Latest Posts from Ministry Of Education Ethiopia (@minstery_of_education) on Telegram

Ministry Of Education Ethiopia Telegram Posts

Ministry Of Education Ethiopia
For more info Web :- moe.gov.et
To contact us Mail :- [email protected]
+251 11 156 5529
We are promoting Educational Achievements
2,340 Subscribers
82 Photos
28 Videos
Last Updated 10.03.2025 18:45

The latest content shared by Ministry Of Education Ethiopia on Telegram

Ministry Of Education Ethiopia

18 Nov, 09:04

733

የትምህርት ቤቶች ስፖርት ሊግ ተጀመረ።
____________ // ______________
(ህዳር 09/2017 ዓ.ም) ትምህርት ሚኒስቴር ከሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የትምህርት ቢሮዎች ጋር በመተባበር የትምህርት ቤቶች ስፖርት ሊግን አስጀምሯል።
ተማሪዎች መደበኛ የትምህርት ጊዜያቸውን ሳይጎዱ በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የስፖርት ሊግ መርሃ ግብሩ ተዘጋጅቶ ወደተግባር ገብቷል። የተማሪዎች ከመደበኛ ትምህርትቸው ጎን ለጎን በተለያዩ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች መሳተፍ የተማሪዎችን አካላዊ፣ ማህበራዊ፣ ስነ ልቦናዊ ጠቀሜታው የጎላ ነው።
ከዚህ አኳያም በ2017 የትምህርት ዘመን በምስራቅ ቀጣና የተደራጀው የሀረሪ ክልል በሁሉም ትምህርት ቤቶች በቮሊቦል፣ በእግር ኳስ፣ በቅርጫት ኳስ፣ በእጅ ኳስ፣ በአትሌትክስ፣ በጂምናስቲክስ፣ በጠረዼዛ ኳስ እና በባህላዊ ስፖርት አይነቶች የክልሉ አመራሮች ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና የትምህርት ቤት አመራሮች በተገኙበት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በድምቀትተከፍቷል።
ስፖርታዊ ውድድሩ አመቱን ሙሉ የሚቀጥል ሲሆን ከሀረሪ ክልል በተጨማሪም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት የማስጀመሪያ መድረክ ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡

በሌሎች የሀገራችን ክፍሎች ደግሞ በደቡብ ቀጣና ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞንና በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በቮሊቦልና በእግር ኳስ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በጉጂ ዞን የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በእግር ኳስ ፣ በቮሊቦል እና በአትሌትክስ ስፖርት በደመቀ ሁኔታ ተጀምሯል፡፡

በሌሎች የቀጣና አደረጃጀቶች ስር የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ስፖርታዊ ውድድሮቹን በቅርቡ የሚያስጀምሩ ይሆናል።
Ministry Of Education Ethiopia

24 Oct, 19:15

3,034

የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆኗል።

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው ፕሮግራም ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታችሁን ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ሆኗል።

ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ምደባችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፦

በድረ-ገፅ 👇
https://placement.ethernet.edu.et

በቴሌግራም 👇
https://t.me/moestudentbot

የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
Ministry Of Education Ethiopia

24 Oct, 19:12

2,654

https://placement.ethernet.edu.et
https://t.me/moestudentbot
Ministry Of Education Ethiopia

10 Sep, 17:31

5,337

Ethiopian Secondary School Leaving Certificate Examination (ESSLCE)
--------------------------------
YONAS NUGUSE GEBREMARIAM
Admission No: 5667384
Gender: M
Stream: Natural Sc.
School: QELAMINO PRE.
--------------------------------
・ Chemistry: 96
・ English: 95
・ Physics: 97
・ Biology: 98
・ Mathematics: 100
・ Scholastic Aptitude Test: 91
・ Civics & Ethical Edu.: 98
---------------------------------
Your total score is 675
Ministry Of Education Ethiopia

10 Sep, 17:31

4,549

YONAS NUGUSE GEBREMARIAM
Ministry Of Education Ethiopia

10 Sep, 16:21

4,144

Ethiopian Secondary School Leaving Certificate Examination (ESSLCE)
--------------------------------
ABDI HUSSEIN HEBO
Admission No: 3765376
Gender: M
Stream: Social Sc.
School: ABDI BORU
--------------------------------
・ Mathematics: 78
・ English: 78
・ Geography: 90
・ Scholastic Aptitude Test: 73
・ History: 94
・ Economics: 88
---------------------------------
Your total score is 501
Ministry Of Education Ethiopia

10 Sep, 16:21

4,082

ABDI HUSSEIN HEBO
Ministry Of Education Ethiopia

09 Sep, 16:39

4,230

የ12ኛ ክፍል ውጤትዎን ይመልከቱ!

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ከዛሬ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ለሊት 6:00 ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ መገለፁ ይታወቃል።

በሚከተሉት አማራጮች ውጤታችሁን ተመልከቱ፦

► በፖርታል 👉 https://result.eaes.et

► በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284

► በቴሌግራም ቦት 👉 https://t.me/EAESbot

ከውጤት መግለጫ ፖርታል እና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማተም እንደምትችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ተፈታኞች በውጤት እና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቅሬታ ካላቸው ወደ አገልግሎቱ ቢሮ በአካል መሔድ ሳያስፈልጋችሁ ከSMS በስተቀር በውጤት መግለጫ አማራጮቹ ላይ Compliant የሚለውን በመጫን የቅሬታቸውን ዓይነት በተዘጋጀ የቅሬታ ፎርም ላይ በትክክል በመሙላት ማቅረብ ትችላላችሁ።

አገልግሎቱ በቅሬታችሁ ላይ ምላሽ ቅሬታቸውን ባቀረቡበት ተመሳሳይ አድራሻ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጿል።

@Minstery_of_education
Ministry Of Education Ethiopia

09 Sep, 14:02

3,623

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና 5.4 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገባቸው ተገለጸ።
-------------------------------------------------
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሚኒስትሩ እንደገለጹት ለአገር አቀፍ ፈተና ከተቀመጡ 674,823 ተማሪዎች ውስጥ 36, 409 ወይም 5.4 በመቶ የማለፊያው ውጤት ማግኘታቸውን ገልጸዋል። የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ በ9,114 ተማሪዎች ብልጫ እንዳለውም ተናግረዋል።

በዚህም በተፈጥሮ ሳይንስ 28,158 ወይም 9 በመቶ በማህበራዊ ሳይንስ 8,251 ወይም 2 በመቶ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን አመላክተዋል።

በፈተናው 1,221 ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን የገለጹ ሲሆን በባለፈው ዓመት ከተመዘገበው 220 አንጻር የተሻለ ውጤት መሆኑም ተገልጿል። ቀደም ሲል በነበረው የመሰናዶ ትምህርት በትግራይ ክልል ፈተናቸውን ከወሰዱ ተፈታኞች መካከል ከ700 በተፈጥሮ ሳይንስ ከትግራይ ቀላሚኖ ት/ቤት አንድ ተማሪ 675 ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ በዚህ ዓመት ፈተናቸውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ከ600 በተፈጥሮ ሳይንስ ከአዲስ አበባ አግዚሊየም ካቴድራል ት/ቤት 575 (በሴት ተማሪ) በማህበራዊ ሳይንስ ከአዲስ አበባ ኢትዮ ፓረንትስ 538 (በሴት ተማሪ) ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል ።

በዚህ ዓመት ሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ከአምናው በተሻለ ተማሪዎችን ማሳለፋቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ 1,363 ት/ቤቶች ግን ምንም ተማሪ አለማሳለፋቸውን ጠቁመዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ በመጨረሻም 50 በመቶና በላይ ያመጡት በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገቡ ጠቅሰው የተወሰኑ ተማሪዎችም በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
Ministry Of Education Ethiopia

09 Sep, 11:28

3,274

የ12 ተኛ ክፍል ውጤት ዛሬ ማታ ለሊት 6 ሰዓት ላይ ይፋ ይደረጋል