ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞ @fenote_abew टेलीग्राम पर चैनल

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞
"አባቶችን ጠይቅ ይነግሩሀል፤የእምነትን ምስጢር ያስረዱሀል
አትለፍ የተዋህዶን ድንበር፤ በውጪ ተጥለህ እንዳቀር"

◈ ይህ ቻናል :- የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ስርዓት እና አስተምሮ የ ጠበቁ ወቅታዊ እና አስተማሪ ፤መንፈሳዊ ፅሁፎች የሚቀርቡበት ኦርቶዶክሳዊ ቻናል ነው።
ሀሳብ አስተያየት ካሎት በተጨማሪም ለpromotion

👉 @fenote_Abew_bot

https://t.me/fenote_abew
3,263 सदस्य
943 तस्वीरें
24 वीडियो
अंतिम अपडेट 10.03.2025 04:48

አባይቱ የመዋህዶ ገበሬነታት እና አርኪያዎች

በዚህ ጽሁፍ እንደ መረጃ እንደተገኘው ጉባኤ ላይ ያለ የኢዜይ እና የሐይማኖት እንደቱ የሚያስተምር ቻናል ይህ ፍኖተ አበው የዊስ ወይዘር ይዞል። ይህየ ኦርቶዶክሳዊ ቻናል የመወዓዝ ሀሳቦችን ለመስጠት በሚያቀርበው ዙሪያ ለመቀበያ ይዞል። እንግዲህ እንደሚባል ነገር እንደ ድንበራዊ እምነት የሚያስተካክል ከምስጢሩ ይኖር። እንዲህ በሆነ ብዙ ቀና የተመስረቱት በመሬት ላይ እንዲወደድ መርማር በህፃናት የአርክይቶማ ሀይማኖታዊ በሚወደድ ዅንጅሮች የሚቀመጥበት መስክ አይዞል።

ፍኖተ አበው የሚገኝ ዋና ዋና ጥናት ምንድነው?

ፍኖተ አበው እንደሚገኘው ዋና ቻናል ይመለከታል። ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ ሀይማኖትን እና አስተምሮ የሚያነሳቃቅቅ ነው። በዚህ ገለጻ በመማር ዝነክ የሚሰበሰቡ ተጨማሪ ኑሮን ይኖር።

የባለሙዝብ ምንጭ መርምር ይዞ በዘመነ እድገት ያለ የምስጢር ስር እንደሚኖሩ ላይ ይወስዳል።

የፍኖተ አበው ጥንቃቄ እንዴት ነው?

ጥንቃቄ የፍኖተ አበው የእምነት ፍንዳታ ምርጫ ይላይ። ይህ ኦርቶዶክሳዊ ችሎታን መለኪያ ይሰጣል።

ጥንቃቄ የተወሰነ መሳሪያ መዋዕል አካባቢው ይቅርታ ነው።

ይህ ቻናል ሞተን እንዴት እንደሚያሳይ?

ይህ ቻናል የእምነታቸውን ምስጢሮች በቻችን እንደ ኡዳ እንደሚሰፍሕ ይወዳዳል።

ይህ የሚገኝ ናት ቻናል የሚወደስ ጥፍር እና አስክራ ይዞን እንዳልናውም እንደ ወᕉሕሩ የለኝ ይህን

የአስተምሮው ቻናል ዋነኛ አይነት ምንድነው?

የአስተምሮ ቻናል ዋነኛ አይነት ይነሳል የምስጢር ወይዘር ይደቅ እንዳውርዳዕ ይመክር! ይቅርታ ሊገኝ ይሆን ከሚወደድ ይመር ይሆናል።

ይህ ክንዋናዊ ዕምነት ፈረዳ የሚወደድም ይወዳዳ.

ይህ ቻናል ዋነኛ ጠቀሜታ እንዴት አለይ?

ይህ ቻናል ዋነኛ ጠቀሜታ የአረቦር ወዴ አበው ይለኝ ይቅርታ የማስትን እንዴት ነው?

ይህ ዋነኛ ቻናል ኢንደ መዋዕል ይለይ ይገናኝ ይላል ወደ ዘመኔው ይህ ቻናል.

የፍኖተ አበው ኦርቶዶክሳዊ ውስጠሡ ጉዳዮች ምንድነው?

እንግዲህ ምንድነው? ይህ ቻናል ውስጠሡ ዝነክ ይኖረዋል ወደዚህ ገለጻችን ጉዳዮች ይመሰለው! በዚይ አክልን በምየው!

ይህ ዝነክ በምይጭ ዉስጠሡ ዝነክ ይሁን ይግጋሙ ይቅርታ.

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞ टेलीग्राम चैनल

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞ ማን ነው? ወደ ምን እንደሚታወቅ ትልቅ ስጦታ እንዲያለብሱ መዋሸት የሚሆነው ከሄኖታችን ዘርፉለሁበት ኦርቶዶክሳዊ ቻናል ነው። አባቶችን ጠይቅ ይነግሩሀል፤ የእምነትን ምስጢር ያስረዱሀል፤ አትለፍ የተዋህዶን ድንበር፤ በውጪ ተጥለህ እንዳቀር። ይህ ስጦታ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ስርዓት እና አስተምሮ የ ጠበቁ ወቅታዊ እና አስተማሪ ፤መንፈሳዊ ፅሁፎች የሚቀርቡበት ኦርቶዶክሳዊ ቻናል ነው። ከመለስ የሚቀረው @fenote_Abew_bot ይጠቀሙ። የቴሌግራም ገንዘብ በእኚኅ ላሉበት ላይ ትክክለኛ መንነት ሳታበርበን የሚያስቡበት ቻናል ነው።

ፍኖተ አበው ዘ✟ዋህዶ ✞ के नवीनतम पोस्ट

Post image

ዐቢይ ጾም (ጾመ 40 ዘጾመ ክርስቶስ)

ይህ ጾም ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ከርሰቶስ በተወለደ በ 30 ዓመቱ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንሰ እጅ ጥር 11 ቀን በዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ከጥር 12 ቀን እስከ የካቲት 21 ቀን ድረስ 40 መዓልትና ሌሊት ከቆመ ሳያርፍ ከዘረጋ ሳያጥፍ በትኅርምት በገዳመ ቆሮንጦስ የጾመው ጾም በመሆኑ ዐቢይ ተብሏል፡፡ [ማቴ. 4.1]፡፡ ጾሙ የተለየ፣ የከበረ፣ የተቀደሰ፣ የጸና፣ የተከለከለ እና እነዚህን የመሰሉ ተቀጽላ ስሞችን ያገኛል፡፡ እኛም ጌታ የጾመውን ለማስታወስ በረከቱን ለማግኘት በግብር እርሱን ለመምሰል የሥጋ ፈቃዳችንን ለነፍስ ፈቃዳችን ለማስገዛት እንጾመዋለን፡፡ ጌታችን የጾመው እቀደስ እከብር ወይም እነፃ ብሎ ሳይሆን ለእኛ አርአያ ለመሆን ነው፡፡ 

ለምን ጾሙን አርባ ቀንና አርባ ሌሊት አደረገው?
✓ እግዚአብሔር አምላካችን የፈጠረውን የሰው ልጆችን አባት አዳምን በልጅነት አክብሮ ገነት ያስገባው በፈጠረው በአርባ ቀኑ ነው፡፡ "ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር ዘገብሮ ለአዳም" አዳምን የፈጠረ እግዚአብሔር ቅዱስ ነው እያሉ እያመሰገነ መላእክት ወደ ገነት አስገብተውታል፡፡ [ቀሌ 4]

✓ ለአዳም አርባ ቀን ከተፈጸመለት በኋላ ወደ ገነት አስገባው፡፡ ሔዋንንም በኹለት አርባ ማለትም በሰማኒያ ቀኑዋ ወደ ገነት አስገባት፡፡ [ኩፋ. 4:12]፡፡ 

✓ በተጨማሪም አዳም ትእዛዘ እግዚአብሔርን ካፈረሰ በኋላ ዲያቢሎስ በአቋራጭ መጥቶ አስወጣው እንጂ ሱባኤ የገባው ለአርባ ቀናት ነበር፡፡ ይህን አርባ ቀን የሰው ልጆች ከስሕተት በኋላ በቀንም ሆነ በዓመት ለጾም፣ ለሱባኤ፣ ከዚያ አልፎ ለመትነት አገልግሏል፡፡

✓ በኦሪት ዘፍጥረት እንደምናነበው የሰው ልጅ በንፍር ውኃ የተቀጣው አርባ መአልትና ሌሊት ነበር፡፡ "አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በምድር ላይ ዝናብ አዘንባለሁና የፈጠርሁትንም ፍጥረት በምድር ላይ አጠፋለሁና፡፡" [ዘፍ. 7:12]፡፡ የሰማይ መስኮቶች ተከፈቱ ዝናቡም አርባ መአልትና አርባ ሌሊት በምድር ላይ ሆነ፡፡ [ዘፍ. 7:12]፡፡

✓ በዚህ ዓይነት አርባ ቀን እግዚአብሔር ሰውን እንደ ቀጣበት እናያለን፤ መቅጣት ብቻ ሳይሆን በዚህ የአርባ መአልትና የአርባ ሌሊት ምድር በዛበት ርኲሰት አጥቧታል፡፡ ምክንያቱም የጥምቀት ምሳሌ ነውና፡፡ ማየ አይህ (የጥፋት ውኃ የጥምታት ምሳሌ ለመሆኑ ቅዱስ ጴጥሮስ እንዲህ በማለት ጽፏል "ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍሳት በውኃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቆየ ጊዜ ቀድሞ አልታዘዙም ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፡፡" [2ኛጴጥ.3.20 ና 21]፤ አሁንም ከዚሁ ሳንርቅ የመርከቧ መስኮቶች የተከፈቱት በአርባ ቀን መሆኑን ይገልጻል፡፡ "ከአርባ ቀን በኋላ ኖኅ የሠራውን የመርከቢቱን መስኮት ከፈተ" [ዘፍ. 8.6]፡፡ መርከቧ የቤተክርስቲያን ምሳሌ ናት፡፡ እስራኤል ወደ ምድረ ርስት ያደረጉት ጉዞ አርባ ዓመት እንደ ፈጀ ተጽፏል፡፡ ይህም መንገድ ደግሞ የአርባ ቀን መንገድ ነበር፤ በእግዚአብሔር ቁጣ ወደ አርባ ዓመታት ተለወጠ እንጂ፡፡ "በሙሴ ተመርተው ከግብጽ የወጡ ሁሉ አይደሉምን? አርባ ዓመትም የተቆጣባቸው እነማን ነበሩ? ሬሳቸው በምድረ በዳ የወደቀ" [ዕብ. 3.7-19] ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ጽፎታል፡፡

✓ እስራኤል አርባ ዘመን መና ከደመና እየወረደላቸው ተመግበዋል፤ ውኃ ከዐለት እየፈለቀላቸው ጠጥተዋል፡፡ ሲያምጹም ተቀጥተዋል፡፡ ሙሴ ወንድሞቹን እስራኤልን ለመጎብኘት የመጣው በአርባ ዓመት ነበር "በዚያም ወራት እንዲህ ሆነ ሙሴ ጎበዝ በሆነ ጊዜ ወንድሞቹ ወጣ የሥራቸውን መከራ ተመለከተ" [ዘጸ. 3:11፤ ሐዋ. 7:23] የተሰደደውም በዚሁ ዕድሜው ነው፡፡ በምድያም በግ በመጠበቅ አርባ ዘመን ኖሯል፡፡ እንደገና እስራኤል ከግብጽ ባርነት ነጻ እንዲያወጣ እግዚአብሔር የላከው በአርባ ዘመን ነበር፡፡ "አርባ ዓመትም ሲሞላ የጌታ መልአክ በሲና ተራራ ምድረ በዳ ታየው፡፡" [ዘጸ. 3:30]፡፡

✓ ይህም ብቻ አይደለም ሙሴ ለዚህ አገልግሎት በተመረጠበት ጊዜ በሲና ተራራ አርባ ቀንና ሌሊት ጾሟል "ሙሴም ወደ ደመናው ውስጥ ገባ ወደ ተራራውም ወጣ ሙሴም በተራራው ላይ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ቆየ" [ዘጸ. 24.19] ዝም ብሎ ሥራ ፈትቶ አይደለም የቆየው፤ ሥራውም ጾም ነው፡፡ "እግዚአብሔርም ሙሴን በእነዚህ ቃሎች መጠን ከአንተና ከእስራኤል ጋር ቃል ኪዳን አድርጌያለሁና እነዚህን ቃሎች ጻፍ አለው በዚያም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከእግዚአብሔር ጋር ነበር አልበላም አልጠጣም" [ዘጸ. 34፡27] እየጾመ ነበር ማለት ነው፡፡ በዚህ ጾሙ ሙሴ የቃል ኪዳኑን ጽላቶች ተቀብሎአል፡፡ ከዚህ የምንረዳው ከንቱ ሳይሆን ዋጋ ያለው እንደኾነ ነው፡፡ የኤልያስ ጉዞ አርባ ቀን አርባ ሌሊት እንደ ነበረ ተጽፏል፡፡ "የእግዚአብሔር መልአክ ደግሞ ኹለተኛ ጊዜ መጥቶ ዳሰሰውና የምትሄደበት መንገድ ሩቅ ነውና ተነሥተህ ብላ አለው፤ ተነሥቶም በላ ጠጣ፤ በዚያም ምግብ ኃይል እስከ እግዚአብሔር ተራራ ኮሬብ ድረስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ሄደ" [ዘጸ.19፡4-8]፡፡

✓ ሕዝቅኤል አርባ ቀን ጾሞ 600 ሙታን አስነሥቷል፡፡ ዕዝራ ሱቱኤል አርባ ቀን ጾሞ የጠፋ መጻሕፍትን መልሷል፤ አብረው የነበሩ ዐምስት ሰዎች ቀን ቀን ይጽፋሉ ማታ ማታ ጥቂት እህል ውኃ ይቀምሱ ነበር፡፡ [ዕዝ.ሱቱ. 13፡23-25] ጌታችን በተወለደ በአርባ ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቷል፡፡ [ሉቃ. 2፡22]: ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርባ መአልትና ሌሊት ጾመ [ማቴ. 4፡2]፡፡ በተነሣ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ [ሐዋ. 11.10]፡፡ ሰው በተፀነሰ በአርባ ቀኑ ተስዕሎተ መልክዕ ይፈጸምለታል፡፡ "በአርባ ቀን ትሾመዋለህ" እንዲል ቅዱስ አትናቴዎስ ወንድ በተወለደ በአርባ ቀኑ ሴት በተወለደች በ80 ቀኗ ኹለት አርባ ክርስትና ይነሣል፡፡ ሰው በአፈር በአርባ ቀኑ ጸሎተ ፍትሐት ይደረስለታል፡፡ ሰው በአርባ ቀኑ ጸሎተ ተክሊል ይደረስለታል፡፡ [ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 24 ገጽ 322]

አርባ ቀን ይህን ያህል ምስጢር ያለው ቀኑ ነው ጌታችን ለምን? አርባ ቀን ጾመ ስንል ከላይ ያየናቸውን አበው ነቢያት ብዙውን ጊዜ የጾሙት አርባ ቀን ነው፡፡ ቢቀንስ አጎደለ ከፍ ቢያደርግ አበዛ ብለው አይሁድ የነቢያትን ሕግ አፈረሰ በማለት ትምህርቱን አንቀበልም ባሉ ነበርና ይህንን ምክንያት በማንሣት አርባ መአልትና ሌሊትን ጾመ፡፡ እስራኤል 40 ዓመት ተጉዘው ምድረ ርስት ገብተዋል፡፡ እናንተም 40 ቀን ብትጾሙ ገነት መንግሥተ ሰማያት ትገባላቹ ሲለን ነው፡፡ ከላይ እንደ ተመለከትነው የጥፋት ውኃ አርባ ቀንና ሌሊት ዘነበ፤ ምድር ጸዳች ሰው አርባ ቀንና ሌሊት ቢጾም ርስት መንግሥተ ሰማያት ይወርሳል ሲለን ነው፡፡ ጾም ሲርስት ለመንግሥተ ሰማያት የሚያበቃ ከኃጢአት የሚያነጻ እንደሆነ ሊያስተምረን በኦሪት በተጾመው ቊጥር ጾም ሥርዓትን ሰጥቶናል፡፡

መላካም ጾም ይሁንላችሁ።

21 Feb, 19:50
144
Post image

‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️
#Valantines_day_እውነት_የፍቅር_ቀን ?
‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️
          

ከልደተ ክርስቶስ በኋላ በአለም ላይ የሠለጠኑት ሮማውያንና ግሪካውያን አምልኮተ እግዚአብሔርን ጠልተወ ሐዋርያትንና ተከታዮቻቸውን እያሳደዱና እየገደሉ በምትኩ ፍጡራን የሆኑ ምድራውያን ነገስታትንና የተለያዩ ጣኦታትን ለአምልኮ ይጠቀሙ
ነበር። ከፍ ሲልም ለእነዚህ ጣኦታቶቻቸው ክብር ሲሉ የተመረጡ እለታትንና ወራትን በስማቸው ይስይሙላቸው ነበር።እንደምሳሌ ዛሬ sunday, የፀሀይ ቀን/ monday, የጨረቃ ቀን.......እያልን እለታቱን የምንጠራበት ምክንያት ይሄው ነወ። በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ የተነሱ
ጣኦት አምላኪያን ደግሞ (february ·15) ቀንን የተኩላ አዳኙ«ሉፐርካልያ (Lupercalia)» ቀን ብለው ሰይመውት ነበር።

💚 @fenote_abew 💚
💛 @fenote_abew 💛
❤️  @fenote_abew ❤️


በአደኑ የሚፈሰውን ደምም በቀይ ቀለም መስለው ለነገራቸው ሁሉ ምልክት በማድረግ እለቷን በየአመቱ በቀይ ነገር እየሰሸበረቁ ያከብሯት ነበር። በ 323 ዓ·ም አካባቢ በቁስጥንጥንያ የነገሠው ክርስቲያኑ ንጉሥ ታላቁ "ቆስጠንጢኖስ"ይህ አይነቱ የባዕድ አምልኮ ሥርዓት እንዲቀር አዘዘ። በዚህ ጊዜ እነርሱ በተለየ መልኩ (february ·15) የሚያከብሯትን የተኩላ አዳኙ« ሉፐርካልያ (Lupercalia)» ቀን በአንድ እለት ወደ ኋላ ስበው (february ·14)ን የፍቅር ቀን በማለት በሽፋን በ valantines ስም ሰይመው ባዕድ አምልኳቸውን
ቀጠሉ።   ነገረ valantine ንን ከየት አመጡት ከተባለ በ2ኛው
መ·ከ·ዘ ማብቂያ ላይ "ክላውዴዎስ 2ኛ" በሮም በነገሰበት ወቅት የሰራዊቱን ቁጥር ለማብዛት ሲል ትዳር የሚመሰርቱ ወጣቶች እንዳይኖሩ ከለከለ ምክንያቱ ደግሞ ቤተሰብ ያፈራ ሰው ቤተሰቡን ትቶ ወደ ውትድርናው አለም እንዲገባ ስለማይገደድ ወጣቶቹ ይህን ሳይፈፅሙ በእነሱ ለመጠቀም በማሰቡ ነበር። ታዲያ ይህንን አዋጅ ብዙ ሰው ስላልደገፈው ልጆቹን በድብቅ ያጋባ ነበር። አቶ valantine ም ይህን ሀሳብ ከሚቃወሙት መካከል ስለሆነ ብዙ ወጣቶቹን በድብቅ እየሞሸሩ ያጋቡ ጀመር።ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ይህ ድርጊታቸው በንጉሱ ክላውዴዎስ ዘንድ በመታወቁ አቶ valantine መጀመሪያ የእስር ቀጥሎ የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው። ይህኔ በሮም ግዛት ሁሉ ስማቸው ገነነ ሥራቸውም በሁሉ ዘንድ ተሰማ  ለወጣቶች ፍቅር ሲሉም እራሳቸውን ለአደጋ እንዳጋለጡ በማሰብ የፍቅር አባት እስከመባል ደረሱ።ይህ ከሆነ ከብዙ ዓመታት በኋላ የተነሳው ቆስጠንጢኖስ ደግሞ የተኩላ አዳኙን ቀን እንዳይከበር ሲከለክል ሕዝቡ እለቷን ሳያስቡ እንዳያልፉ የቆየውንና በህዝቡም ዘንድ በፊት ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝቶ የነበረውን የvalantine ን ታሪክ ስቦ በማምጣት ለባዕድ አምልኳቸው ሰበብ እንዲሆናቸው የፍቅር ቀን ብለው ተጠቀሙበት።እንግዲህ valantines day ከዚህ ጊዜ አንስቶ በፍቅር ቀን ስም መከበር የተጀመረ ሲሆን ከዘመናት በኋላ ደግሞ የካቶሊክ ቤ/ክ ለሰውየው ቅድስና ስለሰጠቻቸው እለቱ በአለም ዙሪያ የቅዱስ ቫላንታይን ቀን ተብሎ እንዲታሰብ ምክንያት ሆነች። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ሰው በዘር ፣ በቀለምና በሃይማኖት ሳይለያይ መያዝ የማይገባውን ስያሜ ሰጥቶ ሲያከብረው  እያየን እንገኛለን።በሀገራችንም እየሆነ ያለው ይሄው ነው።እኛን በቅጡ ለማይወክለን ባህል ሆቴሎችና መዝናኛ ቦታወቻችን በዚህ ቀን ጥንድ ካልሆናችሁና ቀይ ካለበሳችሁ አናስተናግድም እያሉ ነው።ሰውን የፍቅር "ቀን"ብለው ጠርተውት "ሌሊቱን"  እያሳበዱ ያሳድሩታል።የመገናኛ ብዙኃኖቻችን ፍቅር በሀገራችን አልፎ እንደማያውቅ ፣ስለ ፍቅር የተከፈለ መስዋዕትነት በታሪካችን እንደሌለ፣ አብሮነት መዋደድ በማህበረሰባችን እንደማይታወቅና ሃይማኖታችንም ስለፍቅር እንዳልሰበከች ያህል አድርገው የፍቅር ማስተማሪያ ምሳሌዎቻቸውን ሁሉ የሚያመጡልን የኛ ካልሆኑ የምዕራባውያን ታሪኮች ነው። ነጮች ለዚህ ሁሉ ነገር መነሻ የሆነውን ቫላንታይንን ከሰብዓዊነት
የተነሳ ለወጣት ፍቅረኛሞች ህልማቸውን አሳክቶ
ጥሩ ነገር ስላደረገላቸው የፍቅር አባት ብለውት ይሆናል።ነገር ግን ስለ እውነት እንነጋገር ከተባለ ለእኛ ትክክለኛ የፍቅር አባት እርሱ ሊሆን አይችልም ምክንያቱም እኛ ከሰማያዊ መንበሩ በፍቅር ተስቦ የወረደ እዛው ባለበት ሆኖ የወደደውን ማድረግ ሲቻለው ፍፁም ፍቅሩን እንድንረዳ ለአይሁዳውያን ተላልፎ በመሰጠት በሞቱ ሕይወትን ያደለን ክርስቶስ ስላለን valantine ለእኛ የፍቅር አባት መታሰቢያ ቀኑም የፍቅር ቀን ሊሆን አይችልም።እንደው የአምላካችንን ነገር ማንሳት ከከበደንና valantine ን ከእርሱ ጋር አናወዳድረው ካልንም ወደ ሀገራችን ታሪክ ተመልሰን ከቫላላንታይን በላይ ለፍቅር ብዙ የሆኑት ሰዎች አስበን አላከበርናቸውም።በእኛው ታሪክ በ15ኛው መ·ከ·ዘ ግራኝ አህመድ ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ካህናት አባቶቻችን መጠጊያ መጠለያቸው የሆነች ቤተ ክርስቲያን በእሳት ስትፈተን ሥርዓተ ጋብቻን በየምዕመኑ ቤት በድብቅ ነበር የሚፈጽሙት ግን እኛ የፍቅር አባት አላልናቸውም። እነ አፄ በካፋ የወደዷትን ለማግባት በንግስናቸው እንደፈለጉ አዘው ማግኘት የሚችሉበት አጋጣሚ እያለ እንደ ተራ ሰው መናኛ ልብስ ለብሰው የሰው ቤት ደጅ መጥናታቸውን አይተን የፍቅር ምሳሌ አላደረግናቸውም። ከማህበረሰቡ የቆየ የመረዳዳትና የመተዛዘን ባህል ለፍቅር ኑሮ ማስተማሪያ ታሪክ አልመዘዝንም። እናም እኛ ኢትዮጵያውያን ይህ ሁሉ እያለን ምንም አለማድረጋችን የባዶነታችንን ክፍተት የአላዋቂነታችንን ጥግ ያሳያልና ቆም ብለን እናስብ የእምነት መግለጫ ማህተባችንን ማሰር ከብዶን ለጣኦት የተገበረን ደም ማሳያ የሆነን ቀይ ልብስ ለብሰን እንዞራለን ፣የቤተ ክርስቲያናችንን ቅዱሳኖች አመታዊ በዓል በዳቦ
ዘክሮ ለማሰብ እጅ የሚያጥረን የካቶሊክን ቅዱስ
ለማክበር ድንጋይ እንፈነቅላለን።በዚህ ወር የተፈፀሙትን  የነ አብርሃም ደቦጭ ገድል የታላቁን የአድዋን ድል ታሪክ ለማስታወስ ደንታ የሌለን የ valanine ንን ቀን እንዳንረሳ ማስታሻ እንይዛለን።ማን ያውቃል በዚሁ ከቀጠልን ደግሞ ወደፊት ዋና ዋና በዓላቶቻችንን ትተን የነሱን X-MASS ብቻ እናክብር እንላለን።ነገር ግን ይህ ሁሉ ከመሆኑ በፊት  እንዲህ እንደ valanine አይነት ያሉ የምዕራባውያን ባህሎችን በመቃወም ለነገ ዛሬን የማስተካከያ እድል አለን። ይህን ካላደረግን ግን እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ደም  የለንም ማለት ነው። ምክንያቱም እነ አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕትነት የተቀበሉት ኢትዮጵያ በዚህ አይነቱ የእጅ አዙር ቅኝ ተገዥነት እንዳትያዝ ህዝቦቿም መልካም አላማ የያዙ መስለው ሃይማኖታዊ ሕፀፅንና ሥርዓት የለሽነትን በሚያራምዱ  በሽፋን ከሚንቀሳቀሱ የባህል ቅሰጣወችና ማንነት ከሚያጠፉ ነገሮች እንድንጠበቅ ነውና የቆምንበትን እናስተውል።በተለይ ደግሞ ሕዝቧ የሚያከብረው ሃይማኖት የራሱ የሆነ ማንነት አለው በሚባልላት ኢትዮጵያ እንዲህ ሲሆን ማየት ያሳምማልና ከሌላ ወገን የምናመጣቸውን በአላት ከሃይማኖታችን እንደማይጋጭ ከባህል ማንነታችን ጋር እንደማይጣረስ የመጨረሻ አላማና ግባቸው ምን እንደሆነ እንመርምር።

💚 @fenote_abew 💚
💛 @fenote_abew 💛
❤️  @fenote_abew ❤️

14 Feb, 14:02
394
Post image

꧁༒꧂ ጾመ ነነዌ ꧁༒꧂

ነነዌ የአሦር ጥንታዊ ከተማ ነበረ። ፍርስራሹ በጤግሮስ ወንዝ ምሥራቅ ዳርቻ በሞሱል ዙሪያ አሁን አለ። ጾመ ነነዌ ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዷ ስትሆን የምትጾመውም ለሦስት ቀናት ነው፡፡ የምትጀመረው ልክ እንደ ዐቢይ ጾም ሰኞን አትለቅም ቀኑ ሲወርድ ወይም ወደ ኋላ ሲመጣ እስከ ጥር 17 ድረስ ነው ቀኑ ሲወጣ ወይም ወደ ፊት ሲገፋ እስከ የካቲት 24 ቀን ይረዝማል፡፡

በእነዚህ 35 ቀናት ውስጥ ስትመላለስ ከፍ ዝቅ ስትል ትኖራለች ከተጠቀሱት ዕለታት አባቶች እንደ ደነገጉት አትወርድም አትወጣም በዚህ ዓመትም የካቲት 03 ቀን ትጀመራለች፡፡ አጭርና የሦስት ቀን ጾም ብትሆንም እንኳ እጅግ ብዙ ጥቅምን የምታስገኝ ጾም ናት፡፡ ይህም "በመባጃ ሐመር ከፍና ዝቅ ስለሚል ቊጥሩ ከአጽዋማት ሐዋርያት ነው፡፡ አንድ ጊዜ በጥር አንድ ጊዜ በየካቲት ይሆናል፡፡" ታዲያ ነነዌ ማን ናት? ነነዌ በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ ናምሩድ በተባለው ሰው ተመሠረተች፡፡ ለአሰራውያን መናገሻ ከተማ ነበረች፡፡ ሰፊና ውብ ከተማ ሆና የተገነባች ናት፡፡ [ዘፍ. 10:1] አስር ከእስራኤላውያን ጋር ጠላት ሆነው በተቀናቃኝነት የኖሩ መንግሥታት ናቸው፡፡ ዮናስ የተላከው ተቀናቃኝ ወደ ሆኑት ሕዝቦች ነው፡፡ ከተማዋ ውብና ብዙ ሕንፃዎች ነበሩባት የከተማዋ ቅጽር ርዝመት 12 ኪ.ሜ እንደነበር በውስጧ ብዙ ሕንፃዎች ተሠርተውባት ነበር፡፡ የባቢሎን መንግሥት ከክርስቶስ ልደት በፊት ከተማዋን አፈረሳት፡፡ [ዮና.4.1]
 
ሕንፃዎቿን የሠራቸው ሰናክሮም ሲሆን በስተመጨረሻ በ621 ዓ.ዓ የባቢሎን መንግሥት አፍርሷታል፡፡ ነነዌ ዛሬ የኢራቅ ከተማ ምሱል ናት በኩሽ ልጅ ናምሩድ በ1800 ዓ.ዓ ተቆረቆረች፡፡ ሽታር ወይም አስታሮትን ያመልኩ ነበር በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ገጥሟታል፡፡

ታዲያ ለነነዌ ሰዎች የተላከው ዮናስ ከአባቱ አማቴ እና ከእናቱ ሰና እንደተወለደ ታሪኩ ይነግረናል፡፡ ዮናስ ኤልሳዕ ያዳነላት የሰራጵታዎ ሴት ልጅ ነው የሚሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሑራን ይነግሩናል፡፡ ነገር ግን ስለ ነቢዩ ዮናስ ጥልቀት ያለው ታሪክና መረጃ በስፋት አልተገለጸም፡፡ የስሙ ትርጉምም ቢሆን በእብራይስጥ ቋንቋ ርግብ የሚለው ትርጉም እንደሚገልጸው መተርጉማኑ ይገልጻሉ፡፡

ከእግዚአብሔር ዘንድ ለዮናስ የመጣው መልእክት "ክፋቷ በእኔ ፊት ወጥቷልና ወደ ታላቂቷ ከተማ ወደ ነነዌ ሄደህ፣ በእርሷ ላይ ስበክ፡፡" [ዮና. 1.1] የሚል ነበር፡፡ ዮናስ ግን ጥሪውን መቀበል ባለመፈለጉ ኮበለለ፡፡ ከእግዚአብሔር መኮብለል አያዋጣምና ነብዩ ዮናስ በትልቅ አሣ እንዲዋጥ ተደረገ፡፡ በዚህ ውስጥ ዮናስ የትንቢት ቃሉን ለነነዌ ሕዝብ ማድረስ እንዳለበት ተረዳ፤ እግዚአብሔር ለኹለተኛ ጊዜ የነገረውን ድምጽም ሰምቶ ወደ ነነዌ ሄደ፡፡

በወቅቱ ነነዌ እጅግ ታላቅ የሆነች ከተማ ነበረች፡፡ በአርኪዮሎጂ ግኝት እንደተረጋገጠውም ከተማዋ ነቢዪ ዮናስ እንዳለው የሦስት ቀን መንገድ ያህል እጅግ ታላቅ ከተማ (ዮና.3.3) ነበረች፡፡ በአሁኑ ወቅት እንዳሉ ከተማዎች ሁሉ ሕዝብ የበዛበት ነበረች፡፡ ከመቶ ሃያ ሺህ በላይ ሕዝብ ይኖርበት እንደነበረም በዚያው በነቢዩ ዮናስ መጽሐፍ ላይ ተጠቀወሶ እናነባለን፡፡ [ዮና.4.1] ሆኖም ግን በዚህ ሁሉ ውስጥ እግዚአብሔርን እጅግ የሚያሳዝን ኀጢያት ይሠራ ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ነብዩ ዮናስ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ ነነዌ ሕዝቦች ይዞ ሄደ፡፡ ነነዌ እንደምትገለበጥም ተነገራቸው፡፡ 

በዚህ ታሪክ ውስጥ ትልቁን ትምህርት የምናገኘው እዚህ ጋር ነው፡፡ እግዚአብሔር የንስሐ ጥሪን ለኁሉም ያደርጋል፡፡ ከየሰው በኩል የሚሰጠው ምላሽ ግን የተለያየ ሊሆን ይችላል፡፡ የነነዌ ንጉስ ከተማይቱ እንደምትጠፋ በሰማ ጊዜ "ከዙፋኑ ወረደ፤ ልብሱንም አወለቀ፤ ማቅም ለብሶ በዐመድ ላይ ተቀመጠ፡፡" [ዮና.3.6] ከዚህም በኋላ በነነዌ ሕዝብ ዘንድ ጾም እንዲታወጅ እንዲህ ሲል ተናገረ፡- "ማንም ሰው ወይም እንስሳ፣ ከብትም መንጋም ሆነ የበግ መንጋ፤ ምንም ነገር አይቅመስ፤ አይብላ፤ ውሃም አይጠጣ፡፡ ነገር ግን ሰውም እንስሳም ማቅ ይልበስ፤ ኁሉም አጥብቆ ወደ እግዚአብሔር ይጩህ ሰዎችም ኁሉ ክፉ መንገዳቸውንና የግፍ ሥራቸውን ይተው፡፡ እና እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ራርቶ ከጽኑ ቁጣው ይመለስም እንደሆነ ማን ያውቃል" [ዮና. 3:7-9] በዚህም ጥሪ ምክንያት ሕዝቡ በጾም ሆኖ ወደ እግዚአብሔር ተመለሰ፡፡ 

እግዚአብሔርም ለዚህ የሰጠው ምላሽ እንዲህ ነው፡- "እግዚአብሔርም ምን እንዳደረጉና ከክፉ መንገዳቸውም እንዴት እንደ ተመለሱ ባየ ጊዜ ራራላቸው፤ በእነርሱም ላይ ሊያመጣ ያሰበውን ጥፋት አላደረገም፡፡" [ዮና. 3:10]

ነነዌና አንዳንድ ነገሮች
. በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የዚህ ጾም ስም "የዮናስ ጾም" ይባላል፡፡ ሆኖም ግን ቀደምት መዛግብት ላይ የሠፈሩ መረጃዎች (የነነዌ ጾም) በሚለው ይሄዳሉ፡፡ እዚህ ጋር የምንዘክረው የነነዌ ሰዎች የጾሙትን ጾም ብቻ ሳይሆን ነብዩ ለሦስት ቀን በአሣው ሆድ ውስጥ መቆየቱን እናሳስባለን፡፡

. የዚህን ጾም ታሪክ ወደ ኋላ ይዘን ስንሄድ የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን እናገኛለን፡፡ ይህ ጾም በሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ከአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲጾም የነበረ ነው፡፡ በዚህም ጾም ምክንያት ብዙዎች ከአደጋ ለመዳን ችለዋል፡፡   
 
. ለመሆኑ ነብዩ ዮናስን የዋጠው የባሕር እንስሳ ምንድር ነው; ግእዙ (ዐንበሪ) ይለዋል፡፡ ብዙዎች (ዐሣ ዐንበሪ) በማለት ዛሬ ላይ በተለምዶ የምናውቀው ትልቅ ዐሣ ዮናስን እንደዋጠው ይናገራሉ፡፡ ግሪኩ (ኬቶስ) ይለዋል፤ ትርጉሙም ታላቅ የባሕር እንስሳ ማለት ነው፡፡ ሊቁ ኒቆዲሞስ ገዳማዊ st. Nicodemus the hagiorite ስለዚህ (ኬቶስ) የተባለ የባህር እንስሳ ሲናገር እንዲህ ይላል፡-
ዕውቀትን እና መማርን ለሚወዱ ሰዎች ስለ ኬቶስ እንዲህ ብለን እንናገራለን፡፡ ቴዎክለስ እንዳለው ከሆነ ኬቶስ ከአስር መርከብ የበለጠ ነው፡፡ አሊያንስ እንደተናገረው ደግሞ ከዝሆን ዐምስት ጊዜ ይበልጣል፡፡ ኤራቶስቴንስ ሲናገር ደግሞ ሀምሳ ኪውቢት (23 ሜትር) በላይ ርዝማኔ አለው ይለናል፡፡ --- እነዚህን ጥንታዊ ሰዎች በመከተል ታላላቅ አባቶች ስለ ኬቶስ ግዙፍነት ይናገራሉ፡፡ ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ ኤቶስ ሰውነቱ እንደ ትልቅ ተራራ ያለ እንደሆነ እና ደሴት እንደሚመስል ይነግረናል፡፡ (አክሲማሮስ ዘባስልዮስ ድርሳን ሰባት) ታላቁ አምብሮስ ደግሞ ሲናገር ኬቶስ ሲዋኝ ቀና ቢል ሰማይን እንደሚነካ ሁሉ ግዙፍ እንደሆነ እና ትልቅነቱ እንደ ደሴት ወይም እንደ ተራራ እንደሚመስል ይናገራል፡፡ ኤውስጣቴዎስ ዘአንጾኪያ ደግሞ በአክሲማሮስ ሲነግረን አስፒዶኬሎን የታለው ኬቶስ እጅግ ግዙፍ ከመሆኑ የተነሣ ሰዎች ሲያዩት ደሴት እንደሚመስል ተናግሯል፡፡

ሐዋርያትም ሰብአ ነነዌ የተነሣህያን አብነት ናቸውና ሥርዓቱም ጾሙም አይቀር ብለው ሠርተውታል፡፡ እኛም በጾምና በጸሎት ከፈጣሪያችን ምህረትና በረከት ለማግኘት ስንል እንጾመዋለን፡፡ በተጨማሪም ይህ ጾም ለዐብይ ጾም መዘጋጃ በመሆን ያገለግላል፡፡

የፊታችን ሰኞ የሦስት ቀናቱ ጾም ጾመ ነነዌ ይገባል።
ጾሙ ከመግባቱ አስቀድሞ ኦርቶዶክሳውያን ሁላችን ንስሓ እንግባ።
ከዚህ ንስሓ ጋር የታወጀውን የየነነዌ ጾም ጠዋት በኪዳንና ከሰዓት በቅዳሴ ማታ ደግሞ በጸሎተ ምሕላ በየአጥቢያችን እየተገኘን አምላካችንን እንማጸነው።

ይቆየን...

09 Feb, 08:27
550
Post image

#ጾመ_ነነዌ የካቲት 3 ይጀመራል!

" የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፥ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ። "
ዮናስ 3÷5

07 Feb, 18:46
456