ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞ @fenote_abew Channel on Telegram

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

@fenote_abew


"አባቶችን ጠይቅ ይነግሩሀል፤የእምነትን ምስጢር ያስረዱሀል
አትለፍ የተዋህዶን ድንበር፤ በውጪ ተጥለህ እንዳቀር"

◈ ይህ ቻናል :- የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ስርዓት እና አስተምሮ የ ጠበቁ ወቅታዊ እና አስተማሪ ፤መንፈሳዊ ፅሁፎች የሚቀርቡበት ኦርቶዶክሳዊ ቻናል ነው።
ሀሳብ አስተያየት ካሎት በተጨማሪም ለpromotion

👉 @fenote_Abew_bot

https://t.me/fenote_abew

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞ (Amharic)

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞ ማን ነው? ወደ ምን እንደሚታወቅ ትልቅ ስጦታ እንዲያለብሱ መዋሸት የሚሆነው ከሄኖታችን ዘርፉለሁበት ኦርቶዶክሳዊ ቻናል ነው። አባቶችን ጠይቅ ይነግሩሀል፤ የእምነትን ምስጢር ያስረዱሀል፤ አትለፍ የተዋህዶን ድንበር፤ በውጪ ተጥለህ እንዳቀር። ይህ ስጦታ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ስርዓት እና አስተምሮ የ ጠበቁ ወቅታዊ እና አስተማሪ ፤መንፈሳዊ ፅሁፎች የሚቀርቡበት ኦርቶዶክሳዊ ቻናል ነው። ከመለስ የሚቀረው @fenote_Abew_bot ይጠቀሙ። የቴሌግራም ገንዘብ በእኚኅ ላሉበት ላይ ትክክለኛ መንነት ሳታበርበን የሚያስቡበት ቻናል ነው።

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

25 Jan, 12:07


✥✥✥ዝርወተ ዐጽሙ ለማር ጊዮርጊስ✥✥✥

✥    ጥር ፲፰ ዕለት ለሰማዕቱ "ዝርወተ አጽሙ " ትባላለች:: በቁሙ አጥንቱ የተበተነበት እንደ ማለት ነው።

" ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም ናቁ ስለ መንግሥተ ሠማያትም መራራ ሞትን ታገሡ። " እንደተባለ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዘመናት በብዙ ስቃያት ሲያስጨንቁት ኖረው በጽናቱ አሸነፋቸው:: 70 ነገሥታትን ከነ ሠራዊታቸው ከማሳፈሩ ባሻገርም በርካታ (በመቶ ሺ የሚቆጠሩ) አሕዛብን ማርኮ ለሰማዕትነት አበቃ::

✥    በዚህ የተበሳጨ ዱድያኖስም ኮከበ ፋርስ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲቆራርጡት አዘዘ:: ወታደሮቹም ቅዱሱን ቆራርጠው በብረት ምጣድ ላይ ጠበሱት። ያለ ርሕራሔም አካሉን ኣሳረሩት። ቀጥለውም ፈጭተው ዐመድ አደረጉት። በኣካባቢው ወደ ነበረው ትልቅ ተራራ ጫፍ (ደብረ ይድራስ) ወጥተውም በነፋስ በተኑት:: “ሐረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ዓመድ” እንዲል:: (ምቅናይ)

✥     እነርሱ ይህንን ፈጽመው ዘወር ሲሉ ግን የቅዱሱ ዐጽም ባረፈባቸው ዛፎች: ቅጠሎችና ድንጋዮች ሁሉ “ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት” የሚል ጽሑፍ ተገኘ:: ስለዚህም ይህቺ ዕለት ቅዱሱ አለቅነትን የተሾመባት ናት ማለት ነው:: ወዲያው ግን ኃያል ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተበተነበት ተነስቶ ወታደሮችን አገኛቸውና “በክርስቶስ እመኑ” ብሎ አስደንቆ ወደ ሕይወት መራቸው፣ ፸ ው ነገሥታት ግን አፈሩ። ሰማዕቱ አባታችን እኛንም በሃይማኖት በምግባር ያጽናን ተራዳኢነቱም አይለየን አሜን። 🙏

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

20 Jan, 18:22


✝️ ታቦት በሄደበት አይመለስም

ታቦት በሄደበት አይመለስ ብለው ያወጁት አፄ ዘርዓ ያዕቆብ እንደሆኑ ይነገራል
ለዚህም ምክንያት የሆነው ታቦት የሚወጣው ለመባረክ ለመቀደስ በመሆኑ በሄደበት ከሚመለስ በሌላ መንገድ ተመልሶ ያልባረከውን እንዲባርክ በማሰብ ነው (ነገር ግን መመለሻ የሚሆን ሌላ መንገድ ከሌለ በሄደበት ይመለሳል) ።

እውነት ነው በዚህ የጥምቀት በዐል  " የእግዚአብሔር ታቦት የገባበት ስፍራ ቅዱስ ነውና " 2ዜና 8፥11 ተብሎ እንደተነገረው ታቦት የሚሄደበት ቦታ እና የሚያርፍበትን ስፍራ ሁሉ የኢትዮጵያን ምድር እንደሚቀድስ እና ከሀገሪቱ ላይ ወረርሽኝ ... አጋንንትን እና የእነርሱን አሠራር ሁሉ እንደሚያርቅላት እናምናለን ።

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

14 Jan, 05:42


✧°༺༻°✧ የጥር 6 ግዝረትና በዓላት ✧°༺༻°✧

ግዝረት ከጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው፡፡ በተጨማሪም ይህ ቀን ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ዕረገተ ኤልያስ፤ ዕረፍተ ኖኅ፤ ልደተ ቅድስት አርሴማ፤ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፤ አቡነ ኖኅ አባ ሙሴ ገዳማዊ፤ አባ ወርክያኖስ እና ወአባ ሙሴን በዓላት ታከብራለች፡፡

ከእናቱና ከደቀመዛሙርቱ ጋር በሰርግ ቤት የተገኙበት ቃና ዘገሊላ፣ በአርባ ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበትና አረጋዊ ስምዖንን የሰላሳ ዓመት ጎልማሳ የሆነበት “ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ ዐይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና” በማለት የተናገረበት ልደተ ስምዖን ከንዑሳን በዓላት ይመደባሉ፡፡ ክብር ምስጋና ይድረሰውና የጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ግዝረት በየዓመቱ ጥር ፮ ቀን ይውላል።

ልሳነ ዕፍረት ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋው ግዝረትን ተቀበለ፡፡ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ፤›› በማለት እንደ ተናገረው [ሮሜ.፲፭፥፰]፣ የክብር ባለቤት መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ ፈጽሟል፡፡ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ ስሙም ገና በሥጋ ሳይፀነስ የእግዚአብሔር መልአክ ባወጣለት ስም ‹‹ኢየሱስ›› ተብሎ ተጠራ  [ሉቃ.፪፥፳፩-፳፬]፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ [ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ]፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም አረጋዊው ዮሴፍን ‹‹እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንድንሰይመው ብልህ የኾነ ገራዥ ሰው አምጣልኝ፤›› አለችው፡፡ ጻድቁ ዮሴፍም እንዳዘዘችው የሚገርዝ ባለሙያ ይዞ መጣ፡፡ ባለሙያውም በእናቱ በንጽሕት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ ሕፃኑ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ባየው ጊዜ ‹‹እንድገርዘው በጥንቃቄ ያዙት›› አላቸው፡፡ ጌታ ኢየሱስም ‹‹ባለሙያ ገራዥ ሆይ! ደሜ ሳይፈስ ልትገርዘኝ ትችላለህን? በዕለተ ዓርብ በመስቀል ስሰቀል ካልኾነ በስተቀር ደሜ አይፈስምና፡፡ ጐኔን በጦር ሲወጉኝ ያን ጊዜ ውኀና ደም ይፈሳል፡፡ ይኸውም ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆቹ መድኀኒት ይኾናል፤›› አለው፡፡

የክብር ባለቤት ጌታችን የተናገረውን ይህን ቃል ባለሙያው በሰማ ጊዜም አደነቀ፡፡ ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሣና ከጌታችን እግር በታች ወድቆ ሰገደ፡፡ ያንጊዜም ምላጮቹ በእጁ ላይ እንዳሉ እንደ ውኀ ቀለጡ፡፡ ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንም ‹‹ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ፡፡ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ ይህ ልጅሽ ስለ እርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው፤›› አላት፡፡

ጌታችንም ባለሙያውን ‹‹እኔ ነኝ! ትገዝረኛለህን ወይስ ተውክ? ወይስ የአባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ ላድርግ?›› አለው፡፡ ባለሙያውም መልሶ ‹‹የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው?›› ሲል ጠየቀው፡፡ ጌታችንም አብርሃም፣ ይስሐቅ፣ ያዕቆብ የሕዝቡ ዅሉ አባት እንደ ኾኑ ካስገነዘበው በኋላ ‹‹ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጣቸው›› በማለት የግዝረትን ሕግ አስረዳው፡፡ ባለሙያውም ይህን ምሥጢር ሲሰማ ‹‹እኔ ከአንተ ጋር እነጋገር ዘንድ አልችልም፡፡ በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና፤›› ብሎ የኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት መሰከረ፡፡

በዚህ ጊዜ ጌታችን ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ ‹‹አባት ሆይ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሃቸው፤ ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ›› አለ፡፡ ያንጊዜም ያለ ሰው እጅ በጌታችን ላይ ግዝረት ተገለጠ (የግዝረት ምልክት ታየ)፡፡ ከዚህ ላይ ጌታችን ወደ አባቱ ወደ እግዚአብሔር አብ ልመና ማድረሱ የለበሰው ሥጋ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ መኾኑንና ጸሎት ማቅረብ የሚስማማው ሥጋን መልበሱን ለማጠየቅ ነው እንጂ በእርሱና በአብ መካከል ልዩነት ኖሮ አይደለም፡፡

ጌታችን ድንግልናዋን ሳያጠፋ ከድንግል ማኅፀን እንደ መውጣቱ ግዝረቱም አይመረመርም፡፡ በተዘጋ ቤት ወደ ሐዋርያት እንደ ገባና እንደ ወጣ ዅሉ እርሱ በሚያውቀው ረቂቅ ጥበብ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቈረጥ፣ ምንም ደም ሳይፈሰው መገረዙ ተገለጠ፡፡

ገራዡም የጌታችንን ቃል ከመስማቱ ባሻገር በሥጋው ላይ የተደረገውን ተአምር ባየ ጊዜ እጅግ አደነቀ፡፡ ከክብር ባለቤት ከጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ወድቆም ሦስት ጊዜ ሰገደና ‹‹በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ!›› በማለት በክርስቶስ አምላክነት አመነ፡፡ ከዚህ በኋላ ያየውንና የሰማውን ዅሉ እየመሰከረ ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡

በዚህች ዕለት ‹‹መሲሑን ሳታይ አትሞትም›› ተብሎ የተነገረለት፤ በንጉሥ በጥሊሞስ መራጭነት መጻሕፍተ ብሉያትን ከዕብራይስጥ ወደ ጽርዕ(ግሪክ) ቋንቋ ከመለሱ ሰባው ሊቃናት አንዱ የኾነውና ትንቢተ ኢሳይያስን ወደ ጽርዕ ቋንቋ የመለሰው ነቢዩ ስምዖን ጌታችንን በታቀፈው ጊዜ ከሽምግልናው ታድሷል፤ የእግዚአብሔርን ማዳን በማየቱና በተደረገለት ድንቅ ተአምር በመደሰቱም ‹‹አቤቱ ባሪያህን ዛሬ አሰናብተው›› እያለ እግዚአብሔርን ተማጽኗል፡፡

በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶም የክርስቶስን የዓለም ቤዛነትና ክርስቶስ በሥጋው በሚቀበለው መከራ እመቤታችን መራራ ኀዘን እንደሚደርስባት፤ እንደዚሁም ጌታችን ለሚያምኑበት ድኅነትን፣ ለሚክዱት ደግሞ ሞትን  የሚያመጣ አምላክ እንደ ኾነ የሚያስገነዝብ ትንቢት ተናግሯል [ሉቃ.፪፥፳፭-፴፭]፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ነቢዪት ሐናም በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝታ የክርስቶስን ሥራ እያደነቀች ቸርነቱን ለሕዝቡ ዅሉ መስክራለች [ሉቃ.፪፥፴፮-፴፱]፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

10 Jan, 20:46


+ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለሱ+

ሰብአ ሰገል ወደ ሄሮድስ ሔደው ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ጠየቁ:: ከዚያም በኮከብ ተመርተው ወደ ክርስቶስ ደረሱ:: ሔደውም ሰገዱለት:: እጅ መንሻም አቀረቡ::

ከዚያ በኋላ ግን "ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ" ማቴ. 2:12

ይህ መልእክት የተነገራቸው ስለ ሁለት ነገር ነው:: የመጀመሪያው ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ስለሚፈልግ ለሄሮድስ መረጃ እንዳይሠጡ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ እየመሰከሩ የመጡበትን መንገድ ትተው አየነው እያሉ በሌላ መንገድ እንዲመሰክሩና የሕፃኑ ንጉሥ ዝና እንዲሰፋ ወንጌል እንዲስፋፋ ነበር::

መልአኩ ወደ ሄሮድስ አትመለሱ አለ እንጂ “ሄሮድስ ሊገድለው ነው" አላላቸውም:: ምክንያቱም ይህን ዜና ቢሰሙ ጦር ይዘው የመጡ ነገሥታት ናቸውና "እኛ እያለን እስቲ ይሞክረን" ብለው ውጊያ ሊያነሡ ይችሉ ነበር:: የሰላም አለቃ የተባለው ህፃኑ ክርስቶስም የውጊያ መነሻ ይሆን ነበር:: ክርስቶስ ግን የምትዋጋለት ሳይሆን የሚዋጋልህ አልፎም የሚወጋልህ አምላክ ነው::

በዚህ መሠረት ሰብአ ሰገል

"ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ።

ወዳጄ ክርስቶስን ሳታገኝ በፊት ሄሮድስ ጋር ብትሔድ ችግር የለውም:: ክርስቶስን ካገኘህ በኋላ ግን ወደ ሄሮድስ መመለስ ኪሳራ ነው:: እንደ ሰብአ ሰገል ለጌታ እጅ መንሻ አቅርበህ ፣ ዘምረህ ፣ የከንፈር መሥዋዕት አቅርበህ ነፍስህ መድኃኒትዋን አግኝታ ከተደሰተች በኋላ ሕይወት እንዴት ይቀጥላል?

ወደ ሄሮድስ ልትመለስ ይሆን? እንዳታደርገው! ሄሮድስ ጋር ያለው ኃጢአት ነው:: ሄሮድስ ጋር ያለው ክፋት ነው:: እመነኝ እንደ ሰብአ ሰገል ጌታህን ካገኘህ ወዲህ ወደ ሄሮድስ አትመለስ!

ወዴት ልሒድ ካልከኝ መልሱ እዚያው ላይ አለ :‐

"በሌላ መንገድ ወደ ሀገራቸው ሔዱ"

እስቲ ሌላ መንገድ ሞክር! ትናንት ያልኖርክበትን ዓይነት ኑሮ ፣ ትናንት ያልሞከርከው የንስሐ መንገድ እስቲ ዛሬ ሒድበት! ሌላ መንገድ አልነግርህም "መንገድም ሕይወትም እውነትም እኔ ነኝ" ያለህ መድኃኔዓለም ክርስቶስ እርሱ ነው:: በእኔ ኑሩ እንዳለ በእርሱ ኑር:: አደራ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለስ!

ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 2 /2017
----------------
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

@fenote_abew

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

07 Jan, 19:42


✥ ልጁን ወለደችው አብን መሰለችው ✥

👉 የተወደዳችሁ አንባብያን እመቤታችን እግዚአብሔር ወልድን የመውለድዋ የእናትነቷ ምሥጢር ከአብ ጋር ያመሳስላታል፡፡ ይህ እንደምንድ ነው ቢሉ ፦

፩–  በቀዳማዊ ልደት አብ ያለ እናት ወልድን ወለደው በድኃራዊ (በሁለተኛ) ልደት ደግሞ እመቤታችን ያለ አባት ጌታን ወልዳለችና በዚህ የአብ ምሳሌው ሆነች፡፡ ስለዚህ ነገር አበው ‹‹ ልደት ቀዳማዊ ተዓውቀ በድኃራዊ ልደት ›› ያሉት አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከእመቤታችን ያለአባት መወለዱ ቅድመ ዓለም ከአብ ያለእናት እንደተወለደ ያስረዳል፡፡ ቅዱስ ዳዊትም ስለዚህ ነገር በዝማሬው ‹‹ እግዚአብሔር በይሁዳ ታወቀ ስሙም በእስራኤል ታላቅ ነው ›› ኣለ ይኸም ከይሁዳ ወገን (በነገድ) ከሆነች ከእመቤታችን ያለኣባት በመወለዱ ከአብ ያለ እናት የመወለዱን ሃይማኖት ተገለጸ ማለት ነው፡፡

፪. አብ የወለደው ወልድን ነው እመቤታችንም ሥግው ቃልን እንጂ የሩቅ ብእሲ እናት ባለመሆኗ አብን መሰለችው፡፡ ስለዚህም እመቤታችንን ወላዲተ አምላክ እንላታለን፡፡

👉 ቅዱስ ያሬድም « ወይቤላ እግዚአብሔር ለማርያም አዝማንየ አዝማንኪ አምጣንየ አምጣንኪ ማርያም ሐቀፍኪዮ ወአነ ዮም ወለድክዎ» ( እግዚአብሔር ማርያምን ዘመኖቼ ዘመኖችሽ መጠኖቼ መጠኖችሽ ናቸው። እኔ ዛሬ ወለድኩት ማርያም ሆይ አንቺ ታቀፍሺው) (ቅ ያሬ ድጓ) « ዘመኖቼ ዘመኖችሽ ናቸው » ማለቱ ዓለም ከመፈጠሩ ዘመን ከመቆጠሩ በፊት በእርሱ ኅሊና መኖሯን የሚያስረዳ ነው። ይህም አዳምን ሳይፈጥረው በፊት እንደሚበድል እና በርስዋም አማካኝነት እንደሚያድነው ያውቅ ነበር ለማለት ነው። ቅዱስ ጳውሎስ « ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳን፥ ንጹሓንና ያለ ነውር በፍቅር ያደረገን ዘንድ ለእርሱ መረጠን » (ኤፌ ፩፥፬) በማለት ዓለም ሳይፈጠር ፍጥረታት ሁሉ በአምላክ የታወቁ መሆናቸውን ገልጾልናል።

፫. ‹‹ እም ኀበ አብ ወጽአ ቃል ዘእንበለ ድካም ወእም ድንግል ተወልደ ዘእንበለ ሕማም ›› (ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ) እንዲል ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ ድካም ሳይሰማው እንደተወለደ አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከድንግል ሕማም ሳይሰማት እርሱም ሕጻናትን የሚሰማው ሳይሰማው ተወልዷል በዚኽም እመብርሃን አብን መሰለችው፡፡

ዛሬ ሴት ስትወልድ ታምጥ የለምን ቢሉ ይህስ አድፈን ለመንጻታችን ምልክት ነው እንላለን፡፡ ቀድሞ በኦሪት 40 ዕለት በምጥ ተጨንቀው የሚቆዩበት ጊዜ ነበር በዚህም የምጥ ጽናት እና ብዛት በጥፍራቸው በጣታቸው ምድርን እስከመቆፈር ይደርሱ ነበር፡፡ ዛሬ በሐዲስ ኪዳን ግን ይህንን መርገም ጌታችን በቸርነቱ ብዛት በመስቀል በፈጸመው ካሳ ኣርቆልናል፡፡ ዛሬ የተወሰነ ምጥ መኖሩ እንዲህ ያለ መከራ ኣበረብን ጌታ ግን ከዚህ ሁሉ ኣዳነን ብለን ለማመስገን እንዲሆነን ነው፡፡ እመቤታችን ግን በዘር ይተላለፍ የነበረ ይህ መርገም ቀድሞውኑ ያልደረሰባት፤ እንደኛም ኣድፋ ኋላ የነጻች ስላልሆነች ጌታን ስትወልደው ምንም ሕማም ጣር ሳይኖርባት ነውና በዚህ ኣብን መሰለችው፡፡

፬. ወልድ ለአብ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው ብቸኛ የበኸር (የበኩር) ልጁ እንደሆነ ለእመቤታችንም ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው ብቸኛ የበኸር ልጇ ነውና በዚህም አብን መሰለችው፡፡ ውልድ ለአብ ብቸኛ እና የበኸር ልጁ ለመሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ ተገልጧል ለምሳሌ፡-ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ በኩሩን ወደ ዓለም ሲያስገባ›› (ዕብ 1፤6) በማለት የበኸር ልጅነቱን ሲገልጥልን ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌል ‹‹ እግዚአብሔርን ያየው ኣንድስ እንኳ የለም በአባቱ እቅፍ ያለው ኣንድ ልጁ ገለጠልን እንጂ ›› ባለው እና ‹‹ አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን ወዷልና ›› (ዮሐ 1፤18/ 3፤17) በማለቱ ብቸኛ ልጁ መሆኑን ገልጦልናል፡፡
ይህማ በመስቀል ስር ከቅዱስ ዮሓንስ በስተቀር ሌላ ወንድ ሰው ቢያጣ ነው እንጂ ልጆችዋ እነስምኦን ፡ ዮሳ… አሉ የሚል ቢኖር እኛም መልሰን አንተ ሰው ‹‹ አንተን በመስቀል ላይ ቢሰቅሉህ እናትህን እና እውነተኛ ባልንጅራህን በመስቀል ሥር ብታይ ያን ባልንጅራህን እባክህን ያጽናኗት ዘንድ ወደ ልጅዎችዋ እና ወደ ባልዋ (ወደ ወንድሞቼ እና ወደ አባቴ) ወስደህ ስጥልኝ ትለዋለህ እንጂ እነሆ እናትህ ብለህ እርሱ እንዲወስዳት ታዘዋለህን? ›› ይኸስ ከልማድ ውጪ ነው፡፡

👉 ለፍጥረትስ ሁሉ ምግባቸውን የሚሰጥ ጌታ ወተት እየመገቡ ያሳደጉን ክቡር ጡቶቿን ፍጡር እንዴት ሊቀርበው ይቻለዋል ‹‹ ስላጠባኸው ጡቶቿ ›› እያሉ ይማጸኑበታል እንጂ፡፡ ቀድሞ በኦሪት ፈጣሪ ሊቀ ነቢያት ሙሴን ሲያዘው ከሰውም ሆነ ከእንስሳት ወገን የእናቱን ማህጸን አስቀድሞ ከፍቶ የሚወጣውን (የሚወለደውን) የእርሱ እንደሆነና እንዲለይለት ኣዞታል፡፡ ዳግመኛም ከሚያገኙት ከኣሥር ኣንድ (አሥራትን) ለፈጣሪ ብቻ እንደሆነ ለሰውም ሆነ ለተለያዩ ጥቅም እንደማያደርጓቸው ሁሉ እመቤታችንም ለእርሱ ለፈጣሪ እናትነት ብቻ የተለየች በመሆኑዋ ሌላ ልጅንም ባለመውለዷ እግዚአብሔር አብን መሰለችው፡፡ (ዘዳ 1፤31)

👉 ስለዚህ ሁሉ ነገር እመቤታችንን ‹‹ አብን ያየንብሽ ›› እያልን እናመሰግናታለን፡፡ ይህንንም ጌታችን ‹‹ እኔን ያየ አብን አይቷል ›› (ዮሓ፲፬ ) በማለቱ ገልጦልናል፡፡ ‹‹እኔን ያየ›› ሲል በመለኮቱ አይደለም መለኮት በሥጋ ድንግል ተገልጦ ቢታይ ዲዳሰስ ነው እንጂ፡፡ ከድንግል የሚታይ የሚዳሰስ ሥጋን ባይነሳ (ገንዘብ ባያደርግ) ኖሮ ባላየነው ባልዳሰስነውም ነበር፡፡ ወልድ በሥጋ ድንግል ተገልጦ ማየታችን ከእርሱ ጋር በሕልውና አንድ የሆነ አብን እንደማየት ነው፡፡ ስለዚህ ጌታችን ‹‹ እኔን ያየ አብን ዓየ›› አለ፡፡ በዚህ ሁሉ ነገር እመብርሃን አብን መሰለችው ለዚህ ታላቅ ክብር በመብቃትዋ ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች መሆንዋ ተገለጠ፡፡ ስለሁሉም ነገር ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን የወላዲተ አምላክ ረድኤት ኣይለየን፡፡ ይቆየን

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

02 Jan, 06:06


አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኃረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው፤ በ፲፩፻፺፯ ዓ.ም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው «አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለው ሥላሴን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ 

ስም ፍስሐ ጽዮን በኋላ ተክለሃይማኖት፤ የተወለዱበት ቀን ታኅሣሥ ፳፬ ፲፩፻፺፯፤ የትውልድ ቦታ ቡልጋ፤ የአባት ስም ጸጋዘአብ፤ የእናት ስም ቅድስት እግዚእ ኃርያ፤ ያረፉበት ነሐሴ ፳፬[1]፤ ንግሥ ነሐሴ ፳፬፤ የሚከበሩት በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በኮፕት ቤተክርስቲያን በየኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥንክሳር።

‹ተክል› ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣ የሚበላ፣ የሚሸተት፣ ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ፤ ሥርዓት ማለት ነው [ማቴ.፲፭፥፲፫]፡፡ ‹ሃይማኖት› ማለት ደግሞ በሀልዎተ እግዚአብሔር፣ እግዚአብሔር የሁሉ አስገኚ መሆኑን፣ በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት፣ በቅዱሳን ተራዳኢነት ማመን አምኖም መመስከር ማለት ሲሆን ‹ተክለ ሃይማኖት› የሚለው ሐረግም የሃይማኖት ተክል፣ ይኸውም የጽድቅ ፍሬን ያፈራ፣ ከኃጢአት ሐሩር ማምለጫ ዛፍ፣ ምእመናንን በቃለ ወንጌል ያጣፈጠ ቅመም፣ መዓዛ ሕይወቱ የሚማርክ፣ ቢመገቡት ረኃበ ነፍስን የሚያስወግድ ቅጠል፣ የጻድቃን መጠለያ ዕፅ የሚል ትርጕም አለው፡፡‹‹ተክለ ሃይማኖት ማለት የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለት ነው›› ሲል የጻድቁን ስም ይተረጕመዋል፡፡

በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በዐሥራ አምስት ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ /ጌርሎስ/ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ በዚህም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

ከዕለታት በአንዱ ቀን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከጓደኞቻቸው ጋር ወደ ዱር አደን ሄደው ሳለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ለኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ መረጣቸው። ስማቸውንም «ተክለ ሃይማኖት» አለው፡፡ ትርጓሜውም በሃይማኖት ፍሬ ማለት ነው፡፡

አባታችንም ሐዋርያዊ ጉዟቸውን ሲጀምሩ
«አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ተውኩልህ . . . ደካማ ለሆንኩ ለእኔ ያለ አንተ የሚያፀናኝ የለም። ለምፍገመገም ለእኔ ያለ አንተ ደጋፊ የለኝም። ለወደቅሁ ለእኔ ያለአንተ የሚያነሳኝ የለም። ለአዘንኩ ለእኔ ያለአንተ የሚያረጋጋኝ የለም። ለድሀው ለእኔ ያለ አንተ መጠጊያ የለኝም፡፡» [ገድለ ተክለ ሃይማኖት ምዕ ፳፰ ቁ ፪ - ፫] ይህን ብለው ትሕትና በተሞላበትና በተሰበረ ልብ ወደ ፈጣሪያቸው ከለመኑ በኋላ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገራት ከኀጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሰዋል፡፡ በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ፀሐይ ተብለዋል፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን ክታቡ ስለ ቅዱሳን መንፈሳዊ ተጋድሎ ሲገልፅ:-
«እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሱ» [ዕብ. ምዕ ፲፩ ቁ ፴፫ ] እንዳለ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖትም በመንፈሳዊ ተጋድሎ እንዲሁም በትህትና በተአምራት አላዊ የነበረውን ንጉሥ ሞቶሎሚን ወደ ክርስትና መልሰዋል፡፡
«ጽድቅን አደረጉ» እንዳለው አባታችን ወንጌልን በተጋድሎ ሕይወታቸው ተርጉመዋል፡፡
«የአንበሶችን አፍ ዘጉ» [ምዕ ፲፩ ቁ ፴፫ /ምዕ ፲፩ ቁ ፴፬] እንዳለው አባታችንም የአውሬውን፥ የዘንዶውን ራስ ቀጥቅጠዋል።
«ከሰይፍ ስለት አመለጡ» እንዳለው አባታችንም ሞቶሎሚ ከወረወረው ጦር በተአምራት ድነዋል፡፡
«ከድካማቸው በረቱ» እንዳለው አባታችንም ያለ ዕረፍት በብዙ ተጋድሎ በጾምና በስግደት በብዙ መከራ በርትተዋል፡፡
ይህን ሁሉ ገድልና ትሩፋት እየፈጸሙ ዕረፍታቸውም በደረሰ ጊዜ ደቀመዝሙሮቻቸውን «ልጆቼ ሆይ ሁሉም መነኮስ መንግሥተ ሰማይ ይገባል ማለት አይደለም፤ ዓለምን በሚገባ የናቀ ብቻ ይገባል እንጂ መጀመሪያ የእግዚአብሔርን ጽድቁን ብቻ ፈልጉ፤ ጾምና ጸሎትን አዘውትሩ፤ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ ትእዛዛቱንም አጥብቃችሁ ጠብቁ እያሉ ይመክሯቸው ነበር. . .» በኋላም «ለዓለም ጨው ለራሴ አልጫ ሆንኩ፤ ለዓለም ብርሃን ለራሴ ጨለማ ሆንኩ፣ ከእውነተኛው ዳኛ ከጌታዬ ፊት ስቆም ምን እመልሳለሁ?» እያሉ በፍጹም ትህትና እና በልዩ መንፈሳዊ ተመስጦ ይጸልዩ ነበር፡፡

ስለዚህም ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቃንን እንድናስባቸው፣ በስማቸውም ለድሆች እንድንመጸውት፣ መታሰቢያቸውን እንድናደርግ የምትመክረን፤ የምታስተምረን [ማቴ.፲፥፵፩-፵፪]፡፡ ቅዱሳን ጻድቃን በሕይወተ ሥጋ ሳሉም ሆነ ከሞቱ በኋላ በዐጸደ ነፍስ ሆነው በጸሎታቸው ለሚታመኑ፣ በቃል ኪዳናቸው ለሚማጸኑ ምእመናን በመጸለይና ወደ እግዚአብሔር በማማለድ ድኅነተ ሥጋ፣ የድኅነት ነፍስን የሚያስገኙልን የችግር ጊዜ አማላጆቻችንና አስታራቂዎቻን ናቸው፤ ከእነዚህ ቅዱሳን መካከል ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንደኛው ናቸው፡፡

አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው፣ በብሕትውና ኖረዋል፡፡ በተጨማሪም እንደቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ የሰበኩ፣ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሐዋርያ ናቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሚታወሱባቸው በዓላት መካከልም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን የሚከብረው በዓለ ልደታቸው አንደኛው ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ዜና ልደታቸውን ሲናገር ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› በማለት በክብር ጠርቷቸዋል፡፡
                                            
                                           ✥••┈••●◉  ✞  ◉●••┈••✥

ምንጭ፡– ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፤ መጽሐፈ ስንክሳር (ታኅሣሥ ፳፬፣ ጥር ፳፬፣ መጋቢት ፳፬፣ ግንቦት ፲፪ እና ነሐሴ ፳፬ ቀን)

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

28 Dec, 07:42


✥✥✥ ማዳኑ ይደንቃል ✥✥✥

#እሳትን_አጥፎቶ_ማዳን_ይቻላል_እሳቱ_ሳይጠፋ_በነበልባል_ውስጥ_ግን_ማዳኑ_ይደንቃል!!!

በዚህም « ንጉሡ ናቡከደነጾር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም፦ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን ብሎ ተናገራቸው። እነርሱም፦ንጉሥ ሆይ፥ እውነት ነው ብለው ለንጉሡ መለሱለት። ፤ርሱም፦ እንሆ፥ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለኹ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማላክን ልጅ ይመስላል ብሎ መለሰ።» (ት ዳን ፫)

➛ በእርግጥም ነው ። ስሙ ድንቅ መካር ፣ ኃያል አምላክ ፣ የዘላለም አባት ፣ የሰላም አለቃ የተባለው አምላካችን የእርሱ የባሕርይ ገንዘቡ የሆነውን ድንቅነት እና "ኤል (አምላክ)" የተባለው ስሙም በስማቸው ሆኖላቸዋልና ዘወትር ድንቅ ያደርጋሉ። { ት.ኢሳ 9 ፥ 6 / ዘጸ 23 ፥ 21 }

ቅዱስ ገብርኤል ሆይ እኛንም ጠብቀን🤲

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

25 Dec, 19:32


እውነት አርነት ያወጣችኋል

" ጌታ ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀመዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል» አላቸው/ዮሐ.8፡31/፡፡ "

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «እውነት አርነት ያወጣችኋል» እያለ የሚናገራቸው አይሁድ «የአብርሃም ዘር ነን ለአንድም ስንኳ ከቶ ባሪያዎች አልሆንም፤ አንተ፡- አርነት ትወጣላችሁ እንዴት ትላለህ?» በማለት በባርነት መኖራቸውን መቀበል አልፈለጉም ነበር።

አይሁዳውያን የአብረሃም ዘር መሆናቸው እውነት ቢሆንም ይህ ግን የሚያሳፍራቸው እንጂ የሚያስመካቸው አልነበረም የአብርሃምን ሥራ በመሥራት ሳይሆን የአብርሃም ዘር በመሆናቸው ብቻ በከንቱ ይመኩ ነበር ።  አስቀድሞ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ " የአብርሃም ልጆች ነን በማለት ብቻ የምትመኩ አይምሰላችሁ " (ማቴዎስ 3፥9) በማለት የተመከሩ ቢሆኑም እውነትን ለመቀበል ግን አልፈቀዱም። የሚደንቀው ስለ አብርሃም ከመናገር ውጪ የራሳቸውን የጽድቅ ሥራ በጭራሽ አይጠቅሱም የላቸውምና።
.
-> ጌታችንም " ለማንም ባሪያዎች አልነበርንም " ለሚለው ለአይሁድ ንግግር 215 ዐመት በግብፅ ፣ 70 (80) ዐመት በባቢሎን በመሰለው ጊዜ ሁሉ በባርነት የነበሩ መሆናቸው ሊያስታውሳቸው ይችል ነበር ነገር ግን እርሱ ሁሉን ዐዋቂነቱን በመግለጽ እነርሱ በማሳፈር ለራሱ ክብርን ለማግኘት የሰው ባሪያዎች መሆናቸውን ሊያሳይ ሳይሆን ለመዳናቸው፣ ለጥቅማቸው የሚሆን እውነት ወደማወቅ ሊስባቸው ፈልጎ «እውነት እውነት እላችኋለሁ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባሪያ ነው»  /ዮሐ.8፥30-38/ በማለት የኃጢአት ባሪያዎች መሆናቸውን አሳወቃቸው ይህም ባርነት እግዚአብሔር ብቻ ነፃ የሚያወጣበት እጅግ አስከፊ የሆነ  ባርነት ነው።

በእርግጥ ዛሬም እንደ አይሁድ ባርነትን እና ነጻነትን በሥጋ ብቻ የሚመዝኑ ለኃጢአት ባርነት እስራት ምንም የማይሰማቸው የሥጋን ባርነትን እጅግ ከመፍራት፣ ከማፈራቸው፣ ካለመፈለጋቸው የተነሳ ለኃጢአት ባርነት አስር ሺህ ጊዜ ባሪያዎች መባልን የሚመርጡ ብዙ ናቸው። እንዲሁም ክህነት፣ ሊቅነትን፣ ሰባኪነትን፣ ዘማሪነትን፣ አስቀዳሽነትን፣ ገዳም ተሳላሚነትን--- እነዚህን የመሰሉትን ብቻ ገንዘብ በማድረግ መመካታችን ባሪያዎች ከመሆን አያድነንም።

-  እነዚህ አይሁድ «ያመኑ አይሁድ» እንደነበሩ ተብለዋል /ቊ.30-31/፡፡ ይሁንና ከነበሩበት የኃጢአት ባርነት ገና አርነት ያልወጡ ስለነበሩ እውነተኛ አማኞች ነበሩ ለማለት አይቻልም/ቊ.34፣44/፡፡

   ሰው አርነት የሚያወጣውን እውነት ጌታችን ሲናገር «እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀመዛሙርቴ ናችሁ እውነትንም ታውቃላችሁ» ብሏል /ዮሐ.8፡31/፡፡ በእርግጥ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት፣ በመማርና፣ በማንበብ ደረጃ ብዙዎች አርነት የወጡ፣ እውነትን ያወቁ ፣ ደቀ መዛሙርቱ የሆኑ ይመስላቸው ይሆናል፤ ጌታችን ግን «እውነትን ታውቃላችሁ ....» የሚላቸው በቃሉ የሚኖሩትን ነው፡፡ ... ይቆየን

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

05 Dec, 08:19


ኃጢአት እንደሠራህ ይሰማሃል? ꧁

ኃጢአት እንደሠራህ ካልተሰማህ እንዴት ንስሐ ትገባለህ?
ለራስህ ታማኝ ነህ?
ራስህን በትእዛዙ ላይ ትለካለህ?
ራስህን ከቅዱሳን ጋር ታወዳድራለህ?
በራስህ ውስጥ የእውነተኛ ክርስቲያን ባሕርያትን ታያለህ?
በራስህ ረክተሃል?
አሁን ያለህ ሕይወት ለመንግሥተ ሰማያት ብቁ አድርጎሃል?
መንፈሳዊ አባት አለህ?
የሚመራህ ሰው አለ?

አባ አሞጽ “የንስሐ ስድስት መንገዶች አሉ፡-
ኃጢአትን ማውገዝና መተው፣
በጸጸት መናዘዝ፣
የሌሎችን ኃጢአት ይቅር ማለት፣
በደለኞች ከመፍረድ መቆጠብ እና ልብን መያዝ” ብሏል።
"ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።" [1ኛ ዮሐንስ 1:8]

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

04 Dec, 04:01


➥ በአርምሞ በመንፈስ እርጋታ ውስጥ ናችሁን?
ከኾናችሁ እግዚአብሔር ይኽን ቋሚ ደስታ በልባችኹ ውስጥ ይበልጥ ቋሚ ያደርግላችኹ ዘንድ ለምኑት።

➥ በመከራዎችና በችግሮች ከፍተኛ ጥቃት ትታወካላችኁ?
እግዚአብሔር በሕይወታችኹ ውስጥ ያለውን ማዕበል ፀጥ እንዲያደርግላችኹ ለምኑት።

➥ ጸሎታችኁ ተሰምቶአልን?
እግዚአብሔርን አመስግኑ።

➥ አልተደመጣችኹምን?
እስከምትደመጡ ድረስ በጸሎታችኁ በጽናት ቆዩ።

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

29 Nov, 19:11


እመቤታችን ሆይ፣ የቅዱሳንና የምእመናንን ኹሉ ጸሎት በማዕጠንታቸው ከምድር ወደ ሰማይ በሚያሳርጉ በሰማያውያን የካህናት አለቆች አጆች ውስጥ ባለ የወርቅ ማዕጠንት እንመስልሻለን። እንዲኹም ስምሽን በመጥራት የሰው ልጆችን ልመና ወደ ልዩ ሦስትነት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያሳርጋሉ። የወገኖችሽንም ኅጢአት ታስተሠርዪ ዘንድ ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ተፈቅዶልሻልና። ለሰዎች ልጆች የዘለዓለም ሕይወት ድልድይ ትሆኝ ዘንድ የዓለም ኹሉ መድኃኒት ሆይ፣ ለምእመናን ወገኖችሽ መድኃኒታቸው ልትባይ ይገባል። ቅድስት ሆይ ልጅሽ ይቅርታውን ያድለን ዘንድ ለምኝልን።

አንቀጸ ብርሃን

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

29 Nov, 03:13


✥✥✥ ኅዳር ጽዮን በአክሱም ✥✥✥

➙   አክሱም ማርያም ጽዮን በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙት አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ መሠረታቸው ስትሆን ከተማዋም የኢትዮጵያ ሥልጣኔ መነሻ ናት፡፡ አክሱም በሕገ ልቡና የጸናች፣ ሕገ ኦሪትን የፈጸመች፣ በሕገ ወንጌል ያመነች ናት፡፡ ቅዱስ ዳዊት «ሕግ ይወጽእ እምጽዮን፤ ከጽዮን ሕግ ይወጣል» ሲል የተናገረው ቃለ የተገናኘላት ናት፡፡

➙    በዓለ ልደትን በላሊበላ፣ ጥምቀትን በጎንደር፣ ኅዳር ጽዮንን በኣክሱም ጽዮን ሲያከብሩት ልዩ የሆነ ሥርዓት ስለሚቀርብባቸው ምእመናን መንፈሳዊ ደስታ ይሰማቸዋል፡፡

👉   ኅዳር 21 ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል ነው ብለን በተለየ መልኩ የምናከብርበት ምክንያት፡-

1. በብሉይ ኪዳን ታቦተ ጽዮን የፈጸመችውን ልዩ ልዩ ገቢረ ተአምራትን ለማሰብ

2. ቀዳማዊ ምኒልክ ከዓሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል የበኲር ልጆች ጋር ሊቀ ካህናቱን አዛርያስንና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበት ዕለት በመሆኑ

3. በሦስት መቶ ሠላሳ ዓመተ ምሕረት በኣብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ይሁን ተብሎ ዐዋጅ የታወጀበት

4. ነቢዩ ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ ምሳሌ ራእይ ያየበት፣ ነቢዩ ሕዝቅኤል የተቆለፈች ቤተ መቅደስን፣ ዕዝራ የቅድስት አገር ምሳሌ ራእይ ያዩበት

5. አብርሃና አጽብሃ በወርቅና በዕንቍ ያሠሩት ባለ አሥራ ሁለት ክፍል ቤተመቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት

➙    በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቃል ኪዳኑ ታቦት መካከል ጥልቅ የሆነ ምሥጢራዊ ትምህርት አለ፡፡ /ዘፀ. 25÷9-20/፡፡ ይህቺ የቃል ኪዳን ታቦት በደብተራ ኦሪት በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ የኖረች፣ የዮርዳኖስን ባሕር የከፈለች /ኢያ. 3÷14-17/፤ ቅጽረ ኢያሪኮን ያፈረሰች /ኢያ 6÷1-21/፤ ዳጎን የተባለ የፍልስጥኤማውያንን ጣዖት የቆራረጠች /1ሳሙ 5÷1-5/፤ በድፍረት ሊነካ የሞከረውን ኦዛን የቀሰፈች /1ሳሙ 6÷6/፤ በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀምጣ ቤቱን በበረከት የመላች /2ሳሙ 6÷12/፣ ዳዊት የዘመረላት /2ሳሙ 6÷14/፤ ጠቢቡ ሰሎሞን በቤተ መቅደስ በክብር ያኖራት/1ነገ 8÷1/፤ የእግዚኣብሔር የክብር መገለጫ ናት፡፡
በታቦተ ጽዮን እና በዘመነ ሐዲስ በተገለጠችው በቅድስት ድንግል ማርያም መካከል ያለውን ረቂቅ እና ድንቅ ምሥጢራዊ ንጽጽር አስመልክቶ ሦርያዊው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም፤ «ታቦት በወርቅ ልቡጥ እምኩለሔ ዘግቡር እምዕፅ ዘኢይነቅዝ፤ ከማይነቅዝ እንጨት የተቀረጸ በው ስጥ በአፍአ በወርቅ የተለበጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሐ ጠባይዕ ሳያድፍባትና የቅድስና ባሕርይ ሳይጎድፍባት በማየት፣ በመስማት፣ በመዳሰሰ፣ በማሽተት አንዳችም እድፍ ጉድፍ ሳያገኛት በንጽሕናና በቅድስና ጸንታ በኃጢኣት ሳትለወጥ ኖራለች፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም፤ «አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ ላዕሌኪ፤ ምክንያታዊ ነውር ኃጢአት የሌለብሽ የኃጢአት ሸታ ያልደረሰብሽ ንጽሕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና ክብርት በልዕልና ኣንቺ ነሽ» /መኃ 4÷7/ ሲል ተናግሯል፡፡

➙   ታቦተ ጽዮን የቃለ እግዚአብሔር ማደሪያ እንደሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያምም ለአካላዊ ቃል ለእግዚአብሔር ወልድ ማደሪያ ሆናለች፡፡ ይኽንንም ቅዱስ ኤፍሬም ሲያስረዳ፤ «ኮንኪ ታቦቶ ለፈጣሬ ሰማያት ወምድር ፆርኪዮ በከርስኪ ተሰዓተ አውርኃ አንቲ ማእምንት ለዘኢያገምርዎ ሰማያት ወምድር፤ ድንግል ማርያም ሆይ ሰማይና ምድርን ለፈጠረ አምላክ ለእርሱ ማደሪያ ሆንሽ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀንሸ ቻልሽው ተሸከምሽው ሰማይና ምድር የማይወስኑትን ለመወሰን የታመንሽ አንቺ ነሽ» ብሎ ተቀኝቶላታል፡፡

➙     ስለሆነም ከብሉይ ኪዳን እስከ ሐዲስ ኪዳን እግዚአብሔር ራሱን የገለጠበትን የቸርነት በዓል እግዚአብሔር በፈቀደልን ቦታ ሆነን ስናከብር ከእኛ የሚጠበቀውን በጎ ነገር እያሰብን በተግባርም እየገለጥን ከበዓሉ ረድኤትና በረከት ተሳታፊ እንሆን ዘንድ የእግዚአብሔር ቸርነት የእናቱ የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን፡፡

ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ካሎት በ @fenote_Abew_bot ያስቀምጡልን።

ቤተሰብ ይሁኑ
👉TELEGRAM https://t.me/fenote_abew

👉FACEBOOK https://www.facebook.com/profile.php?id=100040602775882

👉 YOUTUBE https://www.youtube.com/@finoteabew

👉TIK TOK https://www.tiktok.com/@fenoteabew_zetewahido?_t=8mB9Wj5mAPV&_r=1

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

21 Nov, 04:30


✥••┈••●◉ ቅዱስ ሚካኤል ◉●••┈••✥
ሚካኤል (በዕብራይስጥ: מִיכָאֵל‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል, ሲተረጎም፡ 'ማንነው እንደ እግዚአብሔር?'; በግሪክ: Μιχαήλ, ሲነበብ፡ Mikhaḗl; በላቲን: Michahel-ሲነበብ፡ ሚካኤል; በአረቢኛ: ميخائيل‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል) በክርስትና በአይሁድ በእስልምና እንዲሁም በመላዕክት አማላጅነት በሚያምኑ ሃይማኖቶች የመላዕክት ሁሉ አለቃ ሊቀ መላዕክት ተብሎ ይጠራል።

በኅዳር ወር በዐሥራ ኹለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ኅዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በዐሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡ እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡ (ይህን ኹለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2 እንደሆነ አክሲማሮስ በሚባለው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡)

መላእክት ቊጥራቸው እጅግ ብዙ ቢሆንም በ 99ኙ ነገደ መላእክት የተከፈሉና አለቆችም ያሏቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ሁሉ መላእክት አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ በትህትናው ልዕልናን ያገኘው ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠው ክብር ከማንኛውም መልአክ የበለጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡

በተጨማሪም ስለ መላእክት ከመጽሐፍ ቅዱስ ለመረዳት እነዚህን ጥቅሶች ይመለከቱ:-

• ሰውን ይረዳሉ [ዘፍ.16፡7፤ ዘፍ.18፡15፤ ዘጸ.23፡20፤ መሳ6፡11፤ 1ኛነገ.19፡5፤ 2ኛነገ 6፡15፤ ዳን.8፡15-19፤ ዳን.3፡17፤ ት.ዘካ.1፡12፤ ማቴ.18፡10፤ሉቃ. 1፡26፤ ሉቃ.13፡6፤ ዩሐ.20፡11፤ ሐዋ.12፡6፤ ራዕይ 12፡7፤]

• ስግደት ይገባቸዋል [ዘፍ.19፡1-2፤ ዘኁ.22፡31፤ ኢያሱ 5፡12፤ መሳ.13፡2፤ 1ኛ ዜና 21፡1-7፤ ዳን.8፡15]

የቅዱስ ሚካኤል ስሞች
ሚካኤል ማለት "መኑ ከመ አምላክ (እግዚአብሔር) እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው" ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ ንጹሕ ርህሩህ ኃይል ረቂቅ ማነው መልሱ የለም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ፣…ናቸው፡፡
መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ - ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡
መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡
መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል።

ሰላም ለርእስከ
ሚካኤል ሆይ፣ መብረቅን ለተጎናጸፈ መልአካዊ ረቂቅ ርእስህ ሰላም እላለሁ።
ተፈጥሮአቸው ከእሳት የሆነ የሰማያውያን የመላእክት ሠራዊት አለቃቸው የምትሆን ሚካኤል ሆይ፣ በኃጢአት ተሰናክዬ ወድቄ እንዳልፍገመገም አንተን ድጋፌ አድርጌአለሁና ፍጹም የማዳንህን ትድግና በኔ ላይ ትገልጽ ዘንድ በስተቀኜ ቁመህ አለሁልህ በለኝ እንጂ በሩቅ ሆነህ አትመልከተኝ። [መልክአ ሚካኤል አንቀጽ ፫]
መልካም በዓል ይሁንላችኹ

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

12 Nov, 10:58


"መላእክትን ማየት ትልቅ ተአምራት አይደለም፥ የራስን ስህተት መመልከት ግን ተአምር ነው።'

ቅዱስ አባ እንጦንስ

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

08 Nov, 08:05


#የዘመናት_ናፍቆቴ

"አንተ ረዳኤ ምንዱባን የችግረኞች አጋዥ ፣ አንተ ተስፋ ቅቡፃን የጨለመባቸው መብራት ፣ አንተ አሰጣጥ የምታውቅበት ፣ የመስጠት ችሎታ ያለህ ፣ ከሞት በኋላም የምትጋብዝ ትልቅ ወዳጅ በባሕርይህ ድካም ፣ በአካላትህ ባዕድ የሌለብህ አድሮ ሁሉን ሳጣው አድሮ የማገኝህ ትሰጠኛለህ ብዬ ሳይሆን ሰጥተህ ያኖርከኝ ፣ ከእኔ ምንም ባይገኝም እንደሚያገኝ ሁነህ የፈለግኸኝ ፣ ቤተ ክርስቲያንን የበረሃ ምንጭ አድርገህ የሰጠኸኝ ፣ ጨለማዬ ላይ ይብራ ብለህ ያወጅኽልኝ ፣ የጸናው ማንነትህ ያልጸናውን እኔነቴን ያልናቀኝ ፣ እራመዳለሁ ስል ብወድቅም ተነሥ ብለህ ያበረታኸኝ ፣ እየሠራሁ ሳበላሽ በገርነት ጎበዝ ያልከኝ ፣ በቤትህ ጠፍቼ ሳለሁ በደጅ በጠፉት ስፈርድ የመከርኸኝ በሚያረክሰው ዓለም ያገኘሁህ ጸዓዳ ልብስ አንተ እግዚአብሔር ነህና ተመስገን። የእኔ ሠራተኛ ፣ ጓዳዬን የምትሞላ ፣ በቤትህ ባድርም አንተ ግን በእኔ ውስጥ ያደርህ ፣ ለመማረክ ወጥቼ አንተ ግን የማረከኝ ፣ ቀኑን ሙሉ ስባዝን ቀኑን ሙሉ የፈለግኸኝ ፣ በምቾቴ ስክድህ በመንሣት ሳይሆን አሁንም በመስጠት ያስተማርከኝ ፣ አጢኜ የማልፈጽምህ እግዚአብሔር ተመስገን። የሰዎችና የሁኔታ ጥገኛ ብሆንም ፣ የቀኑ ወሬ ይዞኝ ብጠፋም ፣ ምድራዊ ጠባቂን እየፈራሁ ጠባቂ መልአኬን ባላከብር ፣ ፍርድ ቤትን እየሰጋሁ ትንሣኤ ዘጉባዔን ብረሳም ፣ በዋጋ ገዝተኸኝ በነጻ ብጠፋም ፣ ሥራዎቼን አተልቄ ውለታህን ባሳንስም ፣ የሚያገለግለኝን አገልጋይ ትቼ የሚገዛኝን ባፈቅርም ፣ ባልቀደምሁበት ሂዱ ብዬ ባውጅም ፣ የማትሞት አባት አንተ በይቅርታ ዓይንህ ታየኛለህ። የዘመናት ናፍቆቴ ባንተ እንደሚፈጸም አምናለሁ። አሜን።

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

04 Nov, 08:35


#ብሂለ_አበው

"ሰይጣን ሊያስመስለው የማይችለው ነገር ትህትናን ብቻ ነው።

✍️ቅዱስ ዮሐንስ ዘቅሊማቆስ(ዘሰዋስው)

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

29 Oct, 09:24


✟ የተባረከች አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች

✟ የተባረከች ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች

✟ የተባረከ ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል

✟ የተባረከች ምላስ የአምላኳን ስጋና ደምን ትቀበላለች

✟ የተባረከ አንደበት ላይ እግዚሐብሔር ይመስገን የሚል ቃል አይጠፋበትም

✟ የተባረከች አንገት የአምልኮ ደም የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ትሸከማለች

✟ የተባረከች ልብ ኢየሱስን እስከ እናቱ አንግሳ በፍቅር ትሞላለች

✟ የተባረከች እጅ የቀረበላትን ምግብ በአምልኮ ስም ትባርካለች

✟ የተባረከች እግር ጠዋትና ማታ የአምላኳን መቅደስ ትረግጣለች

"እኔ እግዚሐብኤር አምላካቹ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ቅዱስም ሁኑ እኔ ቅዱስ ነኝና" ዘሌ. 11፥44

#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

26 Oct, 10:42


ከትላንት በስቲያ ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የአዲስአበባ ሀገረ ስብከትን ጉዳይ አጣርተው ለግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ ለውሳኔ እንዲያቀርቡ የተመረጡት
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ባቀረቡት ጥያቄ መነሻነት ከኮሚቴው ወጥተው ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ተተክተዋል።

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

26 Oct, 08:51


"ሚዲያ ለኦርቶዶክሳዊ ትውልድ ቀጣይነት" በሚል መሪ ቃል ልዩ የሆነ መርሐ ግብር ሊዘጋጅ መሆኑ ተገለጸ !


በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል ሚዲያ ዋና ክፍል " ሚዲያ ለኦርቶዶክሳዊ ትውልድ ቀጣይነት" በሚል መሪ ቃል ልዩ የሆነ መርሐ ግብር ሊያዘጋጅ መሆኑን ገልጿል ።

የመርሐ ግብሩ ዓላማም የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ በኦርቶዶክሳዊ ትውልድ ላይ እየሠራ ያለውንና ሊሠራ የሚገባውን የትውልድ ቀረጻ ሥራ ለምእመናን ማስገንዘብ መሆኑ ተጠቅሷል::

መርሐ ግብሩ እሁድ ጥቅምት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ወይም Oct .27, 2024  በዲሲ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ  8:00 pm እንደሚካሄድም ለማወቅ ተችሏል::

ዝግጅቱ በሁሉም ክፍላተ ዓለማት ያሉ ኦርቶዶክሳውያን ይከታተሉት ዘንድ በቨርቹዋል እንደሚካሄድ የመርሐ ግብሩ አዘጋጅ የማኅበረ ቅዱሳን አሜሪካ ማዕከል ሚዲያ ዋና ክፍል አስታውቋል::

በዕለቱ የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ትውልድ ማፍራት ግድ የሚለው ኦርቶዶክሳዊ ሁሉ በዚህ ዝግጅት እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቧል::

መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን ቴቪ ነው

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

25 Oct, 05:46


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን ጉዳይ የሚያጠኑ ብፁዓን ጳጳሳትን መሰየሙ ተገለጸ፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ ፡
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ፣
ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ እና
ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የሚመሩት ገለልተኛ አጣሪ ኮሚቴ የሰየመ ሲሆን ከመደበኛ የገንዘብ እንቅስቃሴ ውጪ ቅጥር፣እድገትና ዝውውር እንዲቆም መወሰኑ ተገልጿል፡፡

ዐራት ሊቃውንትን በማካተት ችግሩን በዝርዝር በማጥናት ለግንቦት የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እንዲያቀርቡ ተወስኗልም ተብሏል፡፡

ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

24 Oct, 19:27


የኦሬንታል አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ጉባኤ እና ሥርዓተ ቅዳሴ መርሐ ግብር  (Oriental Orthodox Concelebration) የኦርቶዶክስ አብያተክርስቲያናት ቋሚ ጉባኤ (SCOOCH) አሰናጅነት በሰሜን አሜሪካ ኒውጀርሲ የማላንካራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን (Old Tappan) ተካሄደ
(✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

በዚህም ሥነ ሥርዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን ጨምሮ የአርሜንያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ;የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ; የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ; የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሊቃነ ጳጳሳት ተሳትፈውበታል።
ዝግጅቱን ያሰናዱት  ብፁዕ አቡነ ሞር ቴቶ ዬልዶ የማላንካራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡ በመድረኩ ለብፁዕ አቡነ መቃርዮስ በሰሜን አሜሪካ ለኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ እውቅና ሰጥቷል፡፡
በዝግጅቱ ከ400 በላይ ካህናት ዲያቆናትና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡ መርሐ ግብሩም የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ቋሚ ጉባኤ The Standing Conference of Oriental Orthodox Churches in America እኤአ 1973 ዓ.ም የተመሠረተ ሲሆን የጋራ ቅዳሴ መርሐ ግብር በMORAN TV  በቀጥታ ሥርጭት ተላልፏል፡፡
የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በጋራ ጉዳዮች ላይ ምክክር የሚያደርጉበት ጉባኤ ሲሆን ; ባለፉት ዓመታት በርካታ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሃይማኖት አባቶች በየቤተ ክርስቲያኖቻቸው የጉባኤው አባል ሆነው በመወከል ለድርጅቱ እድገትና መስፋፋት ትልቅ አስተዋፅዖ አድርገዋል። በጉባኤው በርካታ የሥነ መለኮት ጉዳዮች ላይ ምክክር ሲያደርግ ቆይቷል።

ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ካሎት በ @fenote_Abew_bot ያስቀምጡልን።

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ https://t.me/fenote_abew

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

22 Oct, 11:43


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሰየመ።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የጥቅምት 2017 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሰይሟል።

ምልዓተ ጉባኤው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የመክፈቻ መልዕክት ዛሬ ጠዋት መጀመሩ የሚታወቅ ሲሆን ከቅዱስነታቸው የመክፈቻ መልእክት በኋላም የመወያያ አጀንዳ ቀርጸው የሚያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን ነው የሰየመው።

በዚህም መሰረት

1.ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ
2.ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ
3.ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
4.ብፁዕ አቡነ ማርቆስ (ዘስያትል)
5.ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ
6.ብፁዕ አቡነ  ኤጲፋንዮስ
7.ብፁዕ አቡነ ኤልሣዕ የተመረጡ ሲሆን አጀንዳ የማርቀቅ ተግባራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ የሚያቀርቡትን ረቂቅ አጀንዳ ከመረመረና ማስተካከያ ካደረገበት በኋላ የጸደቀውን አጀንዳ መሰረት በማድረግ በቅደም ተከተል እየተወያየ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል።

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

21 Oct, 12:35


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በነገው ዕለት ይጀመራል !


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የጥቅምት 2017 ዓ.ም  ምልዓተ ጉባኤ በነገው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ይጀመራል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ጥቅምት 12 እና በዓለ ትንሣኤ በዋለ በ25ተኛው ቀን ምልዓተ ጉባኤውን የሚያከናውን መሆኑ ይታወቃል።

ምልዓተ ጉባኤው በዛሬው ዕለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በሚደረገው የጸሎት መርሐግብር የሚከፈት ሲሆን ከነገ ጀምሮ ቅዱስ ሲኖዶስ በልዩ ልዩ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያንና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ  እንደሚወያይ ይጠበቃል።

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

18 Oct, 17:36


11. ሙስና፣ ዘረኝነት፣ ጎሠኝነት፣ ቡድነኝነት፣ አድሎአዊነትና ግለኝት በተመለከተ በጋራ በአንድ ድምጽ በመነሣት ይኽንን ክብረ ነክና አጋላጭ፣ ለቤተ ክርስቲያን እድገትና ለሐዋርያዊ ተልእኮ እንቅፋት፣ የቤተ ክርስቲያን ማንነት ለሌላቸው ግለሰቦች መደበቂያ፣ በጥቂት ግለሰቦች በደልና ጥፋት በንጽሕና በቅድስና የሚያገለግሉ፣ ካህናትንና ሠራተኞችን የሚያሳፍሩ፣ ምእመናንን የሚያሸማቅቁ በመሆናቸው እነዚህን ክፉ ደዌያት ስም አጠራራቸውን ከቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ለማስወገድ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ በጥናትና በቁርጠኝነት ላይ የተመሠረተ፣ የጥፋት በራቸውን በዘላቂነት የሚዘጋ ሥልት እንዲቀይስ ጉባኤው ያሳስባል

12. በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት እስከ አሁን ቤተ ክርስቲያን በፈረሱባት ሕንፃዎችና ቤቶች ምትክ ቦታ በመስጠት ጉዳቷን ለመቀነሰ የተደረገውን ጥረት ጉባኤው እያደነቀ፤ በተሰጡት ይዞታዎች ላይ በአጭር ጊዜ ግንባታውን በማካሄድ የአባቶችቻንን አሻራ መልሶ በመትከል፣ ይዞታውን ማስከበርና የተቋረጠውን ገቢ ማስቀጠል እንዲቻል ብርቱ ጥረት እንዲደረግ ጉባኤው እያሳሰበ፤ የኮሪደር ልማት የተባለው ጉዳይ በሌሎች የክልል ከተሞችም እየተስፋፋ ስለሆነ በቀጣይ ለሚነሡ የይዞታ ጥያቄዎች ለሚከሰቱ ችግሮች ከወዲሁ ዝግጅት እንዲደረግ፣

13. አዳዲስ አማኞችን አሳምኖ ለሥላሴ ልጅነት ማብቃት፣ የአዳዲስ አብያተ ክርስቲያናት መተከል፣ መታነፅና መባረክ የታየው ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ እመርታ ሁሉን ያስደሰተ በመሆኑ ከዚህ በበለጠ አጠናክረን ለመሥራት ቃል እንገባን፤ 

14. የቅዱስ ባኮስ የቅድስና ዕውቀና ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ ስትዘግበው የቆየ ቢሆንም ጽላት ተቀርፆ እንዲከበር መደረጉ አስደሳች ሲሆን ለሀገር በረከት፣ ለትውልድ የመንፈሳዊ ሕይወት አርአያ፣ ለቅድስና ፍኖት የሆኑ ነገርግን የማይታወቁ የሌሎች ኢትዮጵያውያንን ቅዱሳን ታሪክና ገድል በማጥናት እንዲዘከሩ እንዲደረግ ጉባኤው ያሳስባል፡

15. በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የተከፈቱ መንፈሳውያን ኮሌጆችና የካህናት ማሰልጠኛዎችም በአጥጋቢ ሁኔታ ሥራ መጀመራቸው፣ በዚህ ዘርፍ በእጥፍ እየጨመረ የመጣው ዕድገትና ውጤት ጉባኤው ያደነቀ ሲሆን ወደ ሥራ ለመግባት በሂደት ላይ ያሉት በርካታ መንፈሳዊ ኮሌጆች እየተስሳፉ ያሉ የአብነት ትምህርት ቤቶች፣ ዘመናዊ የትምህርት ተቋማት በአጠቃላይ ሁሉም ትምህርትን የሚመለከት ጉዳይ በትምህርት ኮሚሽን ተቋቁሞ ጥናት በማድረግ እንዲስፋፉ ጉባኤው ያሳስባል፤

16. በሰላም መታጣትና በቀኖና ጥሰት ምክንያት መላው ወለጋ አህጉረ ስብከት ለበርታ ወራት ከማእከሉ ጋር ያለው ግንኙነት ተቋርጦ ከቆየ በኋላ በቅርቡ በሀገረ ሰብከቱ ሊቀ ጳጳስ ወደ መዋቅር መመለሳቸው ጉባኤውን በእጅጉ አስደስቷል፤ ስለሆነም ቀሪ ሥራዎች ተጠናቀው የቤተ ክርስቲያን መዋቅር እንዲጠበቅ፣ በሌሎችም አካባቢዎች ለተፈጠሩት የመዋቅር ጥሰቶች ቀኖናዊ መፍትሔ እንዲበጅለት ጉባኤ ያሳስባል፡፡

17. ሐዋርያዊትና የክርስቶስ አገልጋይ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ቋንቋን በማክበር ታገለግልበታለች እንጅ በቋንቋም አትገደብም፤ ስለዚህ በልዩ ልዩ ቋንቋዎች ሐዋርያዊ ተልእኮ መፈጸሟ እንደተጠበቀ ሆኖ ለወደፊት የሁሉም መዓርገ ክህነት ሢመት፣ በየደረጃው ያሉ የአስተዳደር ሥራ የኃላፊነት ምደባዎች፣ መሠረት እምነትን፣ ቀኖና ቤተክርስቲያንን፣ ዕውቀትና ሙያዊ ብቃትን ብቻ መሠረት ያደረገ ይሆን ዘንድ ጉባኤው በጥብቅ ያሳስባል፤   

18. ሰበካ ጉባኤን ማጠናከር፣ ሰንበት ትምህርት ቤትን ማደራጀት፣ አብነት ትምህርት ቤቶች ማጎልበትና ማስፋፋት፣ ሕጎችና ደንቦችን በማዘጋጀት የተደረገውን ጥረት የሚያስመሰግን ሆኖ አሁን ወቅቱን የጠበቁ ሕጎችና ደንቦችን በማውጣት ሁሉም እንዲሠራበት ማድረግን፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን፣ የራስ አገዝ ልማትን ማሳደግና በገቢ ራስን መቻል፣ በጸደቀው የዐሥር ዓመቱ መሪ ዕቅድ መሥራት የቤተ ክርስቲያናችን ዓይነተኛ ተልእኮ በመሆኑ በሚሰጠው መመሪያ መሠረት ለመፈጸም ቃል እንገባለን፡፡

19. የቤተ ክርስቲያናችን የውጭ ሀገር አገልግሎት እየሰፋና እያደገ መምጣቱ በጉልህ የሚታይ ሲሆን ይኽ እድገትና አደረጃጀት እንዲጠናከር፤ በተጨማሪም ቤተ ክርስቲያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላት ተሳትፎ የበለጠ እንዲያድግ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሠራ ጉባኤው ያሳስባል፤

20. ከውይይትና ከብፁዓን አበው መልእክቶች እንደተሰጠው መመሪያ የቤተ ክርስቲያንን ልዕልና ለመመለስ፣ ለሀገራንችን ሰላምና ደኅንነት ለሰው ልጆች ሁሉ መልካም ግንኙነት የጋራ ጸሎት በኅብረት ይደረግ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ እንዲሰጥበት ጉባኤ በአክብሮት ይጠይቃል፤  

በመጨረሻም እስከ ዛሬ ስንሰበሰብበት ከነበረው መቃረቢያ አዳራሽ ወጥተን ይኽ ዛሬ የተገኘንበት አዳራሽ በአጭር ጊዜ አሁን ባለበት ደረጃ እንዲህ ጸድቶና ተውቦ የ43ኛውን አጠቃላይ ጉበኤ እንዲከናወንበት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አመራር መስጠታቸው ቁርጠኝነት ካለ ብዙ መሥራት እንደሚቻል ያሳየ፣ የሥራ ክትትልና አፈጻጸም አድናቆታችንን በመግለጽ ሐዋርያው እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖርና እንዳለው የአዳራሹ ቀሪው ሥራ ተጠናቆ በቅርቡ እንደሚመረቅ ተስፋችንን እንገልጻለን፤

ይሕ ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጸም ያደረጉ በቅዱስነታቸው አባታዊ ርእሰ መንበርነት፣ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በሳልና የተረጋጋ አመራር ሁሉም መርሐ ግብሮች በተያዘላቸው ሰዓትና ጊዜ ተጠናቀው እንዲፈጸሉ የመሩንን አባቶች በረከታችሁ ይድረሰን እያልን፤

የጉባአው ዋና አዘጋጅ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ዋና ኃላፊና መላው ሠራተኞች፣ ሁሉም ተባባሪ አካላት በገንዘብም በጉልበትም ትብብር ያደረጉ ሁሉ በአጠቃላይ ጉባኤው አመስግኗል፡፡ 

ከሁሉም በላይ ለዚህ ለ፵፫ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ ያደረሰንና ያስፈጸመን የአባቶቻችን አምላክ ልዑል እግዚአሔር ምስጋና ይግባው አሜን ሎቱ ስብሐት ወባርኰት ወጥበብ፣ ወአኰቴት፣ ወኃይል ወጽንዕ ለአምላክነ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

18 Oct, 17:36


የአቋም መግለጫ፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ፵፫ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ የአቋም መግለጫ

“ትውልደ ትውልድ ይንእዱ ምግባሪከ ወይዜንዉ ኃይለከ - የልጅ ልጅ ሥራህን ይናገራሉ፤ ያመሰግናሉ፣ ከሃሊነትህን ይናገራሉ ያስተምራሉ” መዝ 144 ቁ 4

ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ ዓለምአቀፋዊት የሆነቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያዊ ተልዕኮዋ ረጅም ዘመናትን ሰማያዊውን ጥበብንና ምድራዊውን ዕውቀትን በማስተማር፣ የሀገርና የወገንን እምነትና ፍቅር ምንነት ከተግባር ጋር፣ ሰላምና አንድነትና በማስፈን፣ ለሰው ልጅ ዘለዓለማዊ ድኅነት ሌሌት ከቀን ያለማቋረጥ ሰዓት ሳይገድባት፣ መልክዓ ምድር ሳይገድት፣ የሰው ባህልና ቋንቋ ሳይወስኗት፣ ትውልድን፣ ከትውልድ፣ ዘመንን ከዘመን፣ ሰማያውያን ከምድራውያን፣ ፍጡራንን ከፈጣሪ ስታገናኝ ኖራለች፡፡ ለሰው ዘር ጥበብን፣ ለትወልድ ታሪክና ትውፊትን፣ ስትቀምር፣ ነፃነትና ሰብዓዊ ክብርን በዐውደ ምኅረቷ ስታውጅ፣ በአባቶችና በሊቃውንት በሕየወት ሰሌዳ፣ በደመቀ ቀለም በቃልም በመጽሐፍም ስታስተጋባ እስከ አሁን አለች ወደፊትም ትኖራለች፡፡

ከዚህ መሠረታዊ የታሪክ ዕሴት በመነሣት ለዛሬው 43ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ደርሰናል፡፡

በዚሁ ጉባኤው በቆየባቸው ቀናት ውስጥ የቅዱስነታቸውንና የብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ አባታዊ መልእክቶች፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ሪፖርት፣ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር አህጉረ ሰብከት ዘገባዎች፣ ከውይይት ሐሳቦች፣ ከአበው ሊቃነ ጳጳሳት መልእክቶች፣ ከቡድን ውይይትና ዘገባ በመነሣት ከቃለ ጉባኤ ሐሳብ በተጨማሪ በቅዱስ ሲኖዶስ ትኩረት ተሰጥቶባቸው በአጀንዳ ተቀርጸው ውይይትና ምክክር ተደርጎባቸው ውሳኔና መመሪያ ይደረግባቸው ዘንድ እኛም ለተፈጻሚነቱ የራሳችንን ድርሻ መወጣት እንድንችል ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን የአቋም መግለጫ አቅርበናል፤

1. በጉባኤው መክፈቻ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስተላለፉፉልንን ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ጉባኤው በሙሉ ድምጽ ተቀብሎታል፣ ለተግባራዊነቱ ቃል ይገባል 

2. ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፉልንን አባታዊ መልእክት ጉባኤው በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ ተግባራዊ ለማድረግ ቃል እንገባለን፤

3. በብዙ የሀገራችን ክፍል ባለው የሰላም እጦት የተፈጠሩት ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምክንያት የካህናት፣ የመነኰሳትና የምእመናን ሞትና ስደት በጥብቅ እያወገዝን በዚህ ታሪክ የማይረሳው በምድር ወንጀል፣ በመንፈሳዊው ዓለምና በሰማይ ኃጢአት የሆነ እኩይ ተግባር የተሰማራችሁ ሁሉ ወደ ርኃራኄ ልብ እንድተመለሱ ጉባኤው በአጽንዖት ጥሪውን ያስተላልፋል፤ 

4. የሰላም ዕጦት ጉዳይ ምንም እንኳ ዓለም አቀፍ ቢሆንም ሀገራችንም በተከሰተው ግጭትና ጦርነት ምክንያት ሰላም ካጣች ሰንብታለች፣ ስለሆነም ቅዱስ ሲኖዶስ በዓለም የሚደነቅ፣ ለሀገር ተገን የሚሆን አስደነቂ ውሳኔ እንደሚወስን ተስፋች ጽኑ ነው፣ ጸሎታችንም ነው፤ የአገልጋዮች እንባ የሚታበስበት፣ ለነገ ታሪክ የትውልድ ተወቃሽ ከመሆን ይልቅ፤ የሰላምና እርቅ ምሳሌ የምንሆንበት ከፍተኛ የሰላም ሥራ ልዩ የሆነ የሰላም ኮሚቴ ተቋቁሞ ዘላቂ ሰላምን ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያን የሚያመጣ ሥራ እንዲሠራ ጉባኤው ያሳስባል፤

5. የዚህን ዓለም ተድላ ንቀው፣ ደዋ ለብሰው ጤዛ ልሰው በገዳም ተወስነው ድምጸ አራዊቱን ግርማ ሌሊቱን ታግሰው ለመላው የሰው ዘር የሚጸልዩ ይህን ይደግፋሉ ያንን ይቃወማሉ የማይባሉ ገዳማውያን መነኮሳት ከየበአታቸው ተጎትተው ወጥተው የተገደሉበት ሁኔታ በሀገራችን መከሰቱ ጉባኤውን እጅግ አሳዝኖታል ይኽ ጉዳይ ቀጣይነቱ እየታየ ስለሆነ የሚመለከታቸው ሁሉ ተገቢውን የሕግ ሥራ በመሥራት የሰው ልጅ ከአምላክ የተሰጠውን የመኖር መብት፣ የእምነት ነፃነት፣ የመዘዋር ተፈጥሯዊና ሰብዓዊ መብት በሀገራች እንዲከበር ያሳስባል፤ 

6. በታሪካችን ያላየነው ከአባቶቻችን ያልሰማነው በመጻሕፍት ያላነበብነው ከኢትዮጵያ ባህልና ሥነ ልቡና ውጪ በሆነ መንገድ ሰዎችን ለገንዘብ ሲባል ማገት በተለይም ፊትና ኋላ ግራና ቀኝ እሳትና ውኃ ያለዩ ሕፃናት በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው፣ ወጣቶችና አረጋውያን ሳይቀር እያተገቱ የሚሰቃዩበትና የሚደፈሩበት ሁኔታ የገጠመንን ፈተና ክብደቱን የሚያሳይ መሆኑ ይኽ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት መፍትሔ እንዲበጅለት ጉባኤው ጥሪውን ያቀርባል፤

7. ጥላቻና የጥፋት ቅስቀሳዎች፣ በዜጎች መካከል አለመተማመንና መለያየት፣ ለሀገር አንድነትና የሕዝብ አብሮነት ጠንቅ፣ ለወደፊቱ አስጊ የሆኑ እንቅስቃሴዎች የበዙበት፣ የትውልዱ የወደፊት በሰላምና በተረጋጋ ሁኔታ የመኖር ዋስትና እየጠፋ፣ በርካታ ወጣቶች በስደትና በመፈናቀል ላይ ያሉበት ሁኔታ በመኖሩ የጥላች ንግግር፣ ዘለፋና ያልተገባ ትችትና መናናቅ ማንንም የማያንጽ ክፉ ትምህርት፣ ለሀገርም፣ ለሕዝብም የማይጠቅም ሁሉንም የሚያጠፋ ስለሆነ በእንዲህ ያለ ተግባር መገናኛ ብዙኀን በመጠቀም የተሰማራችሁ፣ ሁሉ በሚያፋቅርና በሚያዋድድ ተግባር እንድትሰማሩ ጉባኤው ጥሪውን ያቀርባል፣ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚሁ ትኩረት ሰጥቶ መመሪያና ውሳኔ ያወጣ ዘንድ አጽንዖት እንጠይቃለን፤    

8. በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 20 በእንተ ሰማዕታት የጌታችንን ትምህርት መሠረት በማድረግ በተሠራው ቀኖና ካህናትና ምእመናን ሰማእትነትን የተቀበሉበትን ቀን መዘከርና ማክበር፣ የከበረ አጽማቸውን በቅጽረ ቤተ ክርስቲያን በክብር ማስቀመጥ፣ ቤተሰቦቻቸውንና በእነሱ ሥራ ይተዳደሩ የነበሩ የሰማእታት ቤተሰብ በሚል መርዳት የተደነገገ ቀኖና ነው፤ ይኽን በማድረግ የሰማእትነት ዋጋን እናገኛለን፣ ቤተ ክርስቲያነን እናጸናለን፤ በዚህ ቀኖና መሠረትና ከሰብዓዊ ርኅራሄ በመነሣት በሰማዕትነት የተለዩን ወገኖች መታሰቢያቸው እንዲደረግ፣ ቤተሰቦቻቸውና ጉዳተኞችን ወላጆቻውን ያጡ የካህነትና የምእመንና ጨቅላ ሕፃናትና ያልደረሱ ልጆች፣ ያለጧሪ የቀሩ አረጋውያን የቤተ ክርስቲያንን እንክብካቤ በጥብቅ ይፈልጋሉ፤ ለዚህ መፍትሔ እንዲሆን በውጭና በሀገር ውስጥ ያሉ አህጉረ ሰብከት ያካተተ አስቸኳይ ዓለም አቀፍ ግብረ ኃይል እንዲቋቋም ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲሰጥበት እያሳሰብን ለተግባራዊነቱም ሁላችንም ቃል እንገባለን፣

9. በአንዳንድ አካባቢዎች ሕግንና የአምልኮ ነፃነት ሰብዓዊ መብትን በመጣስ የመስቀል ደመራና የባሕረ ጥምቀት ቦታ መወሰድ ሃይማኖታዊ አለባበስና መስቀል መያዝን በመከልከል የአንገት ማዕተብን መበጠስ፣ በኦርቶዶክሳውያን ላይ እንግልትና ወከባ መፍጠር አሳዛኝ በመሆኑ ድገርጊቱን አጥብቀን እየተቃወመን በቅዱስ ሲኖዶስ ቀርቦ ውይይት እንዲደረግበት ጉባኤው ያሳስባል፤ 

10. ቤተ ክርስቲያን እንኳንስ ተናግራ ሰማች ሲባል የሚያስደነግጥ ግርማና መታፈር፣ መከበርና መወደድ የነበራት በመሠረተችው ሀገር የምትሳደድበት፣ የመሪዎቿ አባቶች ጥሪ የማይከበርበት፣ የሰላም ጥሪ ድምጽዋ የማይሰመባት፣ ምክንያቱ ምን እንደሆነ በመፈተሸ ክብርና ልዕልናዋ እንዲመለስ በቅዱስ ሲኖዶስ ቀርቦ ውይይትና ጥልቅ ምክክር እንዲደረግ መፍትሔም እንዲፈለግለት ጉባኤ ያሳስባል፤

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

15 Oct, 19:13


" ያገኘህን መከራ ሁሉ አመስግነህ ተቀበል፤ ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ ምንም ምን የሚደረግ እንደሌለ ዕወቅ "  (ሃ.አበ ምዕ 125 ፥ 11 )

እግዚአብሔር ለእኛ ይሻላል ብሎ ከሰጠን በላይ ለእኛ የሚሻል የሚሰጠን የለም።

እርሱ ባወቀ የሚጠቅመንን እንጂ የምንሻውን መልስ አይሰጠንም። ይኼ ለእኛ የተሻለ ይሆናል።  እኛ የምንሻው ደግሞ ለእኛ አሁን ተጎዳን ካልነው በላይ የሚጎዳን ይሆናል እርሱ ያለው ግን ሁል ጊዜም ለእኛ የተሻለ ነው

ጤንነት ለኃጢአት በሽታ ከሚዳርገን ይልቅ የሥጋ ደዌ ወደ ጽድቅ የሚያመራን ከሆነ ይህ ደዌ የአምላክ ጸጋ ሆኖልናል ማለት ነው።


ሰይጣን የተዋረደው ኢዮብ ደዌውን ስለ ታገሰ ብቻ ሳይሆን ስላላማረረ ነው ።  

ደዌ የሚቀለው ተመስገን ስንል ነው። የምናማርር ከሆነ ይህን የሚሻ ሰይጣን ከደዌ በላይ ተስፋ በመቍረጥ እንድንጓዳ ያደርገናል ወደ ማማረር በመድረሳችን ይህንን እርሱ (ሰይጣን) የሚሻው ነውና ዘወትር ፈተና ያደርግብናል እናም ሕመም የሚከብደው ሲያማርሩበት ነውና ደዌው እንዲቀልል ተመስገን እንበል🙏

ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ካሎት በ @fenote_Abew_bot ያስቀምጡልን።

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ https://t.me/fenote_abew

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

12 Oct, 18:36


#ቀጸላ_መንግሥቱ_ለጊዮርጊስ

በማኅሌተ ጽጌ ቁመት በየሳምንቱ አዲስ ቃለ እግዚአብሔር የሚደርስ ሲሆን ነገር ግን በሁሉም ሳምንታት ዘወትር እንዘ ተሐቅፊዮ እና ክበበ ጌራ ወርቅ ይባላል።

-> አባ ጽጌ ድንግል እመቤታችንን ከሰማዕቱ ጊዮርጊስ ጋር በምሥጢር አገናኝቷቸዋል :-
" ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እም ዕንቊ ባሕርይ ዘየሐቱ ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ ወለክኒ ይሰግድ ውእቱ ፤
የስሙና የሞቱ መታሰቢያ በአንቺ የተጻፈብሽ የሚያበራ ከሆነ ዕንቍ ባሕርይ ይልቅ የጠራ ወርቅ ክበብ ያለው የራስ ቍር የተባለ የጊዮርጊስ የመንግሥቱ የራስ ልብስ ጌጥ ሽልማት የአበባ አክሊል ማሪያም ሆይ አንቺ ለርሱ ሁሉን ታንበረክኪለታለሽ እርሱ ግን ለአንቺ ይሰግዳል " (አባ ጽጌ ድንግል)

-> አባ ጽጌ ድንግል ይህንን ቃል የወሰደው ከሰማዕቱ ከዜና ገድሉ ነው
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሰባ ነገሥታት ጋር ለሰባት 0መት ተጋድሎ ሲያበቃ ሰማዕትነት በተቀበለ ጊዜ ከአንገቱ ደም ውሃ ወተት ፈሰሰ ጌታችንም ለሰማዕቱ " ወአልበሶ ልብሰ ብርሃን ... ወአስተቀፀሎ በጌራ ወርቅ ጽሩይ ዘልቡጥ በአዕናቊ ባሕርይ ፤ በዕንቊ ባሕርይ ያጌጡ ከጽሩይ ወርቅ የተሠሩ መከራ በተቀበለባቸው ሰባት ዐመታት ልክ ከዕፀ ሕይወት አበቦች የተሠሩ አክሊሎች ያሉበት ዘውድን አቀናጀው" ያለውን ነው ሊቁ ጽጌ ድንግል የወሰደው።

1- ፍልስተ ሥጋው ከፍልስተ ሥጋው ጋር የተገናኘለት በመሆኑ ፦

-> በዚችም ዕለት ዳግመኛ የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋው ከፋርስ አገር ወደ አገሩ ልዳ በክብር የፈለሰበት ነው። የሥጋውም ፍልሰት ከእመቤታችን ድንግል ማርያም የሥጋ ፍልሰት ጋር አንድ ሁኗልና ስለዚህም እርሷን መውደዱ የሚያውቁ ሥዕሉን ከሥዕሏ አጠገብ ይሥላሉ በስሙ ለሚማፀኑ የድኅነት ወደብ ይሆን ዘንድ።

በፍልሰትኪ ድንግል ዘተቶስሐ ፍልሰተ ዐፅሙ። እንዘ ይብል ሶበ ጸለየ ኀቤሃ ቀዲሙ። ምስለ ፍልሰትኪ ደምርኒ እሙ።" እንዲል።  (አርኬ ፦ መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ ፲፮)።

2 - ትምእርተ ስሙ ማር ጊዮርጊስ ማር ማለት በሶሪያ ቋንቋ ቅዱስ ማለት ነው ለሴት ማርት ሲሆን ቅድስት ማለት ነው። ስለዚህ ማር ጊዮርጊስ ሲል ቅዱስ ጊዮርጊስ ማለት ሲሆን ማር የሚለው ስሙ ከእርስዋ ማርያም ከሚለው ስም በሁለቱ ፊደል ተሳትፏልና ትምእርተ ስሙ ስለሆነችለት "ሰላም ለጊዮርጊስ ተውላጠ ፃማሁ ወሕማሙ። እንተ ተለዓለ ሞገሰ ስሙ። " አለ

3- ዜና ገድሉ እንደሚነግረን ሰማዕቱ ሦስት ጊዜ ሞቶ ተነስቶ በአራተኛው ሞቱ ሕይወተ ሥጋው ተፈጽሞ አክሊል ተቀናጅቷል፤ በዚህም አራት ፊደል ካለው "ማርያም" ከተባለው ስሟ ጋር ተገናኝቶለታልና የስሙ እና የሞቱ መታሰቢያ ከእርሷ ተሰማምቶለታልና ሊቁ
"የስሙና የሞቱ መታሰቢያ በአንቺ የተጻፈብሽ " አለ።

-> እመቤታች በደብረ ምጥማቅ በምትገለጽ ጊዜ ከሁሉ ሰማዕታት ቀድሞ መጥቶ ከፈረሱ ወርዶ የሚሰግድላት ሰማዕቱ ነው እርሱ ሰግዶ በተነሳ ጊዜ ሌሎች ደግሞ ለእርሱ ይሰግዱለታልና ሊቁ  " አንቺ ለርሱ ሁሉን ታንበረክኪለታለሽ እርሱ ግን ለአንቺ ይሰግዳል " አለ ።
-> ዳግመኛም ቅዱስ ጊዮርጊስን ያንገላታ የነበረው ንጉሥ ዱድያኖስ ንግሥት እለስክንድርያ የምትባል ሚስት ነበረችው። መሳፍንቱና መኳንንቱ ኹሉ ለእርሷ ይሰግዱ ነበር። በሰማዕቱ ትምህርት አምና ለቅዱስ ጊዮርጊስ የፀጋ ስግደትን ሰገደችለት። በዚህም ምክንያት በሚያዝያ 15 አንገቷን በሰይፍ እንድትቆረጥ ተደርጋለች።
ያቺ ሣር ቅጠሉ ኹሉ ይሰግድላት የነበረች ንግሥት ለቅዱስ ጊዮርጊስ መስገዷን ያስተዋለው ሊቁ ግን በማኅሌተ ጽጌው "አንቲ ኲሎ ታሰግዲ ሎቱ - አንቺ ለእርሱ ኹሉን ታሰግጂለታለሽ" ሲል በእመቤታችንና በሰማዕቱ ምስጋና ላይ ዘከራት።
ይቆየን

ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ካሎት በ @fenote_Abew_bot ያስቀምጡልን።

ቤተሰብ ይሁኑ
👉TELEGRAM https://t.me/fenote_abew

👉FACEBOOK https://www.facebook.com/profile.php?id=100040602775882

👉 YOUTUBE https://www.youtube.com/@finoteabew

👉TIK TOK https://www.tiktok.com/@fenoteabew_zetewahido?_t=8mB9Wj5mAPV&_r=1

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

11 Oct, 05:37


“አንድ ምንም እውቀቱና ልምዱ የሌለው ሰው ዝም ብሎ መሬት ስለ ቆፈረ ብቻ ወርቅ አያገኝም፡፡ ከዚያ ይልቅ ምንም ረብሕና ጥቅም የሌለውን ድካም ያተርፋል እንጂ፡፡ ባስ ካለም የቆፈረው ጉድጓድ ተደርምሶበት ሕይወቱን ሊያጣ ይችላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት እንደሚነበብና እንዴት መረዳት እንዳለበት ያለወቀ ሰውም ይህን ሰው ይመስላል፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ  አፈወርቅ

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

05 Oct, 12:21


#የዘመነ_ስደት_መታሰቢያ_ለምን_በዚህ_ጊዜ_ሆነ?
ከመስከረም 26 እስከ ህዳር 5

✥      እመቤታችን ከልጅዋ ጋር ስደትን የጀመረችው ጥር 3 ነው፥ አገረ ግብጽ የገባችው ግንቦት 24 ነው፥ በግብፅ እና በኢትዮጵያ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ከቆዩ በኋላ ስደቱ አብቅቶ ተመለሱ ብሎ መልአኩ ሲነግራቸው ካሉበት ተነስተው ቁስቋም ከተባለች ቦታ ኅዳር 6 ደርሰዋል ።

#የስደት_መታሰቢያ_ለምን_በመነሻው_ጥር_3_አልሆነም?

ይህ ወቅት ዘመነ አስተርእዮ የደስታ ጊዜ ነው ታህሳስ 29 ልደቱን ጥር 11 ጥምቀቱን የምናከብርበትና በልደቱ እና በጥምቀቱ የተደረገልንን እያሰብን ደስ የምንሰኝበት ጊዜ በመሆኑ ለስደት መታሰቢያ ለማድረግ አይመችም።

#ግንቦት_24_አገረ_ግብፅ_የገባችበትን_ይዘን_ለምን_ስደትን_አናስብም?

ግንቦት 24 በዓለ ሃምሳን የምናከብርበት እንደመሆኑ በዚህ ወቅት ጌታችን በትንሳኤው የሰጠንን ነጻነት የምናስብብት ደስ የምንሰኝበት ጊዜ ስለሆነ መስገድ መጾም ስለማይፈቀድ የስደት መታሰቢያ ለማድረግ አይመችም።


✥      ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ዕፅዋት አበባን ፍሬን የሚያሳዩበት ወቅት ነው።

-   ወቅቱ ለምሳሌ የተመቸ ነውና።

« ትወጽእ በትረ እምሥርወ እሤይ ወየዓርግ ጽጌ እምኔሃ » (ት ኢሳ11፥1) እንዲል የእሤይ የዘር ግንድ ከተባለች ከእመቤታች ጽጌ ጸኣዳ ወቀይህ የተባለ የፍጥረት ሁሉ ጌጥ ጌታችን የተገኘ ነውና በዚህ መስሎ ለማስተማር የሚያመች ወቅት ነውና። በተጨማሪም ጽጌ በእመቤታች ፍሬ በጌታችን ይመሰላል

#አንድም፦ ተመለሰ ከማለት በፊት ተሰደደ ማለት ይቀድማል።

— በዓመት ውስጥ ያሉት የወራት ቅድመ ተከተል ኅዳር 6 ከጥር 3 እና ከግንቦት 24 ይቀድማል። ኅዳር ላይ ከስደት ተመለሰ ብለን ካከበርን በኋላ ጥር ተሰደደ ግንቦት ግብፅ ገባ ብንል አመቺ አይደለም።

ስለዚህ ከጥር 3 ወይም ከግንቦት 24 ይልቅ ኅዳር 6 መታሰቢያ ለማድረግ አመቺ በመሆኑ ቤተክርስቲያን በዚህ ወቅት የስደቱን መታሰቢያ ታደርጋለች።

✥     በቅዱስ ያሬድ አባባል ስደት ከመስከረም 26 እስከ ጥቅምት 20 ሲነገር፤ ከጥቅምት 21 እስከ ኅዳር 6 ድረስ ሚጠት (መመለሳቸው) ይነገራል። ይኼውም ተመየጢ ተመየጢ ሰላመ ሰጣዊት የሚለው ሰላም እንዲቀርብ በማህሌት ስለተወሰነ ነው።

ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ካሎት በ @fenote_Abew_bot ያስቀምጡልን።

ቤተሰብ ይሁኑ
👉TELEGRAM https://t.me/fenote_abew

👉FACEBOOK https://www.facebook.com/profile.php?id=100040602775882

👉 YOUTUBE https://www.youtube.com/@finoteabew

👉TIK TOK https://www.tiktok.com/@fenoteabew_zetewahido?_t=8mB9Wj5mAPV&_r=1

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

05 Oct, 05:56


✥✥✥ ተቀጸለ ማኅሌተ ጽጌ ✥✥✥


✥   በቤተክርስቲያናችን ዘመነ ጽጌ ከመስከረም 26 - ህዳር 5 ቀን በማኅሌት በየሳምንቱ እሑድ እሑድ (በተለምዶው ቅዳሜ ሌሊት በሚባለው)  በስብሓተ ነግሕ /መኀልየ ሰሎሞን በመቆም/ በማኅሌተ ጽጌ በዘወትርም ጸሎትና ስብሐተ እግዚአብሔር ታከብራለች፡፡

✥      አባ ጽጌ ድንግል ማኅሌተ ጽጌ/ የተባለውን ድርሰት ደርሰዋል፡፡ የተወለዱትም በሰሜን ሸዋ በይፋት አውራጃ ውስጥ ሲሆን መጀመሪያ ኢ አማኒ /ያለመነና ያልተጠመቀ/ ነበር፡፡ ከዕለታት ኣንድ ቀን ይህ ሰው በወጣትነት እድሜው ኣውሬ ለማደን ወደ ጫካ ሄደ በጫካ ውስጥም ፊቷ በጽጌረዳ አበባ የተከበበና ያጌጠ እጅግም ደስ የምታሰኝ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ዓይቶ በሥዕሏ ውበት እየተደነቀ ሳለ ጓደኛው መጥቶ ምን እየፈለክ ነው? ይህ እኮ የክርስቲያኖች ሥዕል ነው በማለት በያዘው በትር ሥዕሏን ሲመታት ወዲያው ተቀስፎ ሞተ፡፡ ከዚህ በኋላ ክንፎቹ በጽጌረዳ አበባ ያጌጡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በነጭ ወፍ ተመስሎ ወደ እርሱ መጥቶ ኣንድ ቀይ መነኩሴ እስከሚመጣ ድረስ ይህችን ሥዕል ጠብቃት ብሎ ተሰወረ፡፡

✥      ኢትዮጵያዊው ጻድቅ መነኩሴ አቡነ ዜና ማርቆስ በይፋት ኣውራጃ በነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት ምዕ፲፩÷፩ “ትውፅእ በትር እምሥርወ እሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ ”  የሚለውን በግእዝ ቋንቋ ሲያነብ በሰማ ጊዜ ኣባቶቼ አይሁድ የነቢያት ትንቢት ንባቡን ኣስተምረውኛል አውቀዋለሁ ትርጉሙ ግን አላውቀውምና ተርጉምልኝ አለው፡፡

✥     አቡነ ዜና ማርቆስም ሲተረጉምለት እንዲህ አለ ትወፅእ በትር እምሥርወ እሴይ የሚለው ንባብ ከእሴይ ነገድ የሕይወት በትር የሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትወለዳለች ማለት ነው፡፡ ወይወርድ ጽጌ እምኔሃ የሚለው ንባብ ደግሞ እመቤታችን ተወልዳ ከእርሷም ጌታ በድንግልና ይወለዳል፡፡ ከጌታም ክብር ይገኛል ማለት ነው፡፡ ይህም ጌታ ተወልዶ ትንቢቱ በእውነት ተፈጽሟል ብሎ ተረጎመለት፡፡ ( ት ኢሳ፯÷፲፬ ማቴ፲፰፡፳፬ )


✥     ይህ ሰው በዚህ ትርጉም ደስ ተሰኝቶ ኣባት የኢሳይያስን ትንቢት በመልካም ሁኔታ ተረጎምከው መልካም ነገር ተናገርክ አለውና ሥዕሏ ወዳለችበት ቦታ ወስዶ ታሪኩ ላይ እንደተገለጸው በጫካ ውስጥ ያያትን ሥዕል ጓደኛው በያዘው በትር ሲመታት ወዲያው እንደተቀሰፈና ክንፎቹ በጽጌረዳ አበባ ያጌጡ አንድ ነጭ ወፍ የሆኑ (ቅዱስ ሩፋኤል) ወደ እርሱ መጥቶ ቀይ መነኩሴ እስከሚመጣ ድረስ ይህችን ሥዕል ጠብቃት ብሎ በሰው አነጋገር ያነጋገረውን ሁሉ ነገረው፡፡

✥      አቡነ ዜና ማርቆስ የተደረገውን ሰምቶ እጅግ ደስ አለውና በል በመጀመሪያ እመቤታችን በድንግልና በወለደችው በአብ የባሕርይ ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን ይህችን ሥዕል ያስገኘው ሰማይና ምድር በውስጣቸው ያለውን ሁሉ የፈጠረ እርሱ እንደሆነ እወቅ አለውና በኣብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቆ ጽጌ ብርሃን /ጽጌ ድንግል/ ብሎ ሰየመው፡፡


✥     ማኅሌተ ጽጌ ማለት ማኅሌት የሚለው ቃል የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ምስጋና ማለት ነው፡፡ ጽጌ ማለት እንደሱ የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙ አበባ የፍሬ ምልክት ማለት ነው፡፡ ማኅሌት ጽጌ ተብሎ በአንድነት ሲነገር ሲተረጎም ደግሞ የኣበባ ምስጋና ማለት ነው፡፡ ይህም ድንግል ማርያም የማኅጸኗ ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎችና ፍሬዎች እየተመሰሉ የሚመሰገኑበት ምስጋና ማለት ነው፡፡


✥      ማኅሌተ ጽጌን በግጥም /ቅኔ/ ስንኝ በ5 በ5 የተደረሰ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ድርሰት ነው፡፡
ይህ ድርሰት በቤተክርስቲያን ኣገልግሎት የሚውለው በዘመነ ጽጌ እሑድ እሑድ (በተለምዶ ቅዳሜ ሌሊት በሚባለው)  በሚቆመው ማኅሌት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ሙሉ ድርሰቱ በዜማ በጽናጽልና ከበሮ የሚዘመር ሲሆን በዘወትርና በዓመት በዓላትም በሚቆም ማኅሌት በዓሉን የሚመለከተው ክፍል እያንዳንዱ እየወጣ በዜማና በጽናጽል ይዘምራል፡፡


✥     በሃገራችን የመስከረምና የጥቅምት ወራት የኣበባ ወራት /ዘመነ ጽጌ/ ይባላል፡፡ ይህም ወቅት ተራሮችና ሜዳዎች በኣበባ የሚያጌጡበትና ለዓይን ማራኪ የሚሆኑበት ጊዜ ነው፡፡

-    በዚህ ዘመን ጌታችን ፈጣሪአችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለልብስ ለምን ትጨነቃላችሁ የሜዳ አበቦች እንዴት እንደሚያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፡፡ አይደክሙም ኣይፈትሉም ነገር ግን እላችኋለሁ ሰሎሞን እንኳ በክብሩ ሁሉ ከእነዚህ እንደ ኣንዱ አልለበሰም ብሎ በአበባ ምሳሌነት የሰው ልጆች ስለ ልብስ እንዳይጨነቁ አስተምሯል፡፡ ( ማቴ፭÷፳፰-፴፫ )

-    ንጉሥ ዳዊትም ተዘከር እግዚኦ ከመ መሬት ንሕነ ወሰብእሰአ ከመ ሣዕር ወዋዕሊሁ ወከመጽጌ ገዳም ከማሁ ይፈሪ ኣቤቱ እኛ ኣፈር እንደሆነ ኣስብ ሰውስ ዘመኑ እንደ ሣር ነው እንደ ዱር አበባም እንዲሁም ያብባል ነፋስ በነፈሰበት ጊዜ ያልፋል (መዝ ፻፪፥፲፬-፲፮/) በማለት እንደተናገረው ሣር በቅሎ አድጎ አብቦ ፀሓይ በወጣ ጊዜ ይደርቅና በሞት ነፋስ ይወሰዳል፡፡


✥     አባ ጽጌ ድንግል የደረሰው ማኅሌተ ጽጌም ምሥጢሩ ከእነዚሁ የቅዱሳት መጻሕፍት መልእክታት ጋር ተቀራራቢ ነው፡፡ የማኅሌተ ጽጌ ብዛቱ 150 ነው፡፡ ጽጌ አስተርአየ ሠረጸ አምአጽአሙ አበባ ከአጥንቱ ወጥቶ ታየ ብሎ ይጀምራል፡፡ አጥንት ያለው እንጨቱን ነው፡፡ ዕፅ እመቤታችን አበባው ልጅዋ ኢየሱስ ነው በማኅሌተ ጽጌ ኣበባ ጌታ ሲሆን እመቤታችን ዕፅ ትባላለች ፍሬ ጌታ ሲሆን እመቤታችን አበባ ትባላለች፡፡

✥    ማኅሌተ ጽጌ በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን አሜን ::

ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ካሎት በ @fenote_Abew_bot ያስቀምጡልን።

ቤተሰብ ይሁኑ
👉TELEGRAM https://t.me/fenote_abew

👉FACEBOOK https://www.facebook.com/profile.php?id=100040602775882

👉 YOUTUBE https://www.youtube.com/@finoteabew

👉TIK TOK https://www.tiktok.com/@fenoteabew_zetewahido?_t=8mB9Wj5mAPV&_r=1

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

04 Oct, 19:31


የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትን ለመመርመር በጠቅላይ ቤተ ክህነት የተቋቋመውን አጥኚ ኮሚቴ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ።

መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በቁጥር 782/354/2017 ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ለአጣሪ ኮሚቴ በአድራሻ ሲጻፍ በተመዘገበልን ግልባጭ ለመገንዘብ እንደቻልነው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የሚስተዋሉ የአመራር ግድፈቶችንና በአሠራር ላይ እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮችን አጥንቶ የሚያቀርብ ኮሚቴ መቋቋሙን ተረድተናል፡፡

ለኮሚቴው መቋቋም ምክንያቱ “በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የሚስተዋሉ የአሰራር ግድፈቶች ላይ የተፈጠሩ ችግሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሱ በአገልጋይ ካህናትና ልዩ ልዩ ሠራተኞች ላይ ከፍተኛ ችግር እያስከተሉ መሆኑ” እንደሆነ በደብዳቤ ተገልጿል፡፡ የአጥኚ ኮሚቴው አባላትም አመራረጥ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ከምእመናን እና ከማኅበራት የተውጣጡ መሆኑንም ተረድተናል፡፡
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጠቅላይ ቤተ ክህነት አቋቋምኩት ያለውን ኮሚቴም ሆነ በኮሚቴ ስም የሚቀርብን የጥናት ሪፖርት በሚከተሉት ምክንያቶች የማይቀበለው መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡-

1. ጠቅላይ ቤተ ክህነት አጥኚ ኮሚቴ ያቋቋመው ምንም ዓይነት ለኮሚቴው መቋቋም የሚያበቃ ቅሬታ ሳይቀርብለት እና በማስረጃ የያዘው አቤቱታና ወቀሳ ሳይኖር በመላምት እና በግል ስሜት በመነሳሳት አጀንዳ ለመፍጠር እንደሆነ የተቋቋመው ኮሚቴ በመግቢያ ስብሰባው ለከሳሾች ካቀረበው ጥሪ እና ማስረጃ ፍለጋ ካስተላለፈው መልእክት ለመገንዘብ ችለናል፡፡ይህ በመሆኑም በሀገረ ስብከታችን ላይ ሰዎች ክስ እንዲያቀርቡ የሚያነሳሳ መግለጫ ለመስጠት የተገደደው ቅሬታ ሳይቀርብ በአየር ላይ ማስረጃ የተቋቋመ ስለሆነ ነው።

2. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚታይ የአስራር ችግር ካለ አንዱና ዋነኛው የችግሩ አካል ጠቅላይ ቤተ ከህነቱ ነው፡፡ ለዚህም ማሳያ ለ2015 ዓ.ም ለሀገረ ስብከቱ መተዳደሪያ ደንብ አርቅቆ አጸድቆ ሲሰጥ ፣ አስተዳደር ጉባኤውን በትኖ አዲስ አስተዳደር ጉባኤ በመሰየም፣ ከሕግ ውጪ በሀገረ ስብከቱ የውስጥ አሠራር ጣልቃ የሚገባው ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ መሆኑ የዐደባባይ ምስጢር ነው፡፡ በሌላም በኩል በተለያዩ ጊዜያት ከሀገረ ስብከታችን ጥያቄ ሳይቀርብ ሠራተኛ እየመደበ በግዳጅ የሚያሠራን በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን አማካኝነት በማስረጃ ያልተደገፉ ከአሉባልታ ያልዘለሉ ነገር ግን የሀገረ ስብከቱንም ሆነ የቤተክርስቲያኑን ስም የሚያጠፉ ዘመቻ በተገኘው ዐውደ ምሕረት የሚያስተላልፈው ሆን ተብሎ የሀገረ ስብከቱን ስም እና የሊቀጳጳሱን የአሠራር ሂደት ለማጠልሸት አነጣጥሮ እና አልሞ የቅስቀሳ ሥራ የሚሠራው ጠቅላይ ቤተክህነቱ ነው፡፡

የዚህ ችግር አካል የሆነው ጠቅላይ ቤተክህነት ራሱን እንደገለልተኛ እና ንፁሕ አካል አድርጎ በመቁጠር በሌለ ሕግ እና አደረጃጀት በቤተክርስቲያኗ ላይ ፈላጭ ቆራጭ ሆኖ እራሱን በመቁጠር ያቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ልንቀበለው አንችልም፡፡ማጣራት የሚያስፈልግ እንኳ ቢሆን አጣሪ ሊሰየም የሚገባው የሁለቱም መዋቅሮች የበላይ በሆነው በቅዱስ ሲኖዶስ ነው።

3. የተቋቋመው ኮሚቴ የቤተ ክርስቲያንን የአስተዳደር ሥርዓት ከአስተዳደሩ ውጪ ላሉ አካላት አሳልፎ ከመስጠት ባሻገር የቤተክርስቲያንን አስተዳደር ከአስተዳደር መዋቅር ውጪ ባሉ አካላት እንዲመረመር የሚፈቅድ ሕግ በሌለበት ሀገረ ስብከቱን ለእነዚህ አካላት አሳልፎ የሚሰጠውን የአጣሪ ኮሚቴ መሰየም ምን ዓይነት አጀንዳ ለመፍጠር እና ርካሽ ተወዳጅነትን ከመፈለግ አኳያ ነው እንጂ እውነት ለተቋሟ ታስቦ እንዳይደለ ስለምናውቅ ለመቀበል እንቸገራለን፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የምእመናን እና ማኅበራትን አጥኚ ኮሚቴ ውስጥ ያካተተው ሆን ተብሎ ሀገረ ስብከቱን ከምእመናን እና ከማኅበራት ጋር በማጋጨት የእራስን ስውር አላማ በሦስተኛ ወገን  ለማስፈጸም እና የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተዳደራዊ  መዋቅር ለመናድ ታሳቢ  ያደረገ  እንጂ  አሠራሩን  የሚፈቅድ  ሕግ ኖሮ አይደለም።

4. የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለአስተዳደር እንዲያመች የተዋቀሩ የአስተዳደር እርከኖች ቢሆኑም ሁለቱም የሚመሩት ተጠሪነታቸው ለቅዱስ ሲኖዶስ በሆኑ ሊቃነ ጳጳሳት ሆኖ ሳለ የተሰየመው አጥኚ ኮሚቴ የአንድን ሊቀ ጳጳስ የአመራርነት ሒደት ከቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መዋቅር ውጪ በሆነ አካላት እንዲመረመር የሚያደርግ በመሆኑ ሀገረ ስብከታችን አይቀበለውም፡፡ ሕግ እና አሠራር ባይፈቅዱም ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ ባሉ የቤተክርስቲያን አስፈፃሚ አካላት የአሁኑ መርማሪ ምርጫ ሂደት ተቀባይነት የለውም እንጂ ይሁን እንኳ ከተባለ አንድ ሊቀጳጳስ መጣራት ያለበት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በሊቃነ ጳጳሳት በሚመራ ልዑካን ሊሆን እንደሚገባ አንጠራጠርም፡፡

5. የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በምጣኔ ሃብት ስፋት እና ባሉት አገልጋዮች ብዛት እንዲሁም ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኝ ሆኖ ለጠቅላይ ጽ/ቤቱ ቅርብ መሆኑ ለእይታ እና ለክትትል ምቹ ሁኔታን ፈጥሮ ካልሆነ በስተቀር ከሌሎች አኅጉረ ስብከት የሚለይበት ምንም ዓይነት ምክንያት እንደሌለ ሕገ ቤተክርስቲያኑ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡ በሀገረ ስብከታችን ስራ እስከሰራን ድረስ የአስራር ችግሮች የለብንም ፍፁማን ነን ብለን አናምንም ቢኖሩም እንኳን ከሌሎች አኅጉረ ስብከት የተለየ የአስተዳደር ችግር የለበትም፡፡ በአሁኑ ሰዓት በተለያዩ አኅጉረ ስብከት የሚስተዋሉ አለመግባባቶች እንዳሉ እየታወቀ  የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን ብቻ ለይቶ  የሚያጠና አካል መሰየሙ ምክንያታዊ አይደለም።

6. ጠቅላይ ቤተ ክህነት በየጊዜው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን የፋይናንስ ሒደት የምርመራ ኦዲት እያደረገ በዚህም ሂደት ያገኘው ጉድለት ኖሮ የወሰደው የማስተካከያ እርማት ሳይኖር እንዲሁም ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የሀገረ ስብከቱን የሰው ኃይል ቅጥር እድገትና ዝውውር ምክንያት በማድረግ ቅሬታ ቀረ በልኝ በማለት በተደጋጋሚ ምርመራ ያደረገ ቢሆንም በተለይም በቅርቡ በአስተዳደር ጉባኤ ውሳኔ የተሰየሙ አጣሪዎች በአካል ቀርበው በሰነድ በመስክ ጉብኝት እንዲሁም በቪዲዮ ጭምር የተቀረጸ ማጣራት ተደርጎ የተገኘ ጉድለት ወይም የተሰጠ ማስተካከያ መመሪያ ሳይኖር አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በድጋሚ አጣሪ መሰየሙ አሳማኝ ሆኖ ስላላገኘነው አንቀበልም፡፡

7. የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የአሁን ድርጊት ከመዋቅር ውጪ ያሉ አካላትን የቤተ ክርስቲያን መዋቅርን እንዲያጠና በማድረግ ቀደም ሲል በኦሮሚያ እና በትግራይ ባሉት አኅጉረ ስብከት የተከሰተውን ችግር ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚያስፋፋ ሁከት የሚያነግስ በመሆኑ አንቀበለውም፡፡

    ስለዚህ ከላይ በዝርዝር የተቀመጡትን ምክንያቶች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በጠቅላይ ቤተ ክህነት መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም የተቋቋመውን አጣሪ ኮሚቴ እና በስሙ የሚቀርበውን ሪፖርት እንደማይቀበለው የአስተዳደር ጉባኤ የወሰነ መሆኑን ስንገለጽ ይህ ጉዳይ ለሀገረ  ስብከታችን ብሶት እና ችግር መግለጫ ቢሆንም በግልባጭ የምናሳውቃችሁ የበላይ አካላት እና  መንግስታዊ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ስልጣንን መከታ በማድረግ በሀገረ ስብከቱ እየደረሰ ያለውን ፀብ አጫሪነት በትኩረት እንድትከታተሉት ከአደራ ጋር እናሳስባለን፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት

ምንጭ የአዲስ አበበ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

01 Oct, 07:24


#መስከረም_21

#ብዙኃን_ማርያም

በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ የመጀመሪያው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡ ሁለቱንም ታሪኮች ከዚህ ቀጥለን እንመለከታቸዋለን፤

#ጉባዔ_ኒቅያ
በ፫፻፳፭ ዓ.ም አር*ዮስ የሚባል መ*ና*ፍ*ቅ የእግዚአብሔር ወልድን የባሕርይ አምላክነት አልቀበልም በሚል ክህ*ደት እርሱ ተሰናክሎ ለሌሎችም መሰናክል ኾነ፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት አር*ዮስ ክህ*ደቱን እንዲተው ቢመክሩትም ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይህ የአር*ዮስ ክህ*ደትም በሊቃውንቱ መካከል መለያየትን ፈጥሯል፡፡ ጊዜው ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ‹‹አብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኀዋ፤ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ! አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ!›› የሚል ዐዋጅ የነገረበት ወቅት ነበርና ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በአር*ዮስ ክህ*ደት ምክንያት በኒቅያ የሃይማኖት ጉባኤ እንዲካሔድ በየአገሩ ላሉ ሊቃውንት መልእክት አስተላለፈ፡፡

በዚህም መሠረት ከሚያዝያ ፳፩ ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም ፳፩ ቀን ድረስ ፳፫፻፵፰ (ሁለት ሺሕ ሦስት መቶ ዐርባ ስምንት) ሊቃውንት በኒቅያ ተሰበሰቡ፡፡ ኒቅያ ለዚህ ጉባኤ የተመረጠችበት ምክንያትም ጳጳሱን ከማኅበረ ካህናቱ፤ ንጉሡን ከሠራዊቱ ጋር አጠቃላ ለመያዝ የምትችል ሰፊና ምቹ ቦታ ከመኾኗ ባሻገር ለኹሉም አማካይ ሥፍራ ስለ ነበረች ነው፡፡ በጉባኤው ከተሰበሰቡ ሊቃውንት መካከልም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ፣ ለምጽ ያነጹ፣ አንካሳ ያረቱ፣ የዕውራንን ዓይን ያበሩ ድውያንን የፈወሱ፣ ሌላም ልዩ ልዩ ተአምር ያደረጉ፤ እንደዚሁም ስለ ርትዕት ሃይማኖታቸው በመጋደል ዓይናቸው የፈረጠ፣ እጃቸው የተቈረጠ ይገኙበታል፡፡

ሊቃውንቱ ሱባዔ ይዘው በጸሎት ከቆዩ በኋላ ኅዳር ፱ ቀን በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት፣ በእለእስክንድሮስ አፈ ጉባኤነት ጉባኤው ተጀመረ፡፡ ንጉሡ ሊቃውንቱን "ስማችሁን፣ አገራችሁንና ሃይማኖታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ" ባላቸው ጊዜም ከ፳፫፻፵፰ቱ (2348) መካከል ፫፻፲፰ (318) ሊቃውንት ሃይማኖታቸውን ሲገልጹ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾነው "ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ፤ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ፣ በህልውና አንድ ነው" ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ንጉሡም "ሃይማኖት እንደ ፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት ይኹን" ብሎ ዐዋጅ አስነግሯል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በኦሪት ዘፍጥረት የተጠቀሱት ፫፻፲፰ቱ የአብርሃም ብላቴኖች ምሳሌዎች ናቸው /ዘፍ.፲፬፥፲፬/፡፡

፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮ*ስን አው*ግዘው በመለየት "ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን" የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡ ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር ፱ ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት መስከረም ፳፩ ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት "#ብዙኃን_ማርያም" እየተባለ ይጠራል፡፡ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሃይማኖታዊ ጉባኤ የተሳባሰቡበት ዕለት ነውና፡፡

#ዕፀ_መስቀል
በሌላ በኩል መስከረም ፳፩ ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤

ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር "የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡

ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡ መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡

መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ፲፬፻፵፮ (1446) ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡

ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም ፳፩ ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡ ኀጢአታቸውን ለካህን ተናዘው፣ ንስሐ ገብተው በዚህ ዕለት ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ በመሔድ የሚጸልዩና የሚማጸኑ ምእመናን ኹሉ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የምሕረት ቃል ኪዳን እንደሚያገኙም ጤፉት በተባለችው መጽሐፍ ተጠቅሷል፡፡

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

30 Sep, 19:19


✝️ብዙኃን ማርያም✝️

መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡  ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን ነው

፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮስን አውግዘው በመለየት ‹‹ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን›› የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡ ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር ፱ ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት መስከረም ፳፩ ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት ‹‹ብዙኃን ማርያም›› እየተባለ ይጠራል፡፡

ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ካሎት በ @fenote_Abew_bot ያስቀምጡልን።

ቤተሰብ ይሁኑ
👉TELEGRAM https://t.me/fenote_abew

👉FACEBOOK https://www.facebook.com/profile.php?id=100040602775882

👉 YOUTUBE https://www.youtube.com/@finoteabew

👉TIK TOK https://www.tiktok.com/@fenoteabew_zetewahido?_t=8mB9Wj5mAPV&_r=1

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

25 Sep, 06:42


ለደመራና መስቀል በዓል መስቀል ዐደባባይን የማጽዳት ሥራ ተከናወነ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በዓልን ምክንያት በማድረግ በመስቀል ዐደባባይ የፅዳት ሥራ አከናወነ፡፡

በጽዳት ሥራው ላይም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሃይማኖት መሪዎች እና ምዕመናን ተሳትፈዋል፡፡

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

17 Sep, 19:11


የኦርየንታል ኦርቶዶክስ እና የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት የነገረ መለኮት ውይይት ከ34 ዓመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ በካይሮ መካሄድ ጀመረ  !

ጉባኤው “የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል” (2ኛ ቆሮንቶስ 5፡14) በሚል መሪ ቃል በእምነት እና  እና በአገልግሎት እና በማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሂደዋል፤ ጉባኤው ትናንትና እና ዛሬ በግብጽ ቅዱስ ቢሾይ ገዳም “ሎጎስ” የስብሰባ ማዕከል መካሄድ የጀመረ ሲሆን በኦሪየንታል ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት እና በምሥራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መካከል ይፋዊ የነገረ መለኮት ውይይት በዚህ ስብሰባ ተካሂዷል። ዓላማው ከ30 ዓመታት በላይ የተቋረጠውን ይፋዊ የሥነ-መለኮት ንግግር እንደገና ለመቀጠል እና እንደገና ለመገምገም መሆኑን የግብጽ ቤተ ክርስቲያን አስታውቃለች።

ጉባኤው የተከፈተው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እና በፓትርያርክ አቡነ በርተሎሜዎስ ቀዳማዊ፣ መልእክት ነው።

በስብሰባው ላይ በሁለቱ አቢያተ ክርስቲያናት ቤተሰቦች ላይ የሚነሱ ልዩ ልዩ የአስተምህሮ ጉዳዮች ወደ አንድ ወጥ አቋም ለመድረስ በማለም በዚሁ ልክ ውይይት መደረጉ ነው የተገለጸው።

የምሥራቃውያን ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስቲያናት ልዑካንን ጨምሮ በጉባኤው  የአሌክሳንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ (አስተናጋጅ ቤተ ክርስቲያን)፣ የአንጾኪያ እና የመላው ምሥራቅ ፓትርያርክ (ሶርያ )፣ የአርመን ኦርቶዶክስ፣ የኦርቶዶክስ የኢትዮጵያ የኤርትራ አቢያተ ክርስቲያናት መወከላቸውን የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ገልጻለች።

ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ካሎት በ @fenote_Abew_bot ያስቀምጡልን።

ቤተሰብ ይሁኑ
👉TELEGRAM https://t.me/fenote_abew

👉FACEBOOK https://www.facebook.com/profile.php?id=100040602775882

👉 YOUTUBE https://www.youtube.com/@finoteabew

👉TIK TOK https://www.tiktok.com/@fenoteabew_zetewahido?_t=8mB9Wj5mAPV&_r=1

3,222

subscribers

943

photos

24

videos