Ministry Of Education Ethiopia (@minstery_of_education) Kanalının Son Gönderileri

Ministry Of Education Ethiopia Telegram Gönderileri

Ministry Of Education Ethiopia
For more info Web :- moe.gov.et
To contact us Mail :- [email protected]
+251 11 156 5529
We are promoting Educational Achievements
2,340 Abone
82 Fotoğraf
28 Video
Son Güncelleme 10.03.2025 18:45

Benzer Kanallar

E.Z መረጃ
8,265 Abone
Grade 12 books
6,110 Abone

Ministry Of Education Ethiopia tarafından Telegram'da paylaşılan en son içerikler

Ministry Of Education Ethiopia

09 Sep, 08:47

3,250

የ12 ተኛ ክፍል ውጤት ዛሬ ማታ በ https://eaes.edu.et/ reals ይደረጋል

ለመላው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኞች መልካም እድል
Ministry Of Education Ethiopia

08 Sep, 18:43

3,500

ነገ መጨረሻ ሳይሆን አዲስ ጅምር ነው። መጪው ጊዜ ምንም ቢሆን ብሩህ ነው። ነገን በተስፋ፣ በእምነት እና በጽናት እንጠብቅ - ሁል ጊዜ ወደፊት ብዙ መንገዶች አሉ እና የልጆቻችን አቅም ገደብ የለሽ ነው። በተነገረን መንገድ ብቻ አይደለም። እዚህ ስንደርስ በራሳችን መንገድ ነው የተጓዝነው እንጂ የቤተሰባችን መንገድ አይደለም። ስኬት ለልጆቻችን ከምንጠብቀው ይልቅ ልናደርገው የምንችለው ነገር ነው። በሚችሉት ከጎናቸው እንቆማለን። ተስፋ አንቆርጥም.



ለነገ መልካሙን ሁሉ እመኛለሁ! ”
Ministry Of Education Ethiopia

08 Sep, 18:30

3,436

የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ነገ ይለቀቃል እስከዚያ ድረስ ቻናሉን ሼር ማድረግ አይርሱ
Ministry Of Education Ethiopia

07 Sep, 02:52

3,473

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሰኞ ይፋ ይደረጋል።

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ሰኞ ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ/ም እንደሚገለጽ አሳውቋል።

የዘንድሮው ብሔራዊ ፈተና በቅይጥ ማለትም በወረቀት እና በኦንላይን መሰጠቱ ይታወሳል።
Ministry Of Education Ethiopia

01 Sep, 10:42

3,835

#12_ክፍል

ከ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ጋር በተያያዘ አሁን ያለው ሂደት ከመገናኛ ብዙሀን ከትምህርት ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ገለጻ ተደርጓል።

ከቢሮው የተገኘ የመገናኛ ብዙሃን ምንጭ እንደገለጸው "ባለፉት ዜናዎች በቲክ ቶክ, ቴሌግራም እና ፌስቡክ ላይ ያለውን ግራ መጋባት እናያለን.

የፈተና ዉጤቱ የሚገለፅበትን ቀን በተመለከተ እስካሁን የፈተና ውጤቶችን ማረጋገጥ አለመጠናቀቁን ምንጫችን ገልጿል።

"እንደሚታወቀው በዚህ አመት ፈተናው በኦንላይን እና በወረቀት የተሰጠ ሲሆን ሁሉም ፈተናዎች ኦንላይን መሆን የሚችሉበት ሁኔታ ሲመቻች ውጤቱን ለማስታወቅ ጥቂት ቀናት ይወስዳል" ብሏል።
Ministry Of Education Ethiopia

28 Aug, 10:53

3,862

በ2017 የትምህርት ዘመን የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላቸሁና በተለያዩ ምክንያቶች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች እስከ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ድረሰ በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

አመልካቾች በየተመደባችሁበት የፈተና ማዕከላት እና የመፈተኛ ፕሮግራም መሰረት ከነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናው የሚሰጥ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ለፈተና ወደ ማዕከላት ስትሔዱ የተሰጣችሁን User Name and Password እንዲሁም ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይጠበቃባችኋል።
Ministry Of Education Ethiopia

26 Aug, 18:45

2,833

#Grade_12

የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤትን አስመልክቶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚተላለፉ የውሸት ዜናዎች ተማሪዎች እና ቤተሰቦቻቸው ግራ ሲጋቡ ሚዲያዎቻችን አይተዋል።

የኛ ሚዲያዎች ከፈተና ውጤቱ ጋር ተያይዞ ለብዙ አመታት ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ፣ አላስፈላጊ ውዥንብርን እንድታስወግዱ እና መልካም ጊዜ እንዲያሳልፉ አሳስባለሁ።

ትክክለኛ መረጃ እንደደረሰን እናሳውቆታለን!

=========================

Our media has seen that students and their families are being confused by the spread of false news on various social media regarding the results of the grade 12 examination.

As our media has been doing for many years in connection with the examination results, I urge you to avoid unnecessary confusion and have a good time.

We will keep you informed as soon as we receive actual information!
Ministry Of Education Ethiopia

26 Aug, 00:34

2,556

የትምህርት ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
----------------------------------------
በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አስቀምጠዋል።

በኦሮሚያ ክልል በሱሉልታ ወረዳ ዋሬርሶ ማሌማ ቀበሌ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አሻራቸውን ያኖሩት የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አረንጓዴ አሻራችንን በማኖር አርአያነታችንንና ቁርጠኝነታችንን ለትውልድ በተግባር ማሳየት ይገባናል ብለዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒሰትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በጉጉት ስንጠብቀው ለነበረው ለዚህ ቀን ደርሰው አረንጓዴ አሻራቸውን በማስቀመጣቸው ደስ ያላቸው መሆኑን ገልጸው ሀገራችን ለዓለም አስተዋጽኦ ያደረገችበት መርሃ-ግብር መሆኑን ተናግረዋል።

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች ችግኞቹን የተከሉት በተራቆተ ቦታ በመሆኑ ከአቻ መስሪያ ቤቶች ጋር በመተባበርም የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራ እና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የግድ መሆኑን ተናግረዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች አገር ለትውልድ ለማውረስ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ኃላፊነታችንን ልንወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በኦሮሚያ ክልል በሱሉልታ አካባቢ በተካሄደው አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሀ ግብር የትምህርት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡