Neueste Beiträge von ለጎጆዬ (@legojoye_minbertv) auf Telegram

ለጎጆዬ Telegram-Beiträge

ለጎጆዬ
በትዳር እና በልጅ አስተዳደግ ዙሪያ የሚያጠነጥነውና በሚንበር ቲቪ ተዘጋጅቶ ስለ ሚቀርበው ለጎጆዬ ዝግጅት መረጃ እዚህ ያገኛሉ።
5,131 Abonnenten
1 Fotos
8 Videos
Zuletzt aktualisiert 06.03.2025 23:14

Ähnliche Kanäle

ET MUSLIM INSIDER
6,059 Abonnenten
Medicine Daily
1,316 Abonnenten

Der neueste Inhalt, der von ለጎጆዬ auf Telegram geteilt wurde.

ለጎጆዬ

01 Sep, 13:03

9,710

👱🏼‍♂️🧕🏼በእርግጥ አብሮ በመቆየትና በሒደት ግን የመቀራረብ እድላቸው እየጨመረ ይመጣል አንዱ ሌላውን መረዳትና መግባባቱ እያደገ ሲሄድ የልዩነት ነጥቦች ደግሞ እየጠበቡና እያነሱ ይሔዳሉ፡፡ የትዳር ተጣማሪን ባለበት ሁኔታ ተቀብሎ ለመኖር እራስን ማዘጋጀት ብልህነት ነው፡፡ የሚመሰረተው ቤት ከአደጋ ለመከላከል እጅግ ስለሚረዳው::
👱🏼‍♂️🧕🏼አንዳንድ ጥናቶች ባልና ሚስት ረዘም ላለ ጊዜ አብረው ከመኖራቸው የተነሳ ብዙ ነገራቸው እየተመሣሠለ ሄዶ በመጨረሻም አካሔዳቸውና ቁመናቸው ጭምር እንደሚመሣሰል ይገልፃሉ፡፡
•“ባልና ሚስት ከአንድ ወንዝ ይቀዳሉ” ማለትም ይኸው ነው፡፡
👱🏼‍♂️🧕🏼ስለባልና ሚስት ልዩነት ወደፊት በተለያዩ ርእሰጉዳዮቻችን እየተመላለስን ግንዛቤ ለመፍጠር የቻልነውን ያህል ስለምንሞክር ለጊዜው እዚህ ላይ እናቁም።
በኡስታዝ አብዱልገፋር ሸሪፍ
ሚንበር ቲቪ ዘወትር ማክሰኞ
ምሽት 2:30-3:30
 
ለጎጆዬ

30 Aug, 06:11

7,198

በኡስታዝ አብዱልገፋር ሸሪፍ
ሚንበር ቲቪ ዘወትር ማክሰኞ
ምሽት 2:30-3:30
ለጎጆዬ

30 Aug, 06:10

8,195

በአላህ ስም እጅግ አዛኝ ሩህሩህ በሆነው
ለትዳር መመስረት ሊኖር የሚገቡ
ስነልቦናዊ ዝግጅቶች
ክፍል (1)
መግቢያ
 🧕🏼👱🏼‍♂️አንድ ግለሠብ ደስተኛ፣ ሠላማዊ፣ ፍቅር የሠፈነበት፣ እርስ በርስ መከባበርና መተዛዘን የሰፈነበት ቤት ለመመስረት ጉዞ ሲጀምር የሚያስፈልጉት በርካታ ዝግጅቶች ያሉት መሆኑን መረዳት አለበት፡፡
🚶🏻‍♂️ማንም ሰው እንደሚጉዋዝበት ጉዳይ የመንገዱ ርቀትና መሰል ጉዳዮች ልክ ቅድመ ዝግጅት ያደርጋል።
•ይህም የሰዎች ልምድ ሆኖ የትኛውም አይነት ጉዞ በተለይ አካላዊና መንፈሣዊ ዝግጅቶች ይደረጉበታል፣ጉዞው ለጉብኝት፣ ለስራ፣ ለዳዕዋ፣ ለጦርነት ወይም ትግል ለትምህርት (ለመማር/ለማስተማር/ ሊሆን ይችላል፡፡
•ለዚህም ጉዞው ይረዳው ዘንድ ቁሣዊና ስነልቦናዊ ዝግጅት ማድረጉ አይቀርም ሁሉም የህይወት ዘርፎችም እንዲሁ ናቸው፡፡
•በዚሁ አግባብ ወደ ትዳር የሚጓዝ ማንኛውም ግለሰብ ቁሣዊ፣ አካላዊና፣ ስነልቦናዊ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አለበት፡፡ ይህ የጥምረት ህይወት ረጅምና ውስጡ በርካታ ውጣውረዶች ሊገጥሙት እንደሚችል ከግንዛቤ መግባት አለበት፡፡
•ለዛሬ ሥነልቦናዊውን ዝግጅት ትኩረት አድርገን ብንመካከር ጥሩ ነው፡፡
🤔በዚህ ርእሰ ጉዳይ ስንመካከር አላማው ማስፈራራት ወይም ትዳርን ማወሳሰብ አይደለም።ተቁዋሙ ሊደረግለት የሚገባውን ዝግጅት በማስታወስ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ወደ ትዳር ሲያቀኑ ሊያደርጉት የሚገባን ቅድመ ጥንቃቄና ከአሁኑ ለትዳራቸው መሳካት ማድረግ ያለባቸውን ጥረትና ኢንቨስተመንት ለማስታወስ ነው፡፡
👏🏼ስኬታማ ቤተሰባዊ ህይወት እንዲሁ ዝም ብሎ የሚከሰት ወይም በእድል የሚገኝ ሳይሆን  በቂ ቅድመ ዝገጅት የሚፈልግ፣በእውቀት፣በእቅድና ፕሮግራም ተመርቶ የሚጉዋዝ ጠንካራ ስራ የሚፈልግ መሆኑን በጊዜ ለማስታወስ እወዳለሁ፡፡
👇🏼ስለሆነም ከዚህ በታች ለትዳር በመንደርደር ላይ ለሆኑ እህት ወንድሞች ትኩረት አድርገው ሊዘጋጁባቸው የሚገቡ ወሳኝ ነጥቦችን እናነሳለን፡፡ ቀድሞውኑ በትዳር ውስጥ ያለን ሰዎች ደግሞ አሁንም የቀረንን ጊዜ ደስ ብሎን እንድናሳልፈው ከሚጠቀሱት ባህሪያት አንጻር እራሳችንን ገምግመን ማስተካከል ያለብን ነገር ካለ ብንሞክር ለውጥ ማግኘት እንችላለን በአላህ ፍቃድ፡፡ 🤚🏼1. ትዳር ሀላፊነትን መውሰድ ነው
•ማንኛውም ለትዳር የሚንደረደር ግለሰብ መረዳት ካለበት እውነታዎች አንዱና ዋነኛው ጫንቃው ላይ አዲስ ሃላፊነት የሚጫንበት መሆኑን ነው፡፡
👱🏼‍♂️ወንድሜ ባል በሆንክ ማግስት ስለራስህ ብቻ ሳይሆን ስለሌሎችም ህይወት ሃላፊና ተጠያቂ መሆንክን መርሳት የለብህም፡፡ የሚስትህ (ቀለቡዋ  ጤናዋ ደህንነቱዋ ስነምግባሩዋ ወዘተ)፣ የልጆችህ (ቀለባቸው፣ ጤናቸው፤ ትምህርታቸው፡ የዲናቸውና የስነምግባራቸው)  የቤት ጉዳይ (ኪራዩ፡ ደህንነቱ አመቺነቱ ወዘተ) ወዘተ ጉዳይ ቀጥታ ይመለከትሃል፡፡ ዝም ብሎ ማር እየላሱ መኖር ትዳር ውስጥ የለም
🧕🏼ሚስትም፤ በርከት ያሉ ሃላፊነቶች እንደሚጠብቅሽ ልታውቂ ግድ ነው፡ የቤቱ አስተዳደር፡ የልጆችሽ ጉዳይ፣የባልን ምቾት መጠበቅ፡ የቤቱ ሰላም ወዘተ ያልለመድሺያቸው ሃላፊነቶች ግር ብለው ይመጡብሻል፡
•ከእንግዲህ የታጠበ መልበስ፤ የበሰለ መብላት፤ በተነጠፈ መተኛት አሁን ላይኖር ነው፡ አንቺው ልትሰሪው ነው፡ ለራስሽ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም፡፡

🤚🏼ሀላፊነት
 
•በዚህ ህይወት ውስጥ ስሜታዊ ትስስር ብቻውን አይበቃም፡፡ ባይሆን የወሰድከውን ሃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት በምትችልበት ቁመና ላይ መገኘት የግድ ነው፡፡ መልዕክተኛው እንዲህ ማለታቸው ይታወቃል
•“አዋጅ ሁላችሁም ጠባቂዎች ናችሁ፤ ሃላፊነት በወሰዳችሁበትም ጉዳይ ተጠያቂዎች ናችሁ፡፡”
🤔ይህ ጉዳይ ወንዶችን ብቻ የሚመለከት አይደለም ሴቶችንም የትዳር ሃላፊነት መሸከም እንዲችሉ ማሰናዳት ያስፈልጋል፡፡
•ማፍቀርና መፈቀር ታላቅ ፀጋ ቢሆንም ትዳር የሚፈልጋቸው ሌሎች ግብዓቶች እንዳሉት መረዳት አለብን፡፡ አንድ ቤት የሚገነባው በስሜታዊው ትስስር (ፍቅር) ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ጉዳዮች አሉት በተለይ ከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት ይፈልጋል።
🤫ፍቅር ያሸንፋል እያሉ በመፎከር ብቻ ትዳር አይሰምርም፡፡ ይህ አባባል ጥልቀት የሚጎድለው ይመስለኛል፡ ምሳሌ ፡
🧕🏼ሚስት ባሏ ችግር ቢነካውና ስራ ቢበላሽበት ወይም ግራ መጋባት ቢያዋክበው ቤቷን ሳታፈርስ እንዴት ነው ይህን ፈተና የምታልፈው?
👱🏼‍♂️ባልም ሚስቱ አያርገውና በከባድ ህመም ብትያዝ ወይም ስነምግባሩዋ ቢጎረብጠው ምንድነው የሚያደርገው?  ቤተሰቦቹዋ ጋር መመለስ ነው የሚያስበው ወይስ ወድቆ ተነስቶ እንድትድንና እንድደትሻሻል በመጣር ወደ ድሮ ፍቅራቸው ለመመለስ ነው የሚያስበው???

🤚🏼ሀላፊነት
👱🏼‍♂️🧕🏼ሁለቱም ሃላፊነት ለመውሰድ ቅድመ ዝግጅት የነበራቸው (የሰለጠኑ) ከሆነ አንዱ ሌላውን ተንከባክቦ የመጣውን አስቸጋሪ አጋጣሚ ለመጋፈጥ ታጥቆ ይነሣል፡፡
❤️ይህም እንክብካቤና የአይዞህ ባይነት መንፈስ እውነተኛውንና ቤታችንን ቀጥ አርጎ የሚያቆመውን ጥልቅ ፍቅር በሌላኛው ወገን ላይ ይፈጥራል፡፡
•በኖርማል (መደበኛ) ጊዜማ ሁሉም አፍቃሪ መምሰሉን ሊያውጅ ይችላል፡፡ በጣፋጭ ቃላት ከተከሸኑ አንድ ሺ የፍቅር ቃላት በዚህ አይነት አጋጣሚዎች የሚንፀባረቁ የሃላፊነት ስሜቶች ቀልብን ይገዛሉ፡፡ በጥምረታችን ላይ ተጨማሪ ማጠናከሪያ ማህተሞች ሆነው ያገለግላሉ፡፡
 
🤚🏼ሀላፊነት
•ቀጥሎ ባለው የአላህ ቃል የሁለቱም ወገኖች ሁለት ሁለት ሃላፊነቶች እንዳለባቸው ተንፀባርቋል፡፡
👱🏼‍♂️“ወንዶች በሴቶች ላይ ቋሚዎች (አሣዳሪዎች) ናቸው፡፡ አላህ ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ በማበላለጡና (ወንዶች) ከገንዘቦቻቸው ላይ (ለሴቶች) በመስጠታቸው ነው፡፡
🧕🏼መልካሞቹም ሴቶች (ለባሎቻቸው) ታዛዦች አላህ ባስጠበቀው ነገር ሩቅን ጠባቂዎች ናቸው፡፡”
👱🏼‍♂️በአንቀፁ እንደተጠቀሰው ወንዶቹ የበጀትና አስተዳደር ጉዳይ ሃላፊነታቸው ሲሆን
🧕🏼ሴቶች ደግሞ ቤትን ልጅንና ባልን (ባለበትም በሌለበትም) መንከባከብና መጠበቅ ሌላኛው ደግሞ ባልን በመልካም ሲያዝ መታዘዝ ሃላፊነቷ ነው፡፡
🤚🏼ሀላፊነት
👱🏼‍♂️ሚስትህን ማብቃት፡ ማሳደግ (ማስተማር ማሰልጠን)፤ በአካልም፤ በአእምሮም፡ በመንፈሳዊ ህይወቷ፤ ላይ በሙሉ ማገዝና መደገፍ አለብህ ለልጅህ ምን አይነት እናት ነው የምትመርጠው?ስገምት ንቃተ ህሊናዋ ከፍ ያለ፣በእምነቷ ላይ በቂ ግንዛቤ ያላት፣በራሷ የምትተማመን፤ ብስለት ያላት እንድትሆን የምትፈልግ ይመስለኛል ስለዚህ በነዚህ ጉዳዮች ላይ እድገት እንዲኖራት ለማገዝ ተዘጋጅ።
🧕🏼ሴቶችም እሱ አስተምሮ አግዞ  ሲያበቃሽ ለቤቱ ብርታት እንድትሆኚ እንጂ ትከሻ ለመለካካት እና አላስፈላጊ ፉክክር ውስጥ ለመግባት እንዳልሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡
•የወደፊቷ ሚስትም (አሁን በትዳር ላያ ያላቹም ብትሆኑ) ባልን አግዞ ለስኬታማነቱ መትጋት፣ለልጆችሽ የተሻለ አባት እንዲሆን ነውና ጥቅሙ የጋራ ስለሆነ አስቢበት፤ በምን መንገድ ነው ላግዘውና ብቃቱ እንዲጎለብት የምረዳው ብለሽ  ብትለፊ መልካም ነው፤ ውጤቱን ታይዋለሽ፡፡
•መደጋገፍ እውነተኛ የፍቅር ስሜትን ያመጣል፡ ሃላፊነት የሚሰማቸው ሰዎች ደግሞ ለመፈቀር (ለመወደድ) ከፍተኛ እድል አላቸው፡
 ይቀጥላል…
ለጎጆዬ

21 Aug, 17:04

9,744

በአላህ ስም እጅግ አዛኝ ሩህሩህ በሆነው
ኢስላም ወደ ጋብቻ ያደረገው ጥሪ
ክፍል(5)
(ሁክሙ) አዝዋጅ
🔸ጋብቻን አስመልክቶ የሚኖረው ህግ (ፍርድ) እንደየግለሰቡ ነባራዊ ሁኔታ የሚለያይ ሆኗል አራት አይነት ፍርድ (ስርዓት) የሚያርፍበት ይሆናል፡፡ እነሱም ግዴታ፣ ሱና (የተወደደ)፣ የተጠላ (ከረሃ)፣ ሐራም ናቸው።
🤔 ግዴታ
ነፍሱ ጋብቻን የምትፈልግ፣ ችሎታው (አቅሙ ያለው) እና ካላገባ ሐራም እሠራለሁ ብሎ ለሚፈራ ሰው ጋብቻ ግዴታ ተደርጎበታል፡፡ ችሎታ (አቅሙ) ያለው በማለት ውስጥ የተፈለገው አካላዊ፣ ስነልቦናዊና የገንዘብ አቅምን ያካትታል “እናንተ ወጣቶች የትዳርን ጣጣ ከቻላችሁ አግቡ” ብለዋል ሩሱሉ(ሰ.ዐ.ወ) ጥሪው ሁሉንም አቅም ያለው አካል ወንድም ሆነ ሴት የሚመለከት ነው።
🤔ዋጂብ
(ፈርድ) ነገር በኢስላም የህግ ሊቃውንት (ፉቀሃዕ) ዘንድ ለሰራው ሰው ሽልማት (አጅር) የሚያስገኝ ለተወው ሰው ቅጣትን የሚያስከትል ድንጋጌ ነው፡፡ ልክ እንደ ፆም (ረመዳን) ለፆመኛው አጅር አለው፡፡ ያለበቂ ምክንያት ለሚያፈጥረው ቅጣት ይጠብቀዋል፡፡ ሰላትም እንዲሁ ነው ለሰገደው ያሸልማል ለተወው ያስቀጣዋል፡፡
እናም ነፍሱ ለፈለገች (ለጓጓች) ፀያፍን ለፈራ (ካላገባሁ መንዳለጤ አይቀርም ብሎ ለፈራ ማለት) ነው አቅም ያለው ሆኖ ከተገኘ በሱ ላይ ጋብቻ ዋጅብ ወይም ግዴታ ይሆንበታል፡፡ ከተወው ወንጀል ይሆንበታል “ያላገቡትን ከናንተ መካከል አጋቡዋቸው፡… አንኪሁ (አጋቡ) የሚለው ትዕዛዛዊ ዓረፍተ ነገር ነው፡፡ የሚያናግረውም በተለይ ወላጆችን ሲሆን የሚመለከታቸው ባለስልጣናትም (ቢኖሩን) ይካተታሉ ባገሩ የሚኖሩ ተደማጭነት ያላቸው ሰዎች ሃብታሞች፣ ታላላቆች ሁሉም በቻለው ልክ ወጣት ወንዶችንና ሴቶችን አቅማቸው የፈቀደውን እንዲያጋቡ ታዘዋል፡፡ በሌላ በኩል ወጣቱ በራሱ ላይ ፊትናን ይፈራል የአቅም ውስንነት አለበት የሚረዳው አካል አላገኘም እራሱን መጠበቅ ብቻ ነው፡፡ የሚችለው ይታገስ “የኒካህን ጣጣ መሸፈን የማይችሉ ይጠበቁ…
አላህ ከችሮታው እስኪያብቃቃቸው ድረስ እስከዚያም በፆም ላይ ይበርታ (ያዘውትር) አብደላ ኢብኑ መስዑድ እንዳወሩት ከረሱሉ ዙሪያ እንኖር ነበር ለጋብቻ የሚሆንም ምንም ገንዘብ አልነበረንም እንዲህ አሉን “እናንተ ወጣቶች ከናንተ መሀል የትዳርን ጣጣ የሚችል ያግባ አይንን ለመስበርና ብልትን ለመጠበቅ ይረዳናልና የሚልችል ሰው ፆምን ያዘውትር እርሱ የፍትህወት ፍላጎትን ይቀንሳልና አላህም እንዲ ብሏል፡ “ሴቶች ባሮቻችሁን መጠበቅን ቢፈልጉ የቅርቢቱን ህይወት ጥቅም ለመፈለግ ብላችሁ በዝሙት ላይ አታስገድዷቸው፡፡ የሚያስገድዳቸውም ሰው አላህ ከመገደዳቸው በኋላ (ለተገደዱት) መሀሪ አዛኝ ነው፡፡” ኑር 33 እዚህ ጋር መልዕክቴ ማንኛውም አባት ወይም እናት ለሴት ልጃቸው የሚመጥናት ሰው መጥቶ ሲጠይቃቸው የግል ጥቅማቸውን (ገንዘብን) ምክንያት አድርገው የሚመልሱ ከሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ልጆቹን ለዝሙት እያበረታቱ መሆኑን ይገንዘቡ፡፡ በእርግጥ ዛሬ ላይ ስንት የዚህ አይነት ቤተሰብ እንዳለ ባላውቅም አልፎ አልፎ ቢሆንም አይጠፋምና መጠንቀቅ መልካም ነው፡፡ሐርም በጣም ቀሎና ተመቻችቶ ባለበት ሁኔታ ሀላልን ማወሳሰብ ለሀራም በር እንደመክፈት ስለሆነ ቢታሰብበት ለማለት እወዳለሁ፡፡ በቲርሚዚ ዘገባም ረሱሉ(ሰ.ዐ.ወ) “አሊይ ሆይ 3 ነገሮችን አታዘግይ ሰላት ወቅቷ ከደረሰ፣ ጀናዛም ከቀረበ(ከተሰናዳ) እና ለላጤዋ እኩያዋ ከመጣላት” ፈጥኖ መፈፀም ከሚገቡ ተግባራት ናቸው፡፡
😀 ሱና (ተወዳጅ)
ነፍሱ ለምትፈልግና አቅሙ ለቻለ ሆኖም ዚና ላይ እወድቃለሁ ብሎ ለማይሰጋ ሰው ጋብቻ ተወዳጅ (ሱና) ይሆንለታል፡፡ ሱና (ተወዳጅ ስራ) በአሊሞቹ ዘንድ ለሰራው ሰው ምንዳ (አጅር) የሚያስገኝ ሲሆን የተወውን ሰው አያስቀጣም፡፡ ልክ እንደ ሱና ሰላትና ፆሞች ነው፡፡ ለሰገዳቸውና ለፆማቸው ሰው ከአላህ ዘንድ ትሩፋትን ያስገኛሉ ላልሰራ ሰው ኸይር አመለጠው እንጂ ወቀሳ አይኖርበትም ነፍሱ ፈላጊ ሆና አቅሙም እያለው ዚና ላይ እወድቃለሁ ብሎ ስላልፈራ ብቻ ጋብቻን ሱና ነው ብንልም መተውን ለማበረታታት አይደለም፡፡ በእርግጠኝነት ማግባቱ ካለማግባቱ ይበልጣል፡፡ ጥንድነት የፍጥረተ አለሙ ሱና መሆኑን ከዚህ ቀደም አንስተናል ለብቻ መሆንም ነገሮች ካላመቹና ከአቅም በላይ ከሆነ ነው እንጂ የሚደገፍና የሚበረታታ ተግባር ሆኖም አይደለም፡፡ ጋብቻ የሚመሰረተውም ዚና ፍራቻ ብቻ አይደለም፡፡
ከዚህ ቀደም ረሱሉ ቤት መጥተው ጠይቀው ስለሔዱ ሦስት ሰዎች ባነሳነው ሀዲስ ጋብቻ ሱናቸው እንዲሆንና ይህን ሱና (መንገድ) የሚተው ሰው ከእሳቸው መንገድ ውጭ መሆኑን ማንሣታችን አይዘነጋም፡፡ ስለሆነም የረሱል መንገድ ተከታይና የረሱሉ ወዳጆች የሆናችሁ ወጣቶች አቅማችሁን አሰባስባችሁ ብታገቡ፣ ቤተሰብ ብትመሠርቱ ይበልጥባችኋል፡፡ ከረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) የህይወት መንገድ ማፈንገጥም አይገባም።
🤔ከረሃ (የሚጠላበት) ሁኔታ
ጋብቻ በሚከተሉት ሁኔታዎች የማይደገፍ የማይበረታታ ወይም የተጠላ ተግባር ይሆናል፡፡ የተጣማሪውን መብት በገንዘብ፣ በጤና ወይም በስነ ልቦና ችግሩ ምክንያት ማሟላት የማይችል ሰው ጋብቻ አይወደድለትም፡፡(ወል የስታእፊፊለዚነ ላየጂዱና ኒካሃን ሀታ ዩግኒየሁሙላህ)ሌላ ሰው ያጫትን ሴት ለማጨት መሔድም የተጠላ ነው “ከእናንተ አንዳችሁ ወንድሙ ያጫትን ሴት እንዳጫት (ተደርቦ)” ብለዋል መልዕክተኛው፡፡ በዚህ ሁኔታ ያገባ ሰው ጋብቻው መክሩህ (የተጠላ) ነው፡፡ በእርግጥ ይህ ጉዳይ የኪላፍ አጅንዳ ነው ሀራም ነው ከራሃ በሚለው፡፡ ይህ በወንድማማቾች መካከል ቅራኔ አልፎም ብጥብጥ ሊከስት የሚችልና ማህበራዊ ትስስርን የሚበጣጥስ ተግባር በመሆኑ ተገቢ አይደለም፡፡አንዲት ሴት ታሪክ ጓደኛዋን ይህ ሰው በዲኑ ጥሩ አይደለም አታግቢው ብላት ለራሷ አገባቺው ምነው እንዴት እንዲህ ታደርጊያለሽ ስትላት የወላጅ ትእዛዝ ሆኖብኝ ነው ብላት እርፍ።
ሌላም እገሊትን ለምንልኝ ብሎት ሽምግልና ይልከዋል እሱም ሄዶ ለራሱ ለምኖና ኒካህ አስሮ ምልስ ምን አሉህ እገልዬ ልጅቷ አንተን ከሆነ እሺ ስትል እኔም በቃ ይሁን ብዩ ኒካህ ለራሴ አስሬ መጣሁ፤ አለው፡፡ ሙጊራ ኢብኑ ሹዕባ (ከአረብ ስማርቶች አንዱ ነበር) እንዲህ ሆንኩ ብሎ የራሱን አጋጣሚ ይተርካል “ሰዎች በሃሳብ በልጠውኝ አያውቁም ነበር አንድ ከቁረይሽ የሆነ ወጣት ሲቀር አንዲት ቆንጆ ልጅን ላገባት ፈልጌ አማከርኩት፤ ኧረ አትሆንህም እኔ አንድ ወንድ ሲስማት አይቻለሁ አለኝ፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ እዚያው ወጣት ቤት ለሰርግ ተጠራና ያቺን ልጅ አግብቷት ያያል፡፡ ሙጊራም እንዴት እንዲህ ታደርጋለህ ለኔ ያልከኝ ብለህ ይለዋል አዎ አባቷ ሲስማት አይቻለሁ አለና አረፈው።ብዙ ታሪኮች ብናወራ እህቷን ለመጉዳት ማግባት፣ ጓደኛዋና አግብቼ ላበሳጫት ተብሎ ማግባትም የሚጠላ ነው።
🔸 አታሎ (ሸውዶ) ማግባት
ለጎጆዬ

21 Aug, 17:04

7,237

ከሁለት አንዱን አታሎ ኒካህ እንዲታሰር ማድረግ ለምሳሌ ቤቱ የኔ ነው ይላል ኋላ ተከራይ ሆኖ ይገኛል፡፡ ከዚህ ዩኒቨርሲቲ ተመርቂያለሁ ትላለች ከዚያም ውሸት መሆኑ ሲታወቅ ይህ አይነቱ ስታይል ተገቢ አይደለም፡፡እራስን ክቦ አጋኖ ማቅረብና ኋላ ሲታወቅ ከማፈር እውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር ይሻላል፡፡
😲ሀራም (እርም) የሚሆነው
ሚስቱን (ባሏን እንደሚበድል እርግጠኛ ለሆነ ሰው ጋብቻ ሀራም ነው፡፡ ሀራም እንደሚታወቀው የሰራ ሰው የሚቀጣበት የተወው ሰው የሚሸለምበት አግባብ ነው፡፡ ተጣማሪውን በተለያየ ሁኔታ እንደሚበድል ያረጋገጠ ሰው ለምሳሌ ቀለብ ባለመስፈር አዛ እንደሚያደርግ እያወቀ፣ ባለበት አካላዊም ሆነ ስነልቦናዊ ችግር ተራክቦ መፈፀም እንዳለበት እያወቀ(ቀች) ጋብቻን መፈፀም ክልክል ነው፡፡ ከስግብግብነቱ ብዛት ሚስቱን ቀለብና አስፈላጊ ነገሮችን ባለማሟላት የሚቀጣ መሆኑ ለታወቀ ሰው ልጁን መስጠት ክልክል ነው።
ይህ ኢስላማዊው የሸርዓ ህግ ያስቀመጠው ስርዓት ነው፡፡ ተጨማሪ ማብራሪያ የፈለገ ሰው ዝርዝር ከሚያቀርቡ የፊቅህ ኪታቦች ወይም አሊሞች ዘንድ መሔድና ማግኘት ይችላል፡፡ በግሌ ግን ጋብቻን የሚስትን ያልወደድነውን ባህሪ ለመግራት፣ ለመበቀል (የልጅቷን ህይወት) ለማበላሸት፣ ሆነ ዱንያዊ ጥቅም ተጠቅሞ ለመውጣት (የተወሰነ ገንዘብ ቦጭቆ ለመፍታት) ወዘተ… በሆኑ መጥፎ ኒያዎች ጋብቻን መመስረት ተገቢ ነው ብዬ አላምንም፡፡ውጭ ለመድረስ ብቻ ዲያስፖራ ስለሆነ ተስማምቶ እዚያ ስደርስ ወይም ከትንሽ ጊዜ በኋላ ፈትቼው የራሴን ኑሮ እኖራለሁ ብሎ ማግባትም ነውር ነው፤ ይህ ለሙተዓ የቀረበ በመሆኑም ተቀባይነት የለውም፡፡ ነግ በኔን ማሰብ ጥሩ ነው በራስህ ላይ እንዲሰራ የማትፈልገውን ክፋት በሌሎች ላይ አትሰራ ሲደርስብህ መፅናኛ አታገኝም፡፡
🔸 ከላይ ባሳለፍነውም ይህን በሌላ ምክንያት ፆታዊ ግንኙነት ማድረግ የማይችል ሆና ሳለ ኒካህ ታስሮ ወደቤት ከተገባ በኋላ ከታወቀ (አንዱ ሌላውን ቀድሞ ሳያሳውቅ የገባበት ከሆነ ኒካሁን ያለ ሌላኛው ሰው ፍቃድ ለሴቷ በቃዲው ውድቅ ሊደረግላት መብት አላት። ለወንዱም መፍታት መብቱ ነው፡፡በእድሜ ልክ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ነግረው ቢገቡበት መልካም ነው ከገቡ በኋላ ከመነታረክና ከመራበሽ ቀድሞ አሳውቆ ስምምነት ከተደረሰ በኋላ ከሆነ ችግር የለም፡፡ ነገር ግን ተደብቆ (ከሁለት አንዱ) ከኒካሁ በኋላ ከታወቀ በፍርድ ቤት ኒካሁ ይቀደዳል ቅጣት ሊጣልበት ይችላል ማለት ነው፡፡ይህ ክፍል ተጠናቀቀ🙏
በኡስታዝ አብዱልገፋር ሸሪፍ
ሚንበር ቲቪ ዘወትር ማክሰኞ
ምሽት 2:30–3:30
ለጎጆዬ

16 Aug, 07:35

8,565

በአላህ ስም እጅግ አዛኝ ሩህሩህ በሆነው
ኢስላም ወደ ጋብቻ ያደረገው ጥሪ
ክፍል(4)
🔸እስልምና ተፈጥሯዊውን የፍትወት ፍላጎት ከሥጋዊው መንገድ ውጭ ላረከ ሰው ከባድ ቅጣትን (ግርፋት/ግድያ) በዱንያ ላይ ደንግጓል፡፡ ውሸታሞችን መቅጣት ለእውነተኞች ማበረታቻ ነው ሰነፎችን መቅጣት ለስራ ለማበረታታት ነው ከትዳር ውጭ የሚማግጡ ሰዎችን ከባድ ቅጣት ሲቀጣ ጨዋዎችን ወደ ትዳር ለመጣራትና በማበረታታት ነው፡፡
🔸የትዳርን ጣጣ (መህርን) ቀለል በማድረግ ኢስላም ጋብቻን አበረታቷል አቅም ያላቸውን ሰዎችም ማግባት የሚፈልጉ እህት ወንድሞችን እንዲረዱ ጥሪ አድርጓል፡፡ እንግዲህ ወጣቶቻችን ከጋብቻ መራቅ ምን ያመጣል ማንስ ነው ተጠያቂው?በአንድ በፓሪስ (የሚገኝ የጥናት ተቋም) በተደረገ ጥናት የወጣቶች ከህጋዊ የጋብቻ ማዕቀፍ መራቅ በተለይ በአውሮፓ ብልግና እንዲስፋፋ፣ እራስን ማጥፋት፣ የስነ ልቦና ቀውሶች እንዲበራከቱ፤ስርዓት የለቀቀ የፆታ ልቅነት (ሹዙዝ) እንዲበራከት የሚወለዱ ልጆች ቁጥር ማነስ፣ ወዘተ.. ጣጣ በማምጣት አውሮፓን አሮጌው (አሮጊቷ) አህጉር አስብሏል፡፡ይህን ካስተዋሉ በኋላ አሁን አሁን ድምፆች መሰማት ጀምረዋል አግቡ ተጋቡ የሚሉ አንዳንድ ቆጠራዎች የተወሰኑ ሀገራት በዚሁ ሂደት ከቀጠሉ ከህዝብ ማነስ ምክንያት ሊጠፉ (ሊወድቁ) እንደሚችሉ ተፈርቷል።
🤔ዛሬ ላይ የሚኖረው ህዝባቸው እየሞተ ስለማይተካ መሬት፣ ህንፃ፣ ፋብሪካ፤ መኪና አውሮፕላን ገንዘብ ወዘተ ያለበት ግና ሰው የሌለበት ምድር እንዳይሆኑ ያስፈራቸዋል ወጣቶች ከትዳር የሸሹበትና ቤተሰብ የፈረሰበት ማህበረሰብ መሆናቸውን አምነው አንዳንዶቹ ስለቤተሰበ ጠቀሜታ የሚያስተምር ኮሌጅ ከፍተዋል።በተጨማሪም ቤተሰብን ለማበረታታትና ለመደገፍ የሚሰራ የሚያስተምር እና ቤተሰቦችን እንዲያጠናክር ሚኒስቴር መስሪያ ቤትም አቋቁመዋል፡፡ (የቤተሰብ ሚኒስቴር) እንደ ጀርመን ባለ ሀገር “በአንድ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲ የቤተሰብ ታሪክ መምህር የሆነች አንዲት ምሁር “ወጣቶቻችን ለትዳር ማበረታታትና ቤተሰብ እንዲመሰርቱ ማስገደድ አለብን አሁን ቤተሰብ መመስረታቸው ግድ ሆኗልና” ብላለች፡፡ እንግዲህ ትዳርን በግዳጅ የሚል ማህበረሰብ መፍጠሩ አግራሞትን ይጭራል፡፡ እንዲፈርስ ሲሰሩ ከከረሙ በኋላ🤔ይቀጥላል…
በኡስታዝ አብዱልገፋር ሸሪፍ
ሚንበር ቲቪ ዘወትር ማክሰኞ
ምሽት 2:30–3:30
ለጎጆዬ

12 Aug, 18:46

6,330

በአላህ ስም እጅግ አዛኝ ሩህሩህ በሆነው
ኢስላም ወደ ጋብቻ ያደረገው ጥሪ
ክፍል(3)
🔸 የረሱሉን ሱና ተግባራዊ በማድረግ
የሚገኝ አጅር
አነስ በዘገቡት ሀዲስ “ሦስት ሰዎች ወደ ነቢዩ ሚስቶች (ቤት) በመምጣት ስለ ኢባዳቸው ጠየቁ ሲነገራቸው ጊዜ እንደማሳነስ አሉና ከዚያም የት ነን እሳቸውን እንደሆነ ያለፈውንም የወደፊቱንም ስህተት አላህ ምሯቸዋል፡፡ ስለዚህ ተባባሉ አንዱ እኔ የለይል ሰላት ለሁሌውም እሰግዳለሁ፤ ሌላኛው እድሜ ልኬን እፆማለሁ አላፈጥርም ሦስተኛው ደግሞ ሴቶችን እርቃለሁ፡፡ ለዘላለሜ አላገባም አለ፡፡ ረሱሉም(ሰ.ዐ.ወ) መጡና እናንተ ናችሁ እንዲህ እንዲህ ያላችሁት እኔ ግን በአላህ ይሁንብኝ ከሁላችሁም በላይ አላህን የምፈራውና የምጠነቀቅ ነኝ ነገር ግን እፆማለሁ አፈጥራለሁ፤ እሰግዳለሁ እተኛለሁ ሴትም (ሚስትም) አገባለሁ፤ (ይህ መንገዴ ነው) ከኔ መንገድ ያፈነገጠ ከኔ አይደለም፡፡ አሉ፡፡ ስለዚህ ያለ በቂ ምክንያት ከጋብቻ እራሱን ያገለለ ሰው ከነቢ መንገድ አግልሏል፡፡ የመልክተኛውን መንገድ ተቃርኗል፡፡ በተቃራኒው ለፍቶ ጥሮ ግሮ ቤተሰብ ለመመስረት የሚታገለው ሰው ግን የእሳቸውን ተከትሏል ፈለጋቸውን በህይወቱ በሙሉ ፈፅሟል።
🔸አላህን በመታዘዝ መረዳዳት ያስገኛል
ላጤ ጎረቤቱን ጓደኛውን ወይም ወንድሙን በኢባዳ ላይ ላያግዘው ይችላል፡፡ ነገር ግን የሚያግዛት ወይም የምታግዘው ሲያገባ (ስታገባ) ይህን ደረጃ ያገኛሉ፡፡ ካልሆነ አያገኘውም ሚስትም እንደዛው አባሁረይራ በዘገቡት ሀዲስ ረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል “ሰውዬው (ባል) ከሌሊቱ ክፍለ ጊዜ ተነስቶ ለራሱ ሰግዶ ሚስቱንም የቀሰቀሰ እንደሆነ እምቢም ካለች ውሃ ረጭቶ ከቀሰቀሳት አላህ ይዘንለት፡፡ ሚስትም ለራሷ ተነስታ ሰግዳ እሱንም የቀሰቀሰች እምቢም ካለ ውሃ ረጭታ የቀሰቀሰችው ከሆነ አላህ ይዘንላት” ይህ እንግዲህ የትዳር አጋሩን አላህን በመታዘዝ ላይ ለሚረዳ ሰው ከመልዕክተኛው የተደረገለት ዱዓ ነው፡፡ ከኛ መሀል ከወንድሞቻችን በሌለበት ዱዓ አርግልኝ የሚል ሰው ብዙ ነው ከአላህ መልዕክተኛ ሲሆን ግሩም ነው በእርግጥ ከሳቸው በላይ ዱዓ ሊያደርግልን የምንፈልገው ሰው ያለ አይመስለኝም፡፡
🔸ልጆችን ገርቶ የማሣደግ አጅር
ይህ አጅር አግብቶ ላልወለደ ሰው አይገኝም “የረሱሉን አዝወትሮ በመጠባበቅ የሚታወቅ አለም ነበር፡፡ እንዲህ ይል ነበር ከረሱሉ ሱና አንዱ አምልጦኛል እሳቸው ከሀሰንና ሁሴን ጋር ይጫወቱ ነበር በጀርባቸውም ያስጋልቧቸዋል እኔ ልጅ አልተሰጠኝምና ይህን ሱና መተግበር ሳልችል ቀረሁ ይል ነበር፡፡ አቢ ሰዒዲኒልኹድሪ እንዳወሩት ረሱሉ(ሰ.ዐ.ወ) እንዲ ብለዋል “ሶስት ሴት ልጆችን በስርዓት አሳድጎ የዳረና ለነርሱ መልካምን የዋለ ሰው (አባትና እናትን የሚመለከት ነው) ለርሱ ጀነት ተገባው (አለለት) “እነዚህን ሴት ልጆች በመልካም ያሳደገና በጎ የዋለላቸው ለሱ ከእሳት ግርዶ ይሆኑለታል የአንድ ሙስሊም የትግሉ ጥግ ከእሳት አምልጦ ጀነት መግባት መሆኑ አይዘነጋም፡፡ እናም አግብቶ የወለዳቸውን በአላህ ህግና ስርዓት አሣድጎ ለቁም ነገር ሲያበቃ ከጀሀነም ግርዶውን አሰናዳ ማለት ነው፡፡
🧕 ሴቶች በተለይ ባልን በመታዘዝ
የምታገኙት አጅር
አንዲት ሴት ከወንጀል በመለስ ያለን የባሏን ትዕዛዝ ስትፈፅም የአላህን ውዴታ ትሸምታለች፡፡ ረሰሉ (ሰ.ዐ.ወ) “የትኛዋም ሴት ባሏ በሷ ረክቶባት (እየተደሰተባት) ከሞተች ጀነት ገባች” አሉ፡፡ በሌላ ዘገባም “አንዲት ሴት አምስት ወቅት ሰላቷን ከሰገደች፣ ወሯን (ረመዳንን) ከፆመች፣ ብልቷን (ከሃራም) ከጠበቀች፣ ባሏን ከታዘዘች የጌታዋን ጀነት ገባች” ብለዋል፡፡ ይቀጥላል…
በኡስታዝ አብዱልገፋር ሸሪፍ
ሚንበር ቲቪ ዘወትር ማክሰኞ
ምሽት 2:30–3:30
ለጎጆዬ

10 Aug, 10:56

6,131

በአላህ ስም እጅግ አዛኝ ሩህሩህ በሆነው
ኢስላም ወደ ጋብቻ ያደረገው ጥሪ
ክፍል(2)
ጋብቻ በቁርአንና በሱና
1. ቁርዓን ስለ ቤተሰብ ህግና ስርዓትን አስመልክቶ በልዩ ትኩረት አስተናግዶታል፡፡ ባጠቃላይ 146 አንቀፆችን ስለቤተሰብ፣ ጋብቻ(ትዳር)፣ ስለ አባት፣ እናት፣ ልጆች፣ አስቤዛ፣ ጡት ማጥባት ወዘተ… ሰፋ ያለ መመሪያ ሰጥቷል፡፡
🔸የአላህ መልዕክተኛ በበርካታ ዘገባዎች ስለዚሁ ጉዳይ በዝርዝር ስለመናገራቸው ተዘግቧል፡፡
🔸የኢስላም የህግ (ፊቅህ) ትምህርት ክፍልም ከጠቅላላው የፊቅህ ዝርዝር ትምህርት 1/5ኛውን በዚህ ርዕሰ-ጉዳይ በማድረግ ጥልቅና ዝርዝር ትንታኔ ተሰጥቶበታል በተለይም ስለ ማጨት፣ ኒካህ፣ የባልና ሚስት መብትና ግዴታዎች የልጆች መብትና ግዴታዎች የፍች ህግና ተያያዥ ስነ ስርዓቶች፣ የገንዘብ አያያዝና የአስቤዛ ጉዳይ የውርስ ክፍፍል ጉዳይ በዝርዝርና በተደራጀ መልኩ ተሰርቷል፡፡
🔸የዚህ ሁሉ የእውቀት ክምችት በዚህ ጉዳይ ላይ መኖሩ ባጠቃላይ ኢስላም ለቤተሰብ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ሚያሣይ ነው፡፡
🔸ጋብቻ ምን ያህል ክቡርና ቅዱስ መሆኑን ከማስገንዘቡም በላይ እንዴት የተበረታታ መልካም ባህል (ነገር) መሆኑንም ያስረዳናል፡፡
2. ሌላው ኢስላም ለተጋቢዎች በርካታ ሽልማቶችን (አጅር) ያዘጋጀበት ስረአትም ሳቢ ነው፡፡
🔸በሸሪዓችን የሚፈፀሙ በርካታ ተግባራት በጥንዶች (ባለትዳሮች) እንጂ አይፈፀሙም፡፡አጅራቸውም ለነሱ እንጂ ለላጤዎች አይገኝም ስለሆነም ላጤዎቻችን (ወጣቶቻችን) ቀጥሎ የተዘረዘሩትን አጅሮች ባያገኙም ኢንሻአላህ ሌሎች የኸይር ደጃፎችን እንደማያጡ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ባለትዳሮችን የሚጠብቃቸውን አጅር በከፊልም ቢሆን እንመልከት
🤔 ሚስትንና ልጆችን መቀለብ
ይህ ለባለትዳሮች ብቻ የተገራ ኸይር ነው፡፡ “አንድ ብር በአላህ መንገድ ላይ ብታመጣ፣አንድ ብር ባሪያ ነፃ ለማውጣት ብታወጣ፣አንድ ዲናር ለሚስኪን ሰደቃ ብትሰጠው፣አንድ ብር ለቤተሶበችህ ብትሰጥ፡- በአጅር በላጩ በቤተሰብህ ላይ ያወጣኸው ብር ነው፡፡
🤔ለሚስትህና ልጆችህ ወጭ የምታደርገው ገንዘብ ግዴታና አጅሩም ከሁሉም በላይ እንደሆነ እንረዳለን ነገሩ ጂሃድ ላይ የሚወጣ ቢሆን እንኳ ጂሃዱን በገንዘብ መደገፍ በግለሰብ ላይ ሱና በመሆኑ ረሱሉ(ሰ.ዐ.ወ) “አንድ ሰው ለቤተሰቦቹ ወጪ ሲያደርግ ከአላህ ምንዳን አገኝበታለሁ ብሎ እያሰበ ከሆነ አላህ ዘንድ ወጪው ሰደቃ ተብሎ ይመዘገብለታል! ብለዋል፡፡
🤔ለልጆችህ ባለቤትህ ወጭ በምታደርግበት ጊዜ ይህንን ኒያ (ስሜት) በውስጥ ካኖርክ በአላህ ፈቃድ አጅርህ ተመዝግቦ መቀመጡ አይቀርም፡፡
🤔ትንሽ ቅሬታ በገባህ ቁጥርም ሃላፊነትህን ባለመወጣት (ወጭ በመቁረጥ) ቤተሰቦችህን አታንገላታም፡፡
🤔አጅሩን ካአላህ በመጠበቅ ባለቤትህ ምንም ያህል የሚያስከፋ ነገር ብታደርግም የጋብቻው ሰንሰለት እስካለ ድረስ በርሃብና ችግር አትቀጣም። 🤔ሚስትም የቤቷን ጉዳይ በመጠበቋና በስርዓት በማስተዳደሯ ምንዳን ከአላህ ትከጅላለች፡፡ይቀጥላል…
በኡሰታዝ አብዱልገፋር ሸሪፍ
ሚንበር ቲቪ ዘወትር ማክሰኞ
ምሽት 2:30–3:30
ለጎጆዬ

08 Aug, 15:42

6,349

ሊንኩን ሼር በማድረግ ተደራሽ ያድርጉ!

ለጎጆዬ ፕሮግራም ላይ የቀረቡ ሃሳቦችን እዚህ ይከታተሉ!

https://t.me/legojoye_minbertv
ለጎጆዬ

08 Aug, 14:35

6,188

በአላህ ስም እጅግ አዛኝ ሩህሩህ በሆነው
ኢስላም ወደ ጋብቻ ያደረገው ጥሪ
ክፍል(1)
መግቢያ
🔸ጋብቻ በኢስላም መለኮታዊ ስረአት ነቢያዊ ፈለግና ሰዋዊ ባህሪ ነው። ህይወት በሙስሊሞች ቤት ምሉእ የሆነ ኢባዳ (አምልኮ)፤ የነቢያትን ሱና (ፈለግ) ህያው ማድረጊያ ስፍራና የማያቋርጥ የስልጠና ማእከል ነው፡፡
🔸የአላህ ፍላጎቱና ውሳኔው ሆኖ ሰዎች በምድር ላይ ስንኖር በሴትና ወንድ የጋብቻ ጥምረት ውስጥ እንዲሆን ተደረገ፡፡ የመጀመሪያው የሰው ዘር መቀጠያ ምክንያትም የአባታችን አደምና የእናታችን ሀዋ ቤተሰብ ምስረታ ሆነ። በውስጡ በርካታ ታአምራትን የያዘው ይህ ቤተሰብ በአላህ ምስክርነት ሶስት ትላልቅ መገለጫዎችን ይዞ ይገኛል፡፡
ሰኪና መወዳና ራህማ
🔸የአላህን መኖርም ለሚጠራጠርም ሰው አይነተኛ ምልክትና ታአምር ሆኗል፡፡ ወሚን አያቲሂ፣ ለእናንተም ከነፍሶቻችሁ (ከጎሶቻችሁ) ሚስቶችን ወደ እነሱ ትረኩ ዘንድ መፍጠሩ፤ በመካከላችሁም ፍቅርንና እዝነትን ማድረጉ ከአስደናቂ ምልክቶቹ ነው።
🔸በዚህ ውስጥ ለሚያስተውሉ ህዝቦች ወሁለዚ…እርሱም ያ ከውሃ ሰውን የፈጠረ የዝምድናና አማችም ባለቤት ያደረገው ነው።ጌታህም ቻይ ነው፡፡
🔸ህጋዊው ጋብቻ ወንድና ሴት ለብቻቸው የሚኖሩበትና ተፈጥሯዊ ስሜትን ለማርካት ብቸኛው አማራጭ ነው። በኢስላም ከዚህ ውጭ ሁሉም መንገዶች ጥፋትና ርክሰትን የሚያስከትሉ አመጾች ናቸው።ከአላህ ጋርም ያራርቃሉ። ስለሆነም ቤተሰብ መመስረት የዲን አካል ነው።
🔸ለቤተሰብ ጥበቃና ከለላ ማድረግ ከኢማን ነው።ቤተሰብን ለማፍረስና ከነጭራሹ ለማጥፋት ከዘመቱ በርካታ ፈተናዎችና መከራዎች ጋር መታገል ጂሃድ ነው።የጋብቻ ፍሬ የሆኑ ልጆችን መንከባከብና መጠበቅ የአላህን የሀይማኖት ምልክቶችን (ታእዚም ሸዓኢረላህ) ከማክበርነው።
ያ አዩሀለዚነ…እናንተ የመናችሁ ሆይ፤ ነፍሶቻችሁንና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ደንጋዮች ከሆነች እሳት ጠብቁ…አንድ ሙስሊም ቤተሰብ ከዝግጅት እስከ ምሰረታው ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጠው ከዚያም አላህ ያኖረውን ኢስላማዊ ስርዓት ለመተግበር ከተቻለ እንደ አላማ ያስቀመጥነው አርአያ የሆነ ሙስሊም ማህበረሰብ ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ ውጤቱም ፍቅር ፤ሰላም፤ ህብረት፤ መተሳሰብና መደጋገፍ፤ ጨዋነትና (ንጽህና) ባጠቃላይ መልካም ስነምግባር የጎላበት ስረአት ይፈጠራል፡፡
🔸ለዚህ ነው አላህ የቤተሰብን ስርዓት የዘረጋበትን መንገድ በአንክሮ እንናስተውል ዘንድ ይህ ርእስ የተዘጋጀው፡፡
🔸ከዚህ ቀጥሎ እንደመግቢያ ካነሳነው ሀሳብ በላይ ገባ ብለን ኢስላም ለቤተሰብ ምስረታ (ጋብቻ) የሰጠውን ቦታ (ትኩረት) እንመልከት።ይቀጥላል…
በኡስታዝ አብዱልገፋር ሸሪፍ
ሚንበር ቲቪ ዘወትር ማክሰኞ
ምሽት 2:30–3:30