዙ ተማማሩ፡፡ የሄለንን ታሪክ አዛዡን የራሱን ሂወት እንዲመረምር አደረገው፡፡ እውነተኛ ክርስቲያን ሲገኝ የተደበቀ ክርስቲያን ራሱን ቆፍሮ ማውጣት ይጀምራል፡፡
ንጉሡና ጋሻ ጃግሬዎቹ ከከተማ በር ነበር ሠራዊቱን የተቀበሉት፡፡በሠረገላው ውስጥ የተቀመጠችው ውብ ልጃገረድ ግን የሁሉንም ቀልብ ሳበችው ፡፡ ማናት እዛዡ ለንጉሡ የክብር ሰላምታ ሰጠ፡፡ የጉዞን የውጊያውን ውሎ በአጭር አቀረበ የወርቅ የራስ ቁር ከንጉሥ ተበረከተለትና ጉዞ ወደ ቤተመንግሥት፡፡
“የማናት ውብ ልጃገረድ?” ንጉሡ በአድናቆት ጠየቀ፡፡ አዛዡ ታሪክዋን ዘርዝሮ ተናገረ፡፡
“አማልክት የሰጡህ ውብ ሥጦታ ናት?” ንጉሡ ሳቅ ሲሉ አዛዡም ፈገግ አለ፡፡ “ከዚያች ገልጃጃ ሚስትህ ተላቀቅክ” የአዛዡ ሚስት ረዥም ሞልቃቃና ቀናተኛ መሆንዋን ንጉሡ አበጥረው ያውቃሉ፡፡ አዛዡ ግን የክርስትና ነገር ሆኖበት እግዚአብሔርን አክብሮና ፈርቶ ይዟታል፡፡
“አይዞሽ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነው፡፡ ከእኔ ጋር ሰንብተሽ እልክሻለሁ፡፡ ወንድምሽም አይቀርም ይመጣል፡፡” ከቤተመንግስቱ ሲወጡ አዛዡ ልክ እንደ ሕጻን ልጅ ጸጉሯን እየዳሰሰ ይመክራት ነበር፡፡ ወንድሟ ትዝ አላት እርሱ ነበር እንዲህ ጸጉሯን የሚዳስሳት፡፡

ይቀጥላል፡፡

ቬኒሲያ 💖:
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@Vensi @Vensi @Vensi
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯