Latest Posts from ሐዲስ በአማርኛ (@hadithamharic) on Telegram

ሐዲስ በአማርኛ Telegram Posts

ሐዲስ በአማርኛ
📚ይህ እለታዊ ሶሒሕ የሆኑ ሐዲሶች የሚለቀቁበት ቻናል ነው።

አስተያየት ወይም መልእክት ካለዎት በ @HadithAmharic_bot ይላኩ።
2,364 Subscribers
44 Photos
230 Videos
Last Updated 11.03.2025 02:04

Similar Channels

Abdullah Ali Jaber
12,865 Subscribers
DAILY COMBO Airdrop
5,930 Subscribers
Ethio GSM
1,543 Subscribers

The latest content shared by ሐዲስ በአማርኛ on Telegram

ሐዲስ በአማርኛ

06 Mar, 20:12

260

🕋የጁሙዐ ቀን ሱናዎች🕌

1-ነቢዩ(صلى الله عليه وسلم)ላይ ሶለዋት ማውረድን ማብዛት

2- 📖 ሱረቱ–ከህፍን መቅራት

3-🚿 ሸዋር መውሰድ

4-👚 ካለው ሻል ያለውን ልብስ መልበስ

5-🦷ሚስዋክ መጠቀም(ጥርስን መፋቅ)

6-🌹 ሽቶ መቀባት

7-🌅 ወደ መስጂድ አበክሮ መሄድ

8- ወደ መስጅድ በግር መሄድ

9-📿 ከጁሙዐ ሶላት ቡሃላ 4 ረከዓ(2+2) መስገድ

10- ዱዓ ተቀባይነት ያላትን ሰዓት መጠባበቅ

🔖ሐዲስ በአማርኛ:
ሐዲስ በአማርኛ

28 Feb, 20:09

978

🏞 ጾምን የሚያበላሹ ነገሮች 🌆

1⃣ መብላት እና መጠጣት:-

🧠 ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ጾሙ አይበላሽም።

2⃣ ምግብን እና መጠጥን የሚተኩ ነገሮች:-

💉 ምግብ ነክ መርፌ እና መድሓኒቶች ጾምን ያፈርሳሉ።

🩸ለህመምተኛ የሚሰጥ ደም ጾምን ያፈርሳል።

3⃣ የግብረ-ስጋ ግንኙነት መፈፀም:-

🔵 የፍቶት ጠብታ(መንይ) ቢፈስም ባይፈስምየግብረ-ስጋ ግንኙነት ጾም ያበላሻል።

4⃣ የፍቶት ጠብታን በፍላጎት እና ምርጫ ማፍሰስ(ኢስቲምናእ):-

በመተሻሸት፣በእጅ፣ ደጋግሞ በመመልከት፣ በመሳም.. ወዘተ ከፈሰሰ ጾም ያበላሻል።

💤 በእንቅልፍ ልብ የሚከሰት የዘር ፍሬ መፍሰስ(ኢሕቲላም) ጾም አያበላሽም።

5⃣ አውቆ ማስታወክ:-

🥛ከቁጥጥር ውጭ በራሱ ከወጣ ጾም አያበላሽም።

6⃣ የወር አበባ እና የወሊድ ደም መፍሰስ:-

🩺 ከተለመደው የወር አበባ ቀን ውጭ በበሽታ ምክንያት የሚፈስ ደም(ኢስቲሓዷ) ጾም አያበላሽም።


💡 ከሰውነት ደም ማውጣትን መተው የተመረጠ ነው:-

🆎 ለዋግምት ወይም ደም ለመለገስ ደም ማውጣት ለሊት ማድረጉ ይመረጣል።

🩸ለህክምና ምርመራ ናሙና፣ ነስር፣ ቁስል እና ጥርስ በመንቀል የሚፈስ ደም ምንም ችግር የለውም።

https://T.me/HadithAmharic

🔈ለሌሎችም ያስተላልፉ
ሐዲስ በአማርኛ

23 Aug, 07:56

1,864

عن عبدالله بن عمر وأبي هريرة رضي الله عنهم أنهما سمِعا رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول على أعوادِ مِنبَره:

[ لَيَنْتَهِيَنَّ أَقْوَامٌ عَنْ وَدْعِهِمُ الجمُعَاتِ أَوْ لَيَخْتِمَنَّ الله على قُلُوبِهمْ ،ثُمَّ ليَكُونُنَّ مِنَ الغَافِلينَ]

📚رواه مسلم

🌸«::::::::::::::::» «:::::::::::::::»🌸

ከዐብደላህ ቢን ዑመር እና አቢ-ሁረይረህ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው የአላህ መልዕክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የሚንበራቸው እንጨት ላይ ቆመው እንዲህ ሲሉ ሰምተናል አሉ:-

[ሕዝቦች የጁመዐ ሶላቶችን ከመተው ይከልከሉ። አለዚያ አላህ ልቦቻቸው ላይ ያትምባቸዋል። ከዛም (አላህን ባለማውሳት) ከዘንጊዎች ይሆናሉ።]

📚ሙስሊም ዘግበውታል።

🔖ሐዲስ በአማርኛ:-

Telegram: https://t.me/HadithAmharic
Instagram:https://instagram.com/HadithAmharic
FB: fb.com/HadithAmharic
ሐዲስ በአማርኛ

08 Aug, 20:22

1,862

قَالَ رَسُولُ اللهِ ﷺ

[ إِذَا صَلَّى أَحَدُكُمُ الْجُمُعَةَ فَلْيُصَلِّ بَعْدَهَا أَرْبَعًا ]

📚رواه مسلم.

🌸«::::::::::::» «:::::::::::»🌸


የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–

(አንዳችሁ የጁሙዐ ሶላትን በሰገደ ጊዜ ከሱ ቡኃላ (ሱና) አራት ረከዐ ይስገድ።)

📚ሙስሊም ዘግበውታል።



https://T.me/HadithAmharic
ሐዲስ በአማርኛ

18 Jul, 19:29

2,108

🕋የጁሙዐ ቀን ሱናዎች🕌

1-ነቢዩ(صلى الله عليه وسلم)ላይ ሶለዋት ማውረድን ማብዛት

2- 📖 ሱረቱ–ከህፍን መቅራት

3-🚿 ሸዋር መውሰድ

4-👚 ካለው ሻል ያለውን ልብስ መልበስ

5-🦷ሚስዋክ መጠቀም(ጥርስን መፋቅ)

6-🌹 ሽቶ መቀባት

7-🌅 ወደ መስጂድ አበክሮ መሄድ

8- ወደ መስጅድ በግር መሄድ

9-📿 ከጁሙዐ ሶላት ቡሃላ 4 ረከዓ(2+2) መስገድ

10- ዱዓ ተቀባይነት ያላትን ሰዓት መጠባበቅ

🔖ሐዲስ በአማርኛ:
ሐዲስ በአማርኛ

13 Jul, 15:29

1,506

عَنْ أَبِي قَتَادَةَ رضي الله عنه ، قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم:

[ صِيَامُ يَوْمِ عَاشُورَاءَ أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ ]
            
                   📚رواهُ مسلم 

             🌸«::::::::::::::::::»
«:::::::::::::::::»🌸

ከአቢ-ቀታዳ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው የአላህ መልዕክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም)  እንዲህ  አሉ:-

[ የዐሹራን ቀን መጾም ከርሱ በፊት (ያለፈውን) አመት   ወንጀል ያስሰርዛል  ብዬ  ከአሏህ  እከጅላለሁ። ]

         📚ሙስሊም ዘግበውታል።

●የሙሐረም ወር 10ኛው ቀን እለተ ዐሹራእ በመባል ይታወቃል።

የዘንድሮ (የ1446 ዓ.ሂ) ዐሹራእ የሚሆነው የፊታችን ማክሰኞ  ሐምሌ 9/2016 ነው:: ከፊቱ ወይም ከኋላ መጾም ተገቢ ነው።

🤲አላህ ይወፍቀን

🔖ሐዲስ በአማርኛ:

Telegram: t.me/HadithAmharic
Instagram: instagram.com/HadithAmharic
FB: fb.com/HadithAmharic
ሐዲስ በአማርኛ

07 Jul, 19:26

1,376

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ :           
  قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّم

" أَفْضَلُ الصِّيَامِ بَعْدَ رَمَضَانَ شَهْرُ اللَّهِ الْمُحَرَّمُ
وأفضل الصلاة بعد الفريضة صلاة الليل "

                        📚 رواه مسلم

               🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸

የአላህ መልዕክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡-

“ከረመዷን በኋላ በላጩ ጾም የአላህ ወር ሙሐረም ነው፣ ከግዴታ ሶላት በኋላ በላጩ ሶላት የሌሊት ሶላት ነው።”

                       📚[ሙስሊም ዘግበውታል።]
ሐዲስ በአማርኛ

16 Jun, 03:55

1,442

كل عام وأنتم بخير
تقبل الله منا ومنكم
وعيدكم مبارك
ሐዲስ በአማርኛ

14 Jun, 17:49

1,553

عن أبي قتادة الأنصاريِّ رضي الله عنه أن النبي صلى الله عليه وسلم قال:-

[ صِيَامُ يَوْمِ عَرَفَةَ أَحْتَسِبُ عَلَى الله أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلهُ وَالسَّنَةَ الَّتِي بَعْدَهُ ]

                  📚 رواه مسلم

               🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸

ከአቢ-ቀታዳ አል-አንሷሪ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:-

[የዐረፋን ቀን መጾም ከርሱ በፊት (ያለፈውን) አመት እና ከርሱ ቡሃላ(የሚቀጥለውን) አመት ወንጀል ያስሰርዛል ብዬ ከአሏህ እከጅላለሁ።]

          📚ሙስሊም ዘግበውታል።


📆 የዐረፋ ቀን(ዙልሒጃ  9ኛው) ነገ ነው።


🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram:  https://t.me/HadithAmharic
Instagram: https://instagram.com/HadithAmharic
ሐዲስ በአማርኛ

06 Jun, 14:34

1,406

አስሩን የዙልሒጃ  ቀናት እንዴት እናሳልፍቻው?

1-እውነተኛ  ተውበት ማድረግ

እነዚህንም ሆነ  ሌሎች የዒባዳ ቀናትን ለመቀበል ከሰራናቸው ወንጀሎች በመጸጸት ወደ አላህ መመለስ አለብን። አላህ እንዲ ብሏል:-

{ ምእምናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ።﴿ [ሱረ አል-ኑር፣31]

2- ቀኖቹን በአግባቡ ለመጠቀም ቁርጠኛ  መሆን

በዙልሒጃ 10 ቀናት  ውስጥ ልዩ ትኩረት ሰጥተን አላህ በደነገጋቸው ኢባዳዎች ለማሳለፍ ከወዲሁ ራስን እና ያግዘናል ያልነውን ነገሮች በሙሉ ማዘጋጀ ተገቢ ነው።

አላህ እንዲ ብሏል:- {እነዚያም በኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፤ አላህም በእርግጥ ክበጎ ሠሪዎች ጋር ነው።﴿[ሱረቱ አል-ዐንከቡት፣69]

3- ከወንጀል መራቅ

የአላህን  ተእዛዛት መፈጸም ወደርሱ እንደሚያቃርብ ሁሉ የከለከላቸውን እና እርም ያደረጋቸውን ነገሮች መዳፈር ከርሱ መራቅን እና ከእዝነቱ ለመባረር ምክንያቶች ናቸው።

🕋 አስሩ የዙልሒጃ ቀናት ያላቸው ደረጃ

1-አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ  በነዚህ  ቀናት ምሏል

አላህ በሆነ  ነገር ሲምል የዛን ነገር ትልቅነት እና  ደረጃ ያመለክታል፤ አላህ በትልቅ ነገር እንጅ አይምልም። አላህ እንዲህ ብሏል:-

﴾በጎህ እምላለሁ።በዐሥር ሌሊቶችም።﴿
[አል-ፈጅር፣1-2]
ኢብን ከሢርን ጨምሮ አብዛኞች ሙፈሲሮች እንዳሉት ‘አስሩ ሌሊቶች’ የዙልሒጃ  የመጀመሪያዎቹ ናቸው።

2-አላህ በርሱ ውስጥ እሱን ማውሳትን የደነገገባት “የታወቁ ቀናት” መሆናቸው።

አላህ እንዲህ ብሏል:-
﴾በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከማለዳ እንሰሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ፣ (ይመጡሃል)﴿
[አል-ሐጅ፣28]
ኢብን ዐባስ እንዳሉት የታወቁ ቀኖች የተባሉት የዙሒጃ የመጀመሪያዎቹ አስሩ ቀኖች ናቸው።

3- ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከዱንያ ቀኖች በላጭ መሆኗን ተናግረዋል

ከዐብደላህ ቢን ዐባስ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው ነቢዩ( ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:-
[ከነዚህ አስርት(ከዙልሒጃ  የመጀመሪያዎቹ) ቀናት ይበልጥ አላህ ዘንድ በውስጣቸው የሚሰሩ መልካም ስራዎች ተወዳጅ የሚሆኑበት ቀን የለም።] ብለው ሲናገሩ ሶሐቦች፡- ”የአላህ መልእክተኛ ሆ! በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን?“ በማለት ጠየቁ፤ ነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም):- [ (አዎን!)ነፍሱንና ንብረቱን ይዞ የወጣ፣ ከዚያም አንዱንም ይዞ ያልተመለሰ ሰው ካልሆነ በስተቀር፣ በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን(አይበልጥም።)] አሉ። (አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።)



4- በአስሩ ቀናት ውስጥ የዐረፋ ቀን አለ።

ዐረፋ ከዙልሒጃ የዘጠነኛው ቀን ነው። አላህ ﴾ ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ። ለናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ﴿የሚለውን አያህ ያወረደበት፣ወንጀሎች የሚማሩበት፣ የአላህ ባሮች ከእሳት ነጻ የሚባሉበት ቀን ነው።

5- በአስሩ ቀናት ውስጥ የእርድ ቀን (ዒደል-አድሐ) አለ።

የዙሒጃ አስረኛው የውመነሕር(የእርድ ቀን)የዒድ ቀን  ነው። ከቀናቶች ሁሉ ታላቅ ቀን ነው። ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:-(አላህ ዘንድ ከቀናት ሁሉ ትልቁ የእርዱ(ዒደል-አድሐ) ቀን ነው።(አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።)

6-ዋና ዋና የዒባዳ አይነቶች በነዚህ ቀናት ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ።

ኢብን ሐጀር(አላህ ይዘንላቸው እና) እንዲህ አሉ:- “የዙልሒጃ  አስሩ ቀናት ልዩ የሆኑበት ምክንያት ዋና ዋና የአምልኮ አይነቶች እነሱም:ሶላት፣ ጾም፣ ሶደቃ እና ሐጅ በውስጧ  ስለተሰበሰቡ ነው። ይህ(ስብስብ) በሌሎቹ ውስጥ አይገኝም።”

🕋በአስሩ የዙልሒጃ  ቀናት ውስጥ ከሚሰሩ ታላላቅ ዒባዳዎች:- ሐጅ እና ዑምራ፣ ጾም፣ ሶላት፣ ዚክር እና ደቃ ማብዛት ይገኙበታል።



🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram: t.me/HadithAmharic
Instagram: instagram.com/HadithAmharic
FB: fb.com/HadithAmharic