Latest Posts from ለትውልድ | LETIWULID 🦋 (@letiwulid) on Telegram

ለትውልድ | LETIWULID 🦋 Telegram Posts

ለትውልድ | LETIWULID 🦋
🔰ንቃት ለትውልድ🔰
ቤተሰብ ይሁኑ! 🙏
1,909 Subscribers
64 Photos
4 Videos
Last Updated 01.03.2025 16:30

The latest content shared by ለትውልድ | LETIWULID 🦋 on Telegram


ማንንም አይጠብቅም!
:
እርሱ ፍተሃዊ ዳኛ ነው። ለጥቂቶች አዳልቶ የሚዘገይ፣ በጥቂቶችም ጨክኖ የሚፈጥን አይደለም። ጊዜ ሳያዳላ ይፈርዳል። በአግባቡ የተጠቀመውን ይሸልማል፣ እንዲሁ በዋዛ ፈዛዛ ያሳለፈውንም በሚገባ ይቀጣል። በጊዜ አለንጋ ከመገረፍ ራሳችሁን ጠብቁ። ሳቁ፣ ተጫወቱ፣ አሹፉ፣ ቀልዱ ነገር ግን በፍፁም በውድ ጊዜያችሁ አታሹፉ፣ በፍፁም ትልቁን ስጦታችሁን አታዋርዱት። ራሳቸውን የገዙ፣ ስሜታቸውን የተቆጣጠሩ፣ ስራቸውን በአግባቡ የሰሩ፣ ሁሌም ከዛሬያቸው የሚያተርፉ ሰዎች ጊዜ ጌታ ያደርጋቸዋል፣ ክብር ላይ ክብርን ፀጋ ላይም ፀጋን ይጨምርላቸዋል። በምትኩ በህይወታቸው ያረፈዱትን፣ ጊዜያቸውን በስንፍና የጨረሱትን፣ ሲበዛ ግዴለሽና ደንታቢስ ይሆኑትን፣ አቅማቸውን በዋዛፈዛዛ ያባከኑትን የስራቸውን ይከፍላቸዋል፣ ባይፈልጉትም በግድ ይቀጣቸዋል፣ እንደተጫወቱበት በተራው ይጫወትባቸዋል፣ አንገት ያስደፋቸዋል፣ አሸማቆ ወደ ኋላ ያስቀራቸዋል።

ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@mikre_aimro

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid

ቁሳዊ ስኬት
:
ግብህ
ቁሳዊ ስኬት አይደለም፤ ጥቅም አልባ ዝና አይደለም፤ ለማህበረሰቡ የማይጠቅም፣ አገልግሎት የሌለው ንብረት አይደለም። የፈለከውን ገንዘብ ማግኘትህ ስኬታማ አያደርግህም፤ የፈለከውን ገንዘብ አለማግኘትህም ስኬት አልባ አያደርግህም። ሳይኖርህ ለሰው መኖር፣ ለሰዎች መትረፍ ትችላለህ። በተቃራኒው እያለህ ከእራስህ በላይ ላትኖር ትችላለህ። ያለውንና የሌለውን የሚለየው አንደኛው የስኬት መለኪያ ለሰዎች መኖር፣ ሌሎችን መርዳት፣ ለወገን መድረስ መቻል ነው። መኖርህ፣ ንብረት ማፍራትህ፣ ሃብት ማካበትህ ለውጥ እንድታመጣ ካላደረገህ ምንም ትርጉም የለውም። ቁስ ቢበዛ ነገ ወይ እርሱ ይጠፋል ወይም አንተ ጥለሀው ትሔዳለህ።
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@mikreaimro

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid

THE SCIENCE OF GETTING RICH
ወይም የሀብት ሳይንስ በሚል የተተረጎመው መጽሐፍ 5 አንኳር ሀሳቦች፦

1. ሳይንሱን ካወቅክ ሀብታም መሆን ትችላለህ

ሀብታም የመሆን ሳይንስ አለ፤ እሱም እንደ አልጄብራ ወይም የሂሳብ ዓይነት ትክክለኛ ሳይንስ ነው። ሀብትን የማግኘት ሂደትን የሚቆጣጠሩ አንዳንድ ህጎች አሉ፤ እና ማንኛውም ሰው እነዚህን ህጎች  ከተማረና ለህጎቹ ከታዘዘ፣ ያ ሰው በእርግጠኝነት ሀብታም ይሆናል።

2. ለየት ባለ መንገድ መስራት አለብህ

ሀብታም የሆኑ ሰዎችን ስናጠና ከሌሎች ሰዎች የበለጠ ችሎታ ወይም ተሰጥኦ የሌላቸው በሁሉም ረገድ አማካኝ ሆነው እናገኛቸዋለን። ይህም እነዚህ ሰዎች ሀብታም የሆኑት ሌሎች ሰዎች የሌላቸው ተሰጥኦና ችሎታ ስላላቸው ሳይሆን፣ ነገሮችን በሆነ ለየት ባለ መንገድ በመስራታቸው እንደሆነ ያሳየናል።

3. ካፒታል የለኝም አትበል ችግሩ ካፒታል አይደለም

የመነሻ ካፒታል ማጣት ማንንም ሀብታም ከመሆን አያግድም፤  መነሻ ካፒታል ሲኖርህ ግን ለማደግ ይበልጥ ቀላል እና ፈጣን ይሆንልሃል፤ ነገር ግን መነሻ ካፒታል ያለው ሰው ቀድሞውኑ ሀብታም ስለሆነ እንዴት ሀብታም መሆን እንዳለበት ማሰብ አያስፈልገውም።  ነገር ግን ምንም ያህል ድሃ ብትሆን ነገሮችን በሆነ መንገድ መሥራት ከጀመርክ ሀብታምና ካፒታል ያለህ መሆን ትጀምራለህ።

4. አሁንም እድሎች አሉ

ማእበሉን በመታገል ፈንታ ከማእበሉ ጋር አብሮ ለሚሄድ ሰው ብዙ እድሎች አሉ፡፡ ስለሆነም የፋብሪካ ሰራተኞች እንደ ግለሰብም፣ እንደ ቡድንም እድልን አልተነፈጉም፡፡ ሰራተኞች በቀጣሪዎቻቸው በዝቅተኛ ደረጃ ሆነው እንዲቀሩ ሊደረጉ አይችሉም፡፡ እንደ መደብ አሁን ያሉበትን ደረጃ ሊይዙ የቻሉት ነገሮችን በተወሰነ መንገድ ስለማያደርጉ ብቻ ነው፡፡

5. የተትረፈረፈ ሀብት አሁንም አለ

ማንም ሰው በድህነት ውስጥ የሚኖረው ያለው የሀብት አቅርቦት የተወሰነ ስለሆነ አይደለም፡፡ ለሁሉም ከሚበቃው በላይ የሀብት አቅርቦት አለ፡፡ አንዲት ሀገር በከፍተኛ የእርሻ ልማት የምታመርተው ጥጥ፣ ሱፍ፣ ሀር እና በፍታ እያንዳንዱን የዓለም ህዝብ ሰሎሞን ከክብሩ ጋር ከለበሰው ይልቅ እንዲለብስ የሚያስችል ነው፡፡ ሁሉንም በቅንጦት መመገብም ያስችላል፡፡


#የሀብት_ሳይንስ_መጽሐፍ
https://t.me/Elodia_G

እራሳችሁን አስቀድሙ!

መጀመሪያ እራሳችሁን አድኑ፣ አስቀድማችሁ በደህንነታችሁ እርግጠኛ ሁኑ፣ ባላችሁበት  ሁኔታ ሰላም ይሰማችሁ። ትናንታችሁ ጠባሳ የጣለባችሁ ሳያንስ ዛሬም እናንተው በፍቃዳችሁ ተጨማሪ ጠባሳ እራሳችሁ ላይ አትጣሉ። ከህመማችሁ ለመንፃት መተው ያለባችሁን ነገር ተዉ፤ ስለወደፊት ህይወታችሁ የሚገዳችሁ ከሆነ እስራታችሁን ፍቱ፣ በእርግጥም ህይወትን በሙላት መኖር ካሻችሁ የይቅርታ ልብ ይኑራችሁ። ሸክማችሁን አራግፉ፣ ለደህንነታችሁ ዋስተና አስቀምጡ፣ በምርጫችሁ ወደፊትን ተመልከቱ፣ ኋላ ከቀረውና ከተበላሸው ይልቅ የሚመጣውና ማስተካከል የምትችሉት ጉዳይ ላይ አተኩሩ።

ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid

ሳትጀምር አትሸነፍ!
:
እግርህን ሳታነሳ አትሰበር፤ ባልሆነው አትሸበር፤ ባልተከሰተው አትታሰር፤ ገና ለገና ሊመጣ ይችላል በተባለ የወረደ መላምት ትልቁን ሃሳብህን አትቅበረው። ውድቀትም ይግጠምህ ስኬት ሞክሮ ማየትን የመሰለ ነገር የለም። ምንም ነገር ልታልም ትችላለህ መሳካቱን ልታውቅ የምትችለው ግን ስታደርገውና ስታደርገው ብቻ ነው። ምንም ነገር ሊሆንም ላይሆንም የሚችልበት መንገድ እኩል ነው። የህይወትህ ሚዛን እምነትና አመለካከትህ ነው። እንዲሳካ የምትፈልገው ነገር ቢኖር በፍረሃት ውስጥም ሆነህ ማድረጉ ካለማድረግ የተሻለ ነው። ድፍረት፣ እድገት፣ መነቃቃት፣ ስኬትና ተፅዕኖ ፈጣሪነት በድርጊት ውስጥ ሆነህ የሚፈጠሩ ነገሮች ናቸው። የበይ ተመልካች የምግቡን ጠዓም ሊያውቅ አይችልም፤ በፍረሃት ታስሮ፣ በስጋት ውስጥ ወድቆ ሳይሞክር የቀረም ሊገጥመው የሚችለውን መልካም ነገር ሊያውቅ አይችልም።
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid

የተፃፈ ነገር የለም!
:
አንዳች አስቀድሞ የተወሰነልህና አንተ ምድር ላይ መጥተህ በተግባር የምትገልፀው ነገር ከቶ የለም። ድርሰት ሲኖር ተዋንያን ይኖራሉ። በዚህም ሁኔታ የሰው ልጅ የተፃፈ ወይም የተደረሰ ህይወት ካለው እኛ እየኖርን ሳይሆን እየተወንን ነው ማለት ነው። የህይወት አመክንዮ ግን ፈፅሞ ከዚህ የተለየ ነው። ብዙ ጊዜ "የተፃፈልኝን ነው የምኖረው፣ ይሔ የአርባ ቀን እድሌ ነው ምንም ማድረግ አልችልም፣ ተፈርዶብኛል።" እያሉ የሆነባቸውን ነገር ሁሉ ፈጣሪያቸው እንዳመጣባቸው የሚጠቅሱ ሰዎች ከእያንዳንዱ ምርጫቸው በስተጀርባ ለሚመጣው ውጤት ሃላፊነት ለመውሰድ ዝግጁ ያልሆኑ ሰዎች ናቸው። ፈጣሪ የትኛውንም የሰውን ልጅ ሰነፍ አድርጎ አልፈጠረውም፣ ሰነፍ እንዲሆንም አልፈረደበትም፣ አምላክ ማንም ወድቆ እንዲቀር አይፈልግም። ሁላችንም ነፃ ፍቃድ (Free will) አለን። ያሰኘንን ህይወት ከመኖር በላይ የምንፈልገውን ነገር የማምለኩ ነፃነትም ጭምር በፈጣሪያችን ተሰጥቶናል። ጣዖት አቁመው የሚሰግዱለት ሰዎችም እየኖሩ ነው፣ ፈጣሪዬ አምላኬ ብለው የሚያመልኩት ሰዎችም እኩል እየበሉና እየጠጡ እየኖሩ ነው። ፈጣሪ ፈራጅ ቢሆንና ነፃነትን ባይሰጥ መጀመሪያ እንዲጠፉ የሚፈርድባቸው እነዛ አምላክነቱን ክደው ለጣዖት የሚሰግዱትን ነበር።

ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid

ኑሮህን ኑር!

መስታወት ፊት ቆመህ የእራስህን ገፅ መመልከት ሲኖርብህ ካንተ እንደሚሻሉ የምታስባቸውን ሰዎች ህይወት እየተመለከትክ እራስህን የማይረባ ቅዠት ውስጥ አትክተት። ምንም እንኳን ማህበራዊ ህይወት አስፈላጊ ቢሆንም ማህበራዊ ቅናትና ፉክክር ግን አላስፈላጊ ነገር ነው። ብዙ ሰው ጠልፎ የሚጥለውን እንቅፋት ከፊቱ አስቀምጦ በፍጥነት ይሮጣል፣ የውድቀቱ ምክንያትም እራሱ ይሆናል። የውድቀቱ ጠባሳ ይኖራል ሲሽቀዳደማቸው የነበሩ ሰዎች ግን የሆነ ጊዜ አይኖሩም። አንድ ሰሞን የእርሱ ከእንተና በልጦ መገኘት ከምንም በላይ ያሳስበው ነበር፣ የሆነ ጊዜ የእርሱ አለማደግና የጓደኛው ማደግ ያብከነክነው ነበር፣ የሆነ ሰሞን ከሚያገኛቸው ሰዎች ሁሉ አንሶ መገኘቱ እንቅልፍ ይነሳው ነበር። በስተመጨረሻ ግን እነዚህ ሁሉ ሰዎች አጠገቡ አይኖሩም። ብቻውን የሚቀረው እርሱና እርሱ ብቻ ነው። ጅማሬህ ከማንም ጋር ቢሆንም ፍፃሜህ ግን ከእራስህ ጋር ብቻ ነው፣ ማንንም አይተህ አዲስ ነገር ብተጀምር የመጨረሻው ግብህ ብቻህን ውጤታማ መሆን ነው፣ ማንንም እንዲያግዝህ ብትጠይቅ ዋናውን ስራ የምትሰራው እራስህ ነህ።

ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid

ፍቅርን ያዘው!
:
ፈታኝ አጣብቂኝ ውስጥ ብትገባም፣ አለመግባባት፣ አለመረዳዳት ላሰብከው ግንኙነት መሰናክል ቢሆንብህም፣ ቅድሚያ መስጠት የሚገባህ ነገር ግን ያላስቀደምከው፣ ትኩረትህን የሚፈልግ ነገጰር ግን ያልሰጠሀው ነገር ቢኖርም የፍቅርን ጉዳይ በፍቅር መንገድ ለመፍታት ቅድሚያ ስጥ። የቃላት ጋጋታ፣ ጣፋጭ ንግግር፣ ጊዜያዊ ማሽቃበጥ ለፍቅር ጥላው ቢሆን እንጂ መገለጫው ሊሆን አይችልም። ፍቅርን መኖር ካለብህ በትክክለኛው፣ በአስደሳቹ፣ ስሜት በሚሰጠውና በአምላክ በተባረከው ፍቅር ውስጥ እራስህን አስገባ። ፍቅር ብረሃን ነው። የለም ወይስ አለ የሚል ሰጣገባ ውስጥ ከምትገባ ቢኖር ምን ይጠቅመኛል? ምን አተርፋለሁ? በህይወቴ ብተገብረው፣ ብኖረው ምን አገኛለሁ? ብለህ እራስህን ጠይቅ። ለእራስህ የምትሰጠው ክብርና ፍቅር ከሌሎች ከሚሰጥህ ጋር የተቆራኘ መሆን አይጠበቅበትም። ፍቅር የመሆንህ ዋነኛው ምክንያት እራስህን መቀበል መቻልህና ማንነትህን መውደድህ ነው።
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!

@MentalCounsel

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid

ድል አለን!
:
ከልጅ እስከ አዋቂ፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከትሽ እስከ ትልቅ ሁላችን እንደክብራችን ሁላችን እንደ ኢትዮጲያዊነታችን ድል አለን። ድል ሲባል አንድ ሰሞን የሚነሳ በሌላ ጊዜ የሚወድቅ አይደለም፣ ድል ሲባል በቁስ ወይም በገንዘብ የሚገለፅ ድል አይደለም ድላችን የማንነት ነው፣ ድላችን የእኛነት ነው፣ ድላችን የኢትዮጲያዊነት ብሎም የጥቁር ህዝቦች ጌጥ ነው። ማንም ብቻውን ተዋግቶ ያላሸነፈው፣ ማንም ልብቻው ተጋፍጦ ያላለፈው፣ ማንም ከኢትዮጵያዊነት በላይ ዘሩን ያላስቀደመበት፣ ሁሉም በኢትዮጵያውያዊነቱ እራሱን የሰጠበት፣ በህብረት የተፋለመበት፣ በሃሳብ በአላማ አንድ ሆኖ ተባብሮ ድል ያደረገበት፣ ወራሪውን ሃይል ያሳፈረበት ዘመን የማይሽረው፣ ታሪክ የማይረሳው ታላቅ ድል አለን። እኛ ዛሬ እኛን ስለመሆናችን፣ እያንዳንዳችን የሚያኮራንን ማንነት ስለመያዛችን፣ በየራሳችን ቋንቋ፣ በየራሳችን ባህል ስለመታወቃችን፣ ውስጣችን በጀብድ ልባችንም በንቃት ስለመሞላቱ ዋናው ምክንያት የአያት ቅድመ አያቶቻችን አርበኝነት ነው።


እንኳን ለ128ኛ የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid

የምትሰጠው አትጣ!

የሚሰስት ትርፍ የለውም፣ መስጠት የማይወድ በረከት የለውም፤ እርካታ የለውም። መኖር በመስጠት ውስጥ ነው። ስትሰጥ የምታገኘውን ስጦታ፣ የሚሰማህን ስሜት ምንም ብታደርግ አታገኘውም፣ ምንም ብትፈፅም ሊሰማህ አይችልም። የህይወት ትርጉም የአምላክን ፀጋ በእኛ በኩል ለሰዎች ማሻገር ነው። ሁሉን የሚሰጥ ደግ አምላክ፣ ቸር ፈጣሪ ነው። ባህሪው መስጠት ነው፤ ንፉግነት የለበትም። የእርሱን ባህሪ ለሚከተለው ሌላ ይጨምርለታል፤ ለማይሰጠው ለንፉጉም የሚገባውን ባይከለክለውም እንኳን በመስጠት የሚያገኘውን የተትረፈረፈ በረከት ግን ያሳጣዋል። ለጋስ ለመሆን ከሰፊ አዛኝ ልብ ውጪ የሚያስፈልግ ነገር የለም።

ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
@MentalCounsel

❤️ LIKE & SHARE

ቤተሰብ ይሁኑ👉 https://t.me/letiwulid