Federal Prison Commission-Ethiopia @federalprisonsadministration Channel on Telegram

Federal Prison Commission-Ethiopia

@federalprisonsadministration


የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር

Federal Prison Commission-Ethiopia (Amharic)

የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የኢትዮጵያ ፌደራል ማረሚያ ቤተሰብ ደግሞ እናረጋለን! ለምቹት ተጨማሪ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶችን የተለያዩ መረጃዎችን በአጠቃላይ ለመስጠት እና ስም ይሁኑ። የባለኞች ቀን እና ቀናት ልምድ አደገኛችንን በችግር ለእናረጋለን። የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ ክስ, ጥቁር የሚረፍ የቫይረሱ እና በህፃናት ላይ ከሆናችሁ ከእኛ የሚታየን አድማጮችን እና መረጃዎችን ለመስጠት እና አንባቢዎችን ለመበዳት አመልኩለዋል። አንባቢዎች፣ እና ተማሪዎች ከተከለከሉ በእኛ ላይ፣ እናም ከእኛ ጋር ካለ ወቅታዊ መረጃዎች ፈውሶ ስክትዀተር። ፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር አካሄደን።

Federal Prison Commission-Ethiopia

14 Feb, 07:48


07/6/2017 ዓ/ም
ምክር ቤቱ የተሻሻለውን የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ

የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ በሦስተኛ ቀን ውሎው የቀረቡለትን ረቂቅ አዋጆች መርምሮ አጽድቋል።

ምክር ቤቱ ካጸደቃቸው ረቂቅ አዋጆች መካከል የተሻሻለውን የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ረቂቅ አዋጅ አንደኛው ነው።

የተሻሻለው የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ረቂቅ አዋጅን ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ አዋጁን በተመከተ በዝርዝር ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

የክልሉን ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ጋር የተናበበ እንዲሆን እና አሠራራቸውን ማዘመን እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

የተሻሻለው ረቂቅ አዋጅ ማረሚያ ቤቶችን የማረምና የማነፅ ስራውን ምቹ ለማድረግ እንደሚያስችል ኮሚሽነሩ የገለፁ ሲሆን በተመሳሳይ ረቂቅ አዋጁ የሕግ ታራሚዎችን መብት ለማስጠበቅ እና አያያዛቸውን በተመለከተ የተመቸና አለማቀፍ የታራሚዎች አያያዝ ድንጋጌዎችን መሰረት ያደረገ እንዲሆን እንደሚያስችል ነው ያነሱት ።

ኮሚሽነሩ አክለውም ኮሚሽኑ የተቋቋመለትን ዓላማ በአግባቡ እንዲፈጽም ለማስቻል አዋጁ አስፈላጊ ነው ብለዋል። የተሻሻለውን የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ረቂቅ አዋጅ ለማዘጋጀት ባለድርሻ አካላት እንደተሳተፉበት ገልጸዋል።

አዋጁ ታራሚዎች የተሻሻለ አያያዝ እንዲኖራቸው፣ መብታቸው እንዲጠበቅ እና ራሳቸውን በትምህርት እንዲያበቁ ያደርጋል ነው ያሉት ኮሚሽነሩ።

መረጃው የአማራ ክልል የህዝብ ግንኙነት ክፍል እና የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው ።

Federal Prison Commission-Ethiopia

07 Feb, 11:21


ለሀረሪ ክልል  ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች፣ አባላትና ሰራተኞች በፖሊሳዊ የስነምግባር ዙሪያ የአቅም ግንባታ  ስልጠና መሰጠት ጀመረ።
በሀረሪ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን  ከፍተኛ መኮንኖች፣ አባላትና ሰራተኞች  በፖሊሳዊ ስነምግባር፣ በተቋሙ የውስጠ ደንብና መመሪያ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ  የሀረሪ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኻሊድ ኑሬ ባስተላለፉት መልዕክት የተዘጋጀው የአቅም ግንባታ ስልጠና የኮሚሽኑ አመራሮች፣ አባላትና ሰራተኞች  በፖሊሳዊ ስነምግባር፣ በኮሚሽኑ ደንቦችንና መመሪያዎች ዙሪያ የተሻለ እውቀትና ግንዛቤ ኖሯቸው የህግ ታራሚዎችንና የኮሚሽኑን አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ ደንበኞች በእውቀት ላይ የተመሰረተ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል ነው ብለዋል።
የሀረሪ ክልል ማረሚያ ቤት ም/ኮሚሽነር ሙራድ አብዱላሂ በበኩላቸው ከአቅም ግንባታ ስልጠናው በኃላ የስራ አፈፃፀም ግምገማ ከከፍተኛ አመራሮች ጀምሮ እስከ ፈፃሚዎች ድረስ የስራ አፈፃፀም ግምገማ ይደረጋል ብለዋል።
ስልጠናው ለ4 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን የአቅም ግንባታ ስልጠናውን የኮሚሽኑ ባለሙያዎች እና ተጋባዥ አሰልጣኞች እንደሚሰጡ የሀረሪ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ያደረሰን መረጃ ያመላክታል።

Federal Prison Commission-Ethiopia

30 Jan, 03:51


በኢፌድሪ የሲቪክ ማህረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ለሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ፡፡
አዲስ አበባ - ጥር 21/2017 ዓ.ም (የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ለሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል የትምህርት ቁሳቁስ፣ የሴቶች የንጽና መጠበቂያ እና ለህጻናት አልሚ ምግብ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡
ድጋፉን በሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል ተገኝተው የተረከቡት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የማረም ማነጽና ተሃድሶ ልማት ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ጄኔራል ሉባባ ጀማል የተደረገውን ድጋፍ አስመልክተው እንደተናገሩት የቁሳሰቁስ ድጋፉ በእርምት ሂደት ላይ የሚገኙ የህግ ታራሚዎችን የመማር ማስተማር ሂደት የሚደግፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ም/ኮሚሽነር ጄኔራሏ አክለውም ለማረሚያ ማዕከሉ የተደረገው የአልሚ ምግብ ድጋፍ ያለ ወንጀላቸው ከወላጆቻቸው ጋር በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ ህጻናትን ጤንነት ለመጠበቅና የምግብ ፍላጎታቸውን ለማሟት በሚያደርገው ጥረት አስተዋጽኦው የጎላ ነው ብለዋል፡፡
የአይነት ድጋፉን ለማስረከብ በማዕከሉ የተገኙት በኢፌድሪ የሲቪክ ማህረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ፀሐይ በበኩላቸው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሀገራችን ውስጥ የሚገኙ በጎ አድራጊ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበርና ድጋፍ በማሰባሰብ በማህራዊ ችግር ላይ ለወደቁ የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
ስራ አስፈጻሚዋ አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል ያደረገው የአይነት ድጋፍ ለማስጀመርያ ያህል መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይ የሲቪክ ማህረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ከሌሎች በጎ አድራጊ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ጋር በመተባበር ለማረሚያ ቤቶች የሚያደርገውን ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

የሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል ዳይሬክተር ኮማንደር አይናለም ሳህሉ በበኩላቸው የሲቪክ ማህረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ያደረገው የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ በእርምት ሂደት ላይ ለሚገኙ ሴት የህግ ታራሚዎች በቆይታቸው የግልንጽናቸውን እንዲጠብቁ የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፤ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

28 Jan, 18:15


ያለፉት ስድስት ወራት የኮሚሽኑ ተልዕኮ አፈጻጸም ፣ አንኳር አንኳር ስራዎች መሰረት የያዙበት እና ብዙ ተስፋ ሰጪ መሻሻሎች የታዩበት ነው፤ኮሚሽር ጄኔራል የኑስ ሙሉ፡፡
አዲስ አበባ - ጥር 20/2017 ዓ.ም (የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
ለተከለታታይ ሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየውን የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የመሩት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ እንደተናገሩት በበጀት አመቱ የመጀመርያ ስድስት ወራት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ የሆኑ ውጤታማ እና ለቀጣይ ተስፋ ሰጪ የሆኑ ተግባራት የተከናወኑበት ነው ብለዋል፡፡
ኮሚሽኑ ባለፉት ስድስት ወራት የ2016 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ግምገማ መድረክን መሰረት በማድረግ የአመራር ማስተካከያ ማድረጉን ፣ክፍተቶችን በመለየት ሰፋፊ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ከላይ እስከ ታ ላው ፈጻሚ መስጠቱን እንዲሁም ከበላድርሻ አካላት ጋርም ህጋዊ የጋራ ስምምነት በመፈራም ሰፋፊ ስራዎች ተሰርተዋል፤አሁንም በመሰራት ላይ ናቸው ብለዋል፡፡
ኮሚሽነሩ አክለውም ምንም እንኳ ለቀጣይ ስራ መሰረት የሆኑ እና ተስፋ ሰጪ ሰፋፊ ስራዎች ቢሰሩም አመራሩ የተቋሙን ጥበቃና ደህንነት ለማረጋገጥ በቴክኖሎጅ በመታገዝ በተደራጀ የእዝ ሰንሰለት እና በዲሲፕሊን በመምራት ረገድ በቀጣይ ስድስት ወራት ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት ይገባል፤ ብለዋል፡፡
የኮሚሽኑን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የተከለከሉ ነገሮች ወደ ማረሚያ ቤት እንዳይገቡ ጠንካራ ፍተሻና ቁጥጥር ማድረግ ያስፈልጋል፤ ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራሉ የማረሚያ ፖሊስ አባላቱን በዲሲፕሊን እና በስነ ምግባር በመምራት ውጤታማ ስራ ለማከናወን ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንደሚገባ፤በኮሚሽን ደረጃ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
ኮሚሽኑ ባለፉት ስድስት ወራት በእቅድ ይዞ ያከናወናቸውን ስራዎች የአፈጻጸም ሂደት ከመገምገም በተጨማሪ በተቋሙ የስድስት አመት ትራንስፎርሜሽ እቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡
ሰነዱን ያቀረቡት የኮሚሽኑ የሰው ሃብትና ፋይናንስ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ደስታ አስመላሽ እንደተናገሩት 9 መሰረታ ምሰሶዎችን (Pillars) የያዘው የተቋሙ የስድስት አመት የትራንስፎርሜሽን እቅድ ከሀገራችን የለውጥ ሂደትና ፍትህ ስርዓት ጋር የተሰናሰለና እቅዱ እያንዳንዱን የስራ ክፍል በአግባቡ ለመምራት እንዲችል ሆኖ የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡
ካነጋገርናቸው የውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል ዳይሬክተር ረ/ኮሚሽነር ሙላት ጫንያለው እንዳሉት ኮሚሽኑ የ2016 ዓ.ም የስራ አፈጻጸምን መሰረት በማድረግ ተቋማዊ ለውጥ ለማምጣት የአቅም ግንባታ ስልጠናና የአመራር ድልድል መከናወኑን አስታውሰው የቀረቡት የሁሉም ማዕከል ማረሚያ ቤቶች የእቅድ አፈፃፀም መሻሻሉን ገልጸዋል፡፡
የሴቶች ማረፊያና ማረሚያ ማዕከል ዳይሬክተር ኮማንደር አይናለም ሳህሉ በበኩላቸው የኮሚሽኑን የተልዕኮ አፈፃፀም ከፍ ለማድረግ በአባላት ስነ ምግባር ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ነው ያሉት።
ኮማንደር አይናለም ሳህሉ አክለውም የህግ ታራሚዎችን በማረምና በማነጽ አምራችና ህግ አክባሪ ዜጎች ሆነው እንዲወጡ ለማድረግ የጥበቃና ደህንነት እና የማረም ማነጽ ስራዎች በቅንጅት መሰራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡
በግምገማ መድረኩ ላይ የዋና መስሪያ ቤቱን ጨምሮ የሁሉም ማዕከል ማረሚያ ቤቶች ዳይሬክተሮችና የማስተባበሪያ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

28 Jan, 14:16


የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ መምህራን እና የአምስተኛ አመት የህግ ተማሪዎች በድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል ለህግ ታራሚዎች ስልጠና ሰጡ።
ጥር 20/2017 ዓ.ም (ድሬደዋ)
በድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል በ 2 የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የህግ መምህራን እና በ25 የህግ ተማሪዎች አማካይነት በማዕከሉ ለሚገኙ ለ64 የህግ ታራሚዎች በተለያዬ ቋንቋዎች ጥር 20/2017 ዓ.ም ስልጠና ሰጥተዋል ።
ስልጠናውን ያስተባባሩት የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የህግ መምህርት መሠረት አለማየሁ እና መምህር አራርሣ አልይ እንደተናገሩት የህግ ታራሚዎች ሊኖርባቸው የሚችለውን የህግ ዕውቀት ክፍተት ለመሙላት እና የህግ ግንዛቤያቸውን ለማሳደግ የህግ ተማሪዎችን እና መምህራንን በማስተባባር ስልጠና እንዲያገኙ በማድረግ እንደዜጋ ማህበራዊ ኃላፊነታችንን ለመወጣት አቅደን የሰራነው ስራ ነው፤ ሲሉ በስልጠናው ሂደት ተናግረዋል፡፡
የድሬደዋ ዩኒቨርስቲ የንቃተ ህግ መምህራን እና ተማሪዎች ማረሚያ ማዕከሉን ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸውን በመግለጽ ከማዕከሉ የማረም ማነፅ ቡድን ጋርም በቅርበት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡
መረጃው የማዕከሉ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

09 Jan, 04:26


#ዜና የድሬዳዋ አስተዳደር የህግ ነክ ጉዳዮች የአእምሮ ምርመራ ማእከል በዛሬው እለት ተመረቀ

#DGC ታህሳስ 26/2017

በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ማእከል ውስጥ የተገነባው የድሬዳዋ አስተዳደር የህግ ነክ ጉዳዮች የአእምሮ ምርመራ ማእከል ( ፎረንሲክስ ሳይክልትሪ ዩኒት ) በዛሬው እለት በይፋ ተመርቋል ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከለውጡ ማግስት ከተከናወኑ ወሳኝ ሁሉን አቀፍ መሰረታዊ ለውጦች መካከል ከዚህ ቀደም የነበረውን የወንጀል ፍትህ ስርአት ስብራት ለመጠገን ዘርፈ-ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር ተናግረው በአስተዳደሩና የፍትህ ተቋማት ያለሰለሰ ጥረት የነዋሪውን የረጅም ጊዜ አላስፈላጊ እንግልትና ከፍተኛ ወጪ ከመታደግ ባለፈ ለአጎራባች ክልሎች ጭምር በቅርቡ ከአስክሬን ምርመራ ጋር ተያያዥ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉንም ነው ክቡር አቶ ከድር ጁሀር የተናገሩት ።

የፍትህ ሪፎርም ትግበራ ከህግ ነክ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የአእምሮ ጤና ምዘና ውጤቶች እንደ ሀገር ካለው የምርመራ ማእከላትም ሆነ ባለሞያዎች ውስንነት አንፃር በፍትህ ስርአት ውስጥ የሚገጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ባለድርሻና አጋዥ ተቋማትን በማስተባበርና በቅንጅታዊ አሰራር የድሬዳዋ አስተዳደር የህግ ነክ ጉዳዮች የአእምሮ ምርመራ ማእከል ለማቋቋም መቻሉን የድሬዳዋ አስተዳደር የፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱሰላም አህመድ ተናግረዋል ።

የአእምሮ ምርመራ ማእከል በሀገራችን በአዲስ አበባ ብቻ የነበረ ሲሆን ይህም የፍትህ ስርአቱን ለማፋጠን አዳጋች ሆኖ መቆየቱን የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ ተናግረው የድሬዳዋ አስተዳደር የህግ ነክ ጉዳዮች የአእምሮ ምርመራ ማእከል በድሬዳዋ አስተዳደር እውን በመሆን በእጅጉ አስደሳች እንደሆነና ይኸውም ማእከል በተለይም ፍትህ እንዳይዘገይ ብሎም ዜጎች ማረሚያ ከገቡ በኃላ የአይምሮ ህመም ከማጋጠማቸው አስቀድሞ ለሚፈጠሩ ችግሮች በእጅጉ አጋዥ እንደሆነም ነው ኮሚሽነር አለሙ መግራ ያስታወቁት ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከማረሚያ ቤቱ ጋር በጋራ እየሰሩት ላለው ስራዎች እንዲሁም ለሚያደርጉት ድጋፍ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽነር የሆኑት ኮሚሽነር ጀነራል ዩኑስ ሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበው ማረሚያ ቤቶች ከዚህ ቀደም አስፈላጊ የሆነ ድጋፍ እና ክትትል እንደማይደረግላቸውና አሁን ላይ ግን መንግስት በሰጠው ትኩረት ዘርፈ-ብዙ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነም ነው ኮሚሽነር ጀነራል የኑስ ሙሉ የተናገሩት ።

የድሬዳዋ አስተዳደር የህግ ነክ ጉዳዮች የአእምሮ ምርመራ ማእከል በድሬዳዋ አስተዳደር ተገንብቶ ለምረቃት መብቃቱ በእጅጉ እንዳስደሰታቸውም ነው የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር አየለ ተሰማ ፣ በፍትህ ሚኒስቴር የሚኒስትር ዲኤታ ተወካይ አቶ መዝሙር ያሬድ እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሀላፊ የሆኑት ዶክተር ፅጌረዳ ክፍሌ በእለቱ የገለፁት ።

በአለማየሁ አበበ
ፎቶ :- በአገኘው ሸዋረጋ

Federal Prison Commission-Ethiopia

09 Jan, 04:26


የድሬዳዋ ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ እንደዘገበው

Federal Prison Commission-Ethiopia

27 Dec, 00:36


የፌዴራል ማረሚያ ቤት  ኮሚሽን ከደቡብ ኮሪያ ዓለም አቀፍ የወጣቶ ኅብረት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የውል ስምምነት ተፈራረመ።
አዲስ አበባ- ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም (ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
ኮሚሽኑ  በአቅም ግንባታ ሥራ ላይ ከደቡብ ኮሪያ የዓለም አቀፍ የወጣቶች ኅብረት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ታህሳስ 17 ቀን 2017ዓ.ም.  ተፈራርሟል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት  ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ በስምምነት ሰነዱ የፊርማ ሥነ-ስርዓት ላይ  የደቡብ ኮሪያ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ኅብረት አባላት ለኮሚሽኑ ከፍተኛ፤ መካከለኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በአዕምሮ ውቅር ላይ ጠቃሚ ስልጠናዎችን መስጠታቸውን  አውስተዋል፡፡
ኮሚሽኑ  በቀጣይ ከደቡብ ኮሪያ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ኅብረት ጋር በአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችል የውል ስምምነት ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡
የህግ ታራሚዎችን አምራችና ሕግ አክባሪ ዜጎች ሆነው እንዲወጡ የኮሚሽኑን አመራሮች ባለሙያዎች አቅም መጎልበት ይገባዋል ያሉት ኮሚሽነር ጀኔራሉ የአዕምሮ ውቅር ስልጠና ተቋሙ ለአባሎች በሚሰጠው የመደበኛ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ለማካተት ይሰራል ብለዋል፡፡
የኮሪያ ዓለም አቀፍ ወጣቶች ኅብረት ም/ፕሬዚዳንት ቹይ ጆኒ በኩላቸው ኅብረቱ ለኮሚሽኑ አመራርና ሠራተኞች የሚሰጠውን ስልጠና አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡ 
ኅብረቱ ከኮሚሽኑ ጋር ያለውን ግንኙነት መደበኛ በሆነ መልኩ ለማስቀጠል በውል ማሰሩን የተናገሩት ም/ፕሬዚዳንት የአዕምሮ ውቅር ስልጠና ለሁሉም የተቋሙ ሰራተኞች ለመስጠት ከኮሚሽኑ ጋር በትብብር እንደሚሰሩም አስገንዝበዋል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

24 Dec, 06:53


የድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል የሕግ ታራሚዎች የማረምና ማነጽ ስራ ከምንጊዜውም በላይ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገለፀ፡፡
ድሬዳዋ- ታህሳስ 15/2017 ዓ.ም (የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
በፌዴራል ማረሚያ ቤት የድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል የሕግ ታራሚዎችን አርሞና አንጾ ለማውጣት የቀለም ትምህርትና ልዩ ልዩ ስልጠናዎችን በመስጠት በተለያዬ ሙያ የሰለጠኑ ታራሚዎችን በሰለጠኑበት የሙያ መስክ ተደራጅተው እንዲሰሩ እያደረገ መሆኑም ተመላክቷል፡፡
የድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል ዳይሬክተር ረ/ኮሚሽነር ሙላት ጫንያለው እንደገለጹት የሕግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ከወንጀለኝነት አስተሳሰብ ተላቀው አምራችና ህግ አክባሪ ዜጋ እንዲሆኑ ከምንጊዜውም በተሻለ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል፡፡
ለሕግ ታራሚዎች የምክር አገልግሎት፣ የቀለም ትምህርትና የሙያ ስልጠና በመስጠት ታርመውና ታንፀው እንዲወጡ እየተሰራ መሆኑን የሚናገሩት ዳይሬክተሩ ማዕከሉ በእንጨትና በብረታ ብረት ሥራ፣ በፈሳሽ ሳሙና፣ በልብስ ስፌት፣ በፀጉር ሥራ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በምጣድ ሥራ እና በሌሎች የሙያ መስኮች ስልጠና እንደሚሰጥ አስገንዝበዋል፡፡
ስልጠናዎች የሚሰጡት በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ከሚገኙ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጆች እና ከሌሎች ባልድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መሆኑንም ረ/ኮሚሽነር ሙላት ጫንያለው አመላክተዋል፡፡
የድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል የማረም ማነጽና ተሃድሶ ልማት አስተባባሪ ረ/ኢ/ር ዳግም ሰማኸኝ በበኩላቸው የሕግ ታራሚዎች በሰለጠኑበት የሙያ መስክ ተደራጅተው እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡
በማህበር ከተደራጁ የሕግ ታራሚዎች መካከል የብሎኬት፣ የፈሻስ ሳሙና እና የምግብ ሥራ ማህበራት ጎልተው መውጣታቸውን የሚናገሩት አስተባባሪው የታራሚ ምርቶች እንዲሸጡ የገበያ ትስስር መፍጠራቸውን አመላክተዋል፡፡
በፈሳሽ ሳሙና ሥራ ላይ ተሰማርቶ ያገኘነው ታራሚ ወንድምነህ አስማረ ወደ ማረሚያ ቤት ሲመጣም ምንም አይነት ሙያ እንዳልነበረው ገልጾ፤ ማረሚያ ቤት ከገባ በኋላ ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በመጡ አሰልጣኞች በፈሳሽ ሳሙና፣ በርኪና እና በዲቶል አሰራር ስልጠና ከወሰደ በኋላ በማህበር ተደራጅተው እየሠራ መሆኑን አስረድቷል፡፡
የድሬ ማረሚያ ፈሳሽ ሳሙና ማህበር በ33 ሺህ ብር ካፒታል ተመስርቶ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ400 ሺህ ብር በላይ ካፒታሉ መድረሱን የሚናገረው ታራሚ ወንድምነህ የማህበሩ አባላት በየወሩ ከሚያገኙት ገንዘብ 70 ፐርሰንቱን እንደሚቆጥቡ ገልል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

03 Dec, 11:33


የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የውል ስምምነት ተፈራረመ።
አዲስ አበባ- ህዳር 24/2017 ዓ.ም (ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
ኮሚሽኑ በዛሬው ዕለት 19 አንቀጾችን የያዘ እና በተለያዩ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር ተፈራርሟል።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ስምምነት ሰነዱን አስመልክተው እንደተናገሩት ሁለቱ የፖሊስ ተቋማት ያደረጉት ስምምነት የፍትህ ሥርዓቱን በማረጋገጥ በሀገራችን ላይ የመጣውን ውጤታማ ለውጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ያስችላል ብለዋል።
የተካሄደውን የውል ስምምነት ዓላማ ለማሳካት የሁለቱ ተቋማት አቻ መምሪዎች በቅርበት ይሰራሉ ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ የተልዕኮ አፈፃፀሙን በ 3 ወር አንድ ጊዜ በመገምገም የሚደረገው ተቋማዊ የትብብር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቀዋል፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ለፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ የትብብር ስራው በሕጋዊ ሰነድ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ቀጣይነት ያለው እና ውጤታማ የፍትህ ሥራዎችን በጋራ ለማከናወን ያስችላል ብለዋል።
ተቋሙ በፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት የሚላኩ የህግ ታራሚዎችን እና የቀጠሮ እስረኞችን በመቀበል አምራችና ሕግ አክባሪ ዜጎች ሆነው እንዲወጡ የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር ያለውን የትብብር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮሚሽነር ጄኔራሉ አመላክተዋል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የማረሚያ ፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ላይ እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡
የስምምነት ሰነዱ የተፈፃሚነት ወሰን ሁለቱ ተቋማት በህግ የተሰጣቸው ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት በማድረግ የጋራ እና የተናጠል ሥራዎችን በመለየት ተግባራዊ እንደሚሆን በስምምነቱ ወቅት ተመላክቷል::

Federal Prison Commission-Ethiopia

30 Nov, 14:16


በዕለተ ዕሁድ ከቀኑ 9 ስዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን!

Federal Prison Commission-Ethiopia

29 Nov, 14:59


የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ ቤተ - መዛግብትና ቤተ - መጽሐፍት አገልግሎት ጋር በመተባበር በዝዋይ ማረሚያ ማዕከል የንባብ ሳምንትን አስጀመረ።
ባቱ- ህዳር 20/2017 ዓ.ም (ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
ኮሚሽኑ ህዳር 20/2017 ዓ/ም የንባብ ሳምንትን ከኢትዮጵያ ቤተ - መዛግብትና ቤተ - መጽሐፍት አገልግሎት ጋር በመተባበር '' የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት '' በሚል መሪ ቃል በዝዋይ ማረሚያ ማዕከል አስጀምሯል።
የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ፍቅሬ አቡዬ በ የመክፈቻ ንባ ሳምንት ማስጀመርያ ስነ- ስርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የንባብ ሳምንት በማረሚያ ቤት መከበሩ ትልቅ ትርጉም አለው ፤ መጽሐፍት የህግ ታራሚዎችን አመለካከትና ባህሪ ከማሻሻል በተጨማሪ የነገ ተስፋቸውን ለመንደፍ ያስችላል፤ብለዋል።
የህግ ታራሚዎች ለራሳቸውና ለሀገራቸው የሚጠቅሙ ዜጎች ሆነው እዲወጡ ለማድረግ የማረሚያ ማዕከሉ ቤተ መጻፍት ከጊዜ ወደ ጊዜ በአግባቡ እየተደራጀ ነው፤ ያሉት ም/ኮማንደር ፍቅሬ አቡዬ የኢትዮጵያ ቤተ - መዛግብትና ቤተ - መጽሐፍት አገልግሎት የከፍተኛ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ቤተ - መዛግብትና ቤተ - መጽሐፍት አገልግሎት ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ አባተ ካሳው በበኩላቸው ተቋሙ የማረሚያ ማዕከሉን ቤተ መጽሐፍ በማደራጀት በኩል ድጋፍ ሲደርግ መቆየቱን አስታውሰው ፤ እየተከበረ ያለውን የንባብ ሳምንት ምክንያት በማድረግ 4 መቶ ሺህ ብር ግምት ያላቸውን 1300 የተለያዩ መፅሐፍት ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።
አቶ አባተ አክለውም የህግ ታራሚዎች ከማረሚያ ቤት ሲወጡ የሚገጥማቸውን መደበኛ ኑሮ በማሸነፍ እራሳቸውን እንዲችሉ መፅሐፍ አምባቢ መሆን አለባቸው ፤ ይህንን ተልዕኮ እውን ለማድረግ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጽሐፍት አገልግሎት የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል፤ ብለዋል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ አዝመራ አብደታ በበኩላቸው በፍርድ ቤት ውሳኔ ወደ ማረሚያ ቤት የሚላኩ የህግ ታራሚዎችን በመቀበል ደህንነታቸውን ከማረጋገጥ በተጨማሪ መሰረታዊ ፍላጎታቸውን በማሟላት የትምህርትና ስልጠና አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን አንስተዋል።
ለትምህርትና ስልጠና ተልዕኮን ለማሳካት የመፅሐፍት ሚና ትልቅ ነው፤ ያሉት መሪ ስራ አስፈጻሚው የህግ ታራሚዎች ለንባብ ትኩረት በመስጠት የባህሪ ለውጥ እንዲያመጡ አሳስበዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ብርጋዴር ጄኔራል ካሳዬ ጨመዳን ጨምሮ ሌሎች ደራሲዎች እና ጋዜጠኞች በመገኘት የህይወት ተሞክሯቸውንአጋርተዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን 30 ለሚሆኑ ለፋይናንስ፣ ሰው ሃብት ፣ መዝገብ ቤትና ተያያዥ ሙያ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች በሠነድ እና መዝገብ ምንነት፣ አያያዝ እና ጠቀሜታ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።

Federal Prison Commission-Ethiopia

26 Nov, 07:41


17/03/2017 ዓ.ም
የህግ እሰራኞች ተረጋግተው የፍርድ ሂደታቸውን እንዲከታተሉ እና አርሞና አንጾ ለማውጠት በመዝናኛ መስክ ትኩራት ተሰቶ መስረት እንዳለበት የቀጠሮ ማረፊያ ማዕከል አመራሮችና አባሎች ገለፁ፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ሙዚቃና ቲያትር ቡድን በቀጠሮ ማረፊያ ማዕከል በእስር ላይ ለሚገኙ እስራኞች በየዞኑ በመግባት ለ 3 ተከታታይ ቀናት አዝናኝ እና አስተማሪ የኪና ጥበብ ስራዎችን በባህላዊና በዘመናዊ ባንድ ታጅቦ አቅርቧል፡፡
ለህግ እስረኞች የኪና ጥበብ ስራው በየዞኑ እንዲቀርብላቸው የማስተባባር ስራ እየሰሩ ያገኜናቸው የቀጠሮ ማረፊያ ማዕከል የማረም ማነጽና ተሀድሶ ልማት አስተባባሪ ዋ/ኢ/ርአሸናፊ አሰፋ እንደተናገሩት እስረኞችን በማዝናናት እያስተማሩ፣ አርሞና፣አንጾ መልካም እና አምራች ዜጋ አድርጎ ለማውጣት የመዝናኛ መስክ ላይ ትኩራት ሰጥቶ መሰረት እንዳለባት አስገንዝበዋል፡፡
በኪነ ጥበብ መዝናኛ ላይ ስሳተፉ ካገኘናቸው የህግ እስራኞች መካካል ጀንቦ ብርሀኔ በማረፊያ ማዕካሉ የሚዘጋጁ የእስፖርት እና የሙዚቃ ስራዎች ጭንቀታቸውን ከማስወገድ በተጨማሪ ቀሪ የዕስር ጊዜቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ለማሳለፍ እንደሚረዳቸውና እስረኛው ያለውን ችሎታ ለማውጣት ጥሩ ጥቅም እንዳለው ተናግሮዋል፡፡
መረጃው የማዕከሉ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

20 Nov, 12:01


ለፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ስትራቴጂክና ክፍተኛ አመራሮች የሥራ ላይ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መሰጠት ተጀመረ፡፡
ቢሾፍቱ- ህዳር 11/2017 ዓ.ም (ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
ኮሚሽኑ ከህዳር 11/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀናት ለስትራቴጅክ አመራሮች፣በከፍተኛ አመራርነት ደረጃ የሚገኙ የማዕከላት ኃላፊዎች፣የየስራ ክፍል ዳይሬክተሮች እና ጽ/ቤት ኃላፊዎች እየተሳተፉበት የሚገኝ ስልጠና ቢሾፍቱ በሚገኘው በኢትዮጵያ ስራ አመራር ኢንስትትዩት መሰጠት ተጀምሯል፡፡
በስልጠና የመክፈቻ ሥነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የፍትህ ሚኒስቴር የተጠሪ ተቋማት ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኡመድ ኡጁሉ በአደረጉት ንግግር ባለፉት የለውጥና የስኬት ዓመታት ከተመዘገቡ ዘርፈ ብዙ ውጤቶችና የሃገራዊ ለውጡ ቱሩፋቶች መካከል የፀጥታና የፍትህ ተቋማት ሪፎርም እንደሚገኙበት አመላክተዋል፡፡
ኮሚሽኑ ከፍትህ ዘርፉ የ10 ዓመት ስትራጂክ ዕቅድ የተቀዳ እና አሁን ካለበት ችግር ለመውጣት የሚያስችለውን የ6 ዓመት ተቋማዊ የሪፎርም ዕቅድ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር መግባቱን የተናገሩት አቶ ኡመድ ኡጁሉ በኮሚሽኑ የ6 ዓመታት ዕቅድ ውስጥ ከሰፈሩት ዘጠኝ አምዶች መካከል ለኮሚሽኑን አመራርና ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት አንዱ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
ለኮሚሽኑ ከፍተኛና ስትራቴጂክ አመራሮች መስጠት የተጀመረው የሥራ ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመካከለኛና ለዝቅተኛ እርከን አመራሮች እንዲሁም ለሁሉም ፈፃሚ ሰራተኞች እንደስራ ኃላፊነታቸው ተቃኝቶ እንደሚሰጥ ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል የኑስ ሙሉ በበኩላቸው ኮሚሽኑ ባለፉት አምስት ዓመታት በተገበረው ተቋማዊ ሪፎርም አበረታች ውጤቶች የተገኘ ቢሆንም የተሟላ ተቋማዊ ሪፎርም ማምጣት አለመቻሉን አመላክተዋል፡፡
ባሰለፍነው በጀት ዓመት ኮሚሽኑ ካካሄዳቸው ግምገማዎች በመነሳት የማስተካከያ እርምጃ መወሰዱን ያስታወሱት ኮሚሽነር ጀኔራሉ በተካሄዱ የማስተካከያ እርምጃዎች ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
ለኮሚሽኑ ከፍተኛና ስትራቴጂክ አመራሮች የተዘጋጀው ስልጠና በተቋሙ ውስጥ የሚስተዋሉ የአመራርነት፣ የመልካም አስተዳደርና የሥነ ምግባር ችግሮችን ለማስተካከልና የሃብት ብክነትን ለማስወገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
ስልጠናው በሃገራዊ ህልምና ራዕይ፣ በመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጂ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ ጽንሰ ሃሳብና ተግባራዊ እርምጃዎች፣ በፊዚካል ሳይበር ሴኩሪቲ ምህዳር፣ በመንግስት ግዥ ሃብትና በጀት አስተዳደር ስርዓት፣ በተቋማት ግንባታና የአመራር ሥነ ምግባር እምርታ፣ በመሪነት አዕምሯዊ ውቅር እና ከስትራቴጂክና ከፍተኛ አመራሮች በሚጠበቀው ሚና ላይ ትኩረት በማድረግ እንደሚሰጥ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡
የመጀመርያው ቀን ስልጠና ከአለም አቀፍ የወጣቶች ፌዴሬሽን በመጡ ሙህር የልቦና ውቅር(Mind Set) በሚል ርዕሰ ጉዳይ ተጀምሯል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

19 Nov, 17:29


የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ስትራቴጂክና ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያን ጎበኙ፡፡
አመራሮቹ ሥራዎች በሚመለከተው ባለሙያ ከተሰሩ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ከጉብኝቱ መገንዘባቸውንም ተናግረዋል፡፡
ቢሾፍቱ- ህዳር 10/2017 ዓ.ም (ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
የስትራቴጅክ እና ከፍተኛ አመራሮችን ጉብኝት የመሩት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል የኑስ ሙሉ እንዳሉት የኢትዮጵያን አየር ኃይል ጠቅላይ መመሪያን ቀደም ሲል እንደሚያውቁት አስታውሰው፤ ቀድሞ ከሚያውቁት ብዙ ነገር ብዙ አዳዲስ ነገር ተጨምሮ እና ተሻሽሎ እምርታዊ ለውጥ መታየቱን ተናግረዋል፡፡
የኮሚሽኑ አመራሮች የኢትዮጵያን አየር ኃይል እንዲጎኙ የተፈለገበት ዋና ዓላማ ሁሉም አመራር በየተመደበበት ቦታ ሙያን ማዕከል በማድረግ ከተሰራ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምን ያህል ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ለማስገንዝብ መሆኑንም ኮሚሽነር ጀኔራሉ አስረድተዋል፡፡
የኮሚሽኑ የፋይናንስና የሰው ኃብት ሥራ አመራር ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ጀኔራል ደስታ አስመላሽ በበኩላቸው በጉብኝቱ ሃገራችን ምን ያህል ሃብትና አቅም እንዳላት ማየታቸውን ገልፀዋል፡፡
የገቢው ውበት ሠራተኞች ደስ ብሏቸው ሥራቸውን ማከናወን እንደሚያስችላቸው የተናገሩት ም/ኮሚሽነር ጀኔራሉ በጉብኝቱ ከ1921ዓ.ም. ጀምሮ ያለውን የተቋሙን ታሪክና በአሁኑ ሰዓት እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡
የኮሚሽኑ የጥበቃና ደህንት ዳይሬክተር ም/ኮሚሽነር አለባቸው ጥጋቡ በሰጡት አስተያየት የጠቅላይ መምሪያው ከሃገራችን አልፎ ለአህጉራችን ምሳሌ እንደሚሆን የተናገሩት ዳይሬክተሩ ሥራዎች በሚመለከታቸው ባለሙያ ከተሰሩ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል መገንዘባቸውን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮሎኔል መኳንት ደሳለኝ በበኩላቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኢትዮጵያ ሕዝብ ተቋም በመሆኑ በራቸውን ክፍት በማድረጋቸው ባሳለፍነው በጀት ዓመት ከ29 ሺህ በላይ ከሕፃናት እስከ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ድረስ መጎብኘታቸውን አስገንዝበዋል፡፡
ለታላቅ ሀገር ታላቅ አየር ኃይል የሚል መሪ ቃል አንግበው ፕሮፌሽናል የሆኑ ሙያተኞች የሚወጡበት ተቋም እንዲሆን በመስራታቸው ትልቅ ለውጥ ማምጣታቸውንም ኮሎኔሉ ተናግረዋል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

19 Nov, 05:20


ጠንካራ ሀገር የሚገነባው ጠንካራ ተቋማት ሲኖሩ ነው ፤ ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ለተቋሙ የፖሊስ አባላትና ሰራተኞች በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ሰጠ።
ኮሚሽኑ ለተቋሙ የፖሊስ አባላትና ሰራተኞች ''የህልም ጉልበት ፡ ለእምርታዊ ዕድገት!"በሚል ርዕሰ ጉዳይ ሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሚሽኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ስልጠና ሰጥቷል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ በስልጠናው የመክፈቻ ስነ ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ሁሉም የፖሊስ አባልና ሰራተኛ አለም አቀፋዊና ሀገራዊ ሁኔታዎችን በመረዳት የተቋሙን ተልዕኮ እውን ለማድረግ በታማኝነት እና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል።
ከዚህ በፊት " ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል ርዕስ የተሰጠው ሀገራዊ ስልጠና ውጤት ማምጣቱን ያስታወሱት ኮሚሽነር ጄኔራሉ የኮሚሽኑ አመራር፣ አባላትና ሰራተኞች በስልጠና የታገዘ የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነታቸውን በማጠናከር የተቋሙን አላማ ከማሳካት ባሻገር ለሀገር ግንባታ በሚደረገው ጥረት ላይ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማድረግ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
የስልጠና መድረኩን የመሩት የኮሚሽኑ የፋይናንስ እና የሰው ኃብት ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ጄኔራል ደስታ አስመላሽ በበኩላቸው ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ እንደ ሀገር ባለፉት 6 ዓመታት በርካታ ውጤታማና ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወናቸውን አመልክተዋል።
ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራሉ አክለውም መንግስት በለውጥ ሂደቱ ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት በቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ በስፋት እየሰራ መሆኑን ተናግረው ሁሉም የኮሚሽኑ አባላትና ሰራተኞች አለም አቀፋዊ እና ቀጠናዊ ሁነቶችን ከመረዳት በተጨማሪ በተቋማችን ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመለየት ስር ነቀል ለውጥ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል።
በስልጠና መድረኩ ከሰልጣኞች በርካታ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በም/ኮሚሽነር ጄኔራሉ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በመድረኩ የኮሚሽኑ የሙዚቃና ትያትር ቡድንም የተለያዩ ሀገራዊ ይዘት ያላቸውን የኪነጥበብ ስራዎች በማቅረብ ለስልጠናው ስኬት ሚናውን ተወጥቷል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

13 Nov, 05:27


የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የውል ስምምነት ተፈራረመ።
ኮሚሽኑ ያስጀመራቸውን የግንባታ ፕሮጀክቶች በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እና በሌሎች ሥራዎች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችል የውል ስምምነት ሰነድ ህዳር 03/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተፈራርሟል።
የጋራ ስምምነቱን አስመልክተው የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ እንደተናገሩት በተቋሙ ተጀምረው ሳይጠናቀቁ ለረዥም ዓመታት የቆዩ የግንባታ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ገልፀው፤ የኮሚሽኑን ተልዕኮ በሚያሳኩ ተግባራት ላይ በትብብር መስራት አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
የሀገራችን ማረሚያ ቤቶች ለዓለም አቀፍ እና ለሀገር ውስጥ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና ድርጅቶች ክፍት መሆናቸውን የተናገሩት ኮሚሽነር ጄኔራሉ ዓለም አቀፍ ዝቅተኛ መስፈርቶችን በማሟላት ለህግ ታራሚዎች እና ለቀጠሮ እስረኞች ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ኮሚሽኑ የሚያደረገውን ጥረት እንዲሳካ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ተወካይና የአስተዳደር እና ልማት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተመስገን ወንድሙ በበኩላቸው ኮሚሽኑ የሚሰራቸውን ፕሮጀክቶች የሲቪል፣ ኤሌክትሪካል፣ ኤሌክትሮ ሜካኒካልና ሌሎች ክፍተቶች በጥናት ከመለየት በተጨማሪ በአጪር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መፍትሄ አመላካች ሙያዊ የምክር አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል፡፡
ዩኒቨርስቲው ከማማከር በተጨማሪ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በስራ ላይ ስልጠና፣ በመማር ማስተማር አገልግሎት፣ በሳይት ልየታ፣ በታራሚዎች መልሶ የመቀላቀል ቅድመ ሁኔታዎች እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ዶ/ር ተመስገን ወንድሙ ተናግረዋል።
ከዛሬው የጋራ የውል ስምምነት በፊት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የግንባታ አማካሪ ቡድን አባላት በጋራ በሚሰሩ መሰረታዊ ኃሳቦች ዙርያ ውይይት ማረጋቸው ይታወሳል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

11 Nov, 14:30


02/03/2017 ዓ.ም
በፌዴራል ማረማያ ቤት ኮሚሽን የቀጠሮ ማረፊያ ማዕከል የተቋሙን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ።
የቀጠሮ ማረፊያ ማዕከል የተቋሙን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ከሌሎች የፀጥታ ተቋማትና የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገለጸ።
የቀጠሮ ማረፊያ ማዕከል ዳይሬክተር ኮማንደር ዓለምሰገድ አስገዶም ለዝግጅት ክፍላችን በሰጡት ማብራሪያ የማእከሉን የውስጥ እና የውጭ ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከአቃቂ ቃሊቲ ፖሊስ መምሪያ እና ከአካባቢው የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ብለዋል።
የማዕከሉን የውስጥ ሠላምና ደህንነት ለማስቀጠል ከፖሊስ አባላት በተጨማሪ የቀጠሮ እስረኞች የሠላም ተባባሪ በመሆናቸው ውጤታማ መሆን ተችሏል ብለዋል፡፡
የቀጠሮ ማረፊያ ማዕከል የጥበቃ ደህንነትንና ትጥቅ አስተባባሪ ዋና ኢንስፔክተር ንጉሴ ጉርሜሣ በበኩላቸው የሕግ እስረኞችን ደህንነት ለማረጋገጥ ወደ ፍርድ ቤት እና ህክምና በሚደረገው ምልልስ ችግር እንዳይከሰት ተገቢውን እጀባ እና ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
የህግ እስረኞች የፍርድ ቤት ቀጠሮ እንዳይስተጓጎል ለማድረግ ከፌዴራል ፖሊስ ጋር በመተባበር የእጀባ ስራ እንደሚከናወንም አስተባባሪው ገልፀዋል።

Federal Prison Commission-Ethiopia

10 Nov, 22:44


https://youtu.be/77JFiXEy3-k?si=Zm2BpIqdA3fcPJMC

Federal Prison Commission-Ethiopia

07 Nov, 11:50


28/02/2017 ዓ.ም
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ጋር በግንባታ ፕሮጀክት ስራዎች ዙርያ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት አደረገ፡፡
ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም በዋናው መ/ቤት የኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራሮች እና የዩኒቨርስቲው የፕሮጀክት አማካሪዎች ቡድን ውይይት አድርገዋል፡፡
ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ የጀመራቸውን ትልልቅ ፕሮጀክቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ወደ አገልግሎት ለማስገባት እንዲሁም ዋናውን መ/ቤት ጨምሮ በቀጣይ በሚሰሩ በርካታ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክቶች ዙርያ፣በቴክኖሎጂ ሽግግር፣በሰው ኃይል ስልጠና እና በፕሮጀክት ጥገናዎች ላይ ትኩረት በማድረግ የካበተ ልምድ ባለቤት የሆነው የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሮጀክት አማካሪዎች ቡድን ለከፍተኛ አመራሮች እና ለኮሚሽኑ የፕሮጀክት ባለሙያዎች ገለጻ አድርጓል፡፡
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ኮሚሽኑ የሚሰራቸውን ፕሮጀክቶች በአማካሪነት በመያዝ ውጤታማ ስራ መስራት የሚያስችለውን የጋራ ስምምነት በአጭር ቀናት ውስጥ ተፈራርሞ ወደ ስራ እንደሚገባ በውይይቱ ወቅት ተገልጧል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

06 Nov, 13:00


27/02/2017 ዓ.ም
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከUNODC (United Nations Office on Drugs and Crime)ጋር ሲሰራ የቆየውን የትብብር ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ፡፡
የኮሚ ሽኑ ከፍተኛ አመራሮች አዲስ ከተመደቡት የምስራቅ አፍሪካ የUNODC ተወካይ ሚስ አሽታ ሚታል እና የልኡካን ቡድናቸው ጋር በጋራ እየሰሩባቸው ባሉት እና ወደፊትም ሊሰሩባቸው በሚችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሚሽኑ ዋና መስሪያ ቤት ውይይት አካሂደዋል፡፡
በጋራ ውይይት መድረኩ ላይ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ እንደተናገሩት በፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት ወደ ማረሚያ ቤት የሚላኩ የቀጠሮ እስረኞችን እና የህግ ታራሚዎችን በመቀበል ሰብአዊ ክብራቸውን ከመጠበቅ በተጨማሪ መሰረታዊ ፍላጎታቸውን በማሟላት የማረም ማነጽ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል፡፡
በሲንጋፖር እና ኬንያ ማረሚያ ቤቶች ላይ የሚሰሩ ተሞክሮዎችን በመቅሰም በሀገራችን የማረሚያ ተቋማት ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ይሰራል ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ ከUNODC (United Nations Office on Drugs and Crime)ኢትዮጵያ እና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር ያለው ዘርፈ ብዙ የትብብር ስራዎችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል፡፡
በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የUNODC ተወካይ ሚስ አሽታ ሚታል በበኩላቸው በፌዴራል እና ክልል ደረጃ የሚገኙ የማረሚያ ተቋማትን ለማሻሻል የሚደረገው ዘርፈ ብዙ ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙትን የማረሚያ ተቋማት ለውጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ከመስጠት በተጨማሪ አለማቀፋዊ ተሞክሮዎችንና ድንጋጌዎችን በማስፋት በኩል በትኩረት እንደሚሰራ የገለጹት ሚስ አሽታ ሚታል የህግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ውስጥ በሚኖራቸው ቆይታ እንደ ወንጀል ደረጃቸው አማራጭ ቅጣቶችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የፋይናንስና የሰው ኃብት ልማት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል ደስታ አስመላሽ እንደገለጹት ኮሚሽኑ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የኮሚሽኑን አዋጅ ከማሻሻል ጀምሮ ትልልቅ የሪፎርም ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸው፤ UNODC ኢትዮጵያ ሲያደርገው የነበረው ድጋፍ እና ክትትል ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራሉ አክለውም የህግ ታራሚዎች በማረሚያ ማዕከላት ውስጥ በሚኖራቸው ቆይታ በሰሩት የወንጀል ደረጃ ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ብሎ በመመደብ የማረም ማነጽ አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልጸው፤ ኮሚሽኑ አዲስ ከተመደቡት የምስራቅ አፍሪካ የUNODC ኢትዮጵያ ተወካይ ጋር የነበረውን ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

04 Nov, 10:51


https://www.youtube.com/watch?v=YmFLVU4x3SM

Federal Prison Commission-Ethiopia

29 Oct, 11:24


19/02/2017 ዓ.ም
በሀገራዊ የሪፎርም ውጤቶች እና ተጨባጭ መረጃዎች ላይ ተገቢውን ግንዛቤ መውሰድ ያስፈልጋል፤ ም/ኮሚሽነር ጄኔራል ደስታ አስመላሽ፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን አመራሮች እና ሰራተኞች በሀገራዊ የ100 ቀናት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኮሚሽኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በ2017 በጀት ዓመት ሀገራዊ የ100 ቀናት እቅድ አፈጻጸም ላይ በተቋሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ውይይት አካሂደዋል፡፡
ሀገራዊ የ100 ቀናት ዕቅድ አፈጻጸም መድረኩን የመሩት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የፋይናስና ሰው ሃብት ልማት ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ጄኔራል ደስታ አስመላሽ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለጹት በሀገራችን እየተካሄደ የሚገኘውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የሪፎርም ውጤቶች ላይ እንደ ዜጋም ሆነ እንደ መንግስት ሰራተኛ የማረሚያ ቤት ኮሚሽን አመራሮች፣አባላት እና ሰራተኞች ተገቢውን ግንዛቤ በመውሰድ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ የኮሚሽኑን አስተዋጽኦ ከፍ ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡
በሀገራችን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው የሪፎርም ስራ አካታችና ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት እውን እንዲሆን ከማድረግ በተጨማሪ የተሻለ የመንግስት ገቢ እንዲኖር እና የኢንቨስትመንት ውጤታማነት እንዲረጋገጥ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው፤ያሉት ም/ኮሚሽነር ጄኔራሉ
ምክትል ኮሚሽር ጄኔራል ደስታ በመድረኩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ አለም አቀፍ የፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ አዝማሚያዎች በሀገራችን ላይ የሚያሳድሩትን ተጽዕኖ በመረዳት እና በባለሙያዎች ሰፊ የሆነ ሳይንሳዊ ጥናት በማካሄድ ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና ሪፎርም በመስራት ወደ ተግባር መገባቱን አስረድተዋል፡፡
የ2017 በጀት አመት የመጀመሪውን ሀገራዊ የ100 ቀናት ሪፎርም አፈጻጸም ያቀረቡት የኮሚሽኑ የስትራቴጅክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ ወንድሙ በበኩላቸው የአለም አቀፉ እና የምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ አዝማሚያ በሀገራችን ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ መኖሩን ተናግረው እንደሀገር በተያዘው የ2017 በጀት አመት የሀገራችን የእድገት ትንበያ 8.4% መሆኑን አመላክተዋል፡፡
አቶ ቴዎድሮስ ወንድሙ አክለውም የሀገራችን የእድገት ዕውን እንዲሆን መንግስት በኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝም ፣ በኤክስፖርት እና በስራ እድል ፈጠራ ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡
ከገለጻው በኋላ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ከተሳታፊዎች እና ከመድረክ መሪው ማብራሪያ በመስጠት እና የጋራ መግባባት በመፍጠር መድረኩ ተጠናቋል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

23 Oct, 11:25


13/02/2017 ዓ.ም
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ስፖርት ክለብ በያዝነው በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ተገቢውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የኮሚሽኑ ስፖርት ክለብ በ2016 ዓ.ም ያመጣቸውን ውጤቶች በማስቀጠል በያዝነው በጀት ዓመት ተወዳዳሪ ክለብ ለመሆን በአትሌቲክስ፣ በቦክስ፣ በወንዶች የእጅ ኳስና በሴቶች ቮሊቮል ተገቢውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡
የስፖርት ክለቡ ያለውን ዝግጁነት ለዝግጅት ክፍላችን ማብራሪያ የሰጡት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ስፖርት ክለብ ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ወንድወሰን ማንደፍሮ እንደተናገሩት ክለቡ በ2016 ዓ.ም በተሳተፈባቸው የሀገር ውስጥ ውድድሮች 9 ዋንጫ፣ 33 ወርቅ፣ 23 ብር፣ 35 ነሃስ እና 43 ዲፕሎማ በማምጣት ከ2015 በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡን አመልክተዋል፡፡
የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባካሄዳቸው የ1ኛ ዲቪዚዮን ውድድሮች 2ኛ ደረጃ በመውጣት ዕውቅና ማግኘቱንም አስታውሰዋል፡፡
የኮሚሽኑ ስፖርት ክለብ በተሳተፈባቸው ዓለም አቀፍ ውድድሮች 2 ዲፕሎማ፣ 3 የወርቅ እና 4 የነሃስ ሜዳሊያ ማምጣቱን የገለጹት ም/ኮማንደር ወንድወሰን ማንደፍሮ በእንጻሩ የአትሌቶች ፍልሰትና የበጀት እጥረት በስፖርት ክለቡ ውጤት ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በያዝነው በጀት ዓመት የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ አስፈላጊውን የሰው ኃይል ቅጥር ከመፈጸም በተጨማሪ ለአትሌቶች የሚሰጠው የላብ መተኪያ በጀት በማስተካከል ችግሩን በመቅረፍ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከኮሚሽኑ ስትራቴጅክ አመራር ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽንን የስፖርት ክለብ በሃገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ውድድሮች ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የኮሚሽኑንና የሀገራችንን ገጽታ ለመገንባት በትኩረት ይሰራል ያሉት ም/ኮማንደር ወንድወሰን ማንደፍሮ ለክለቡ መጠናከር የሚመለከታቸው አካላት ድጋፍና ክትትል እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Federal Prison Commission-Ethiopia

20 Oct, 18:55


https://youtu.be/Phk3U9HHkiU?si=oX3c-8zsL-4aIZN-

Federal Prison Commission-Ethiopia

20 Oct, 12:37


10/02/2017 ዓ.ም
የማረሚያ ተቋማት የህዝብ ግንኙነት መዋቅር የሚድያ አማራጮችን አሟጦ በመጠቀም የመዋቅሩን ተልዕኮ በአግባቡ ወደ ህዝብ ተደራሽ ማድረግ ይጠበቅበታል፤ም/ኮሚሽነር ጄኔራል ሉባባ ጀማል፡፡
የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የጋራ ፎረም እና የግምገማዊ ስልጠናውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል ተወካይ እና የተሐድሶ ልማትና የማረም ማነጽ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ጄኔራል ሉባባ ጀማል እንደተናሩት የማረሚያ ተቋማት የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች የተለያዩ የሚድያ አማራጮችን አሟጦ በመጠቀም የመዋቅሩን ተልዕኮ በአግባቡ ለኅብረተሰቡ ተደራሽ የማድረግ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ይገባዋል ብለዋል፡፡
የፌዴራልና የክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገቢውን ሙያዊ ስልጠና ከመስጠት በተጨማሪ የጋራ ፎረም በመመስረት ተመሳሳይ አሰራሮችን በማጎልበት የተቋሙን ተልዕኮ የሚያሳኩ መረጃዎችን ለአድማጭ ተመልካች ማድረስ ይገባል ብለዋል፡፡
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የኮሚሽነር ጄኔራል ጽ/ቤት ኃላፊና ስታፍ ዳይሬክተር ም/ኮሚሽነር መኮንን ደለሳ በበኩላቸው ማረሚያ ቤት በፍትህ ስርዓት ውስጥ የሚያልፉ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮችን አካቶ የሚሰራ ተቋም መሆኑን አንስተው ለዚህ ደግሞ የህዝብ ግንኙነት መዋቅሩ የጀርባ አጥንት መሆኑን ተረድቶ ከፌዴራል እስከ ክልል በተናበበ መልኩ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
በመድረኩ ዓላማ ላይ ገለጻ ያደረጉት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ አቶ ገረመው አያሌው መድረኩ ከፌዴራል እስከ ክልል የተደራጀ እና የተመጋገበ፤በዕውቀት ላይ የተመሰረተ የህዝብ ግንኙነት ስራ ለመስራት እንዲቻል ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ ነው ብለዋል፡፡
ስራ አስፈጻሚው አክለውም ወቅቱ የደረሰበትን የዲጂታል ሚዲያ እና ዋና ዋና ሀገር አቀፍ እና ክልላዊ ሚዲያዎችን በአግባቡ በመጠቀም ከተቋሙ አንጻር በህዝብ ዘንድ የሚታየውን የመረጃ ግልጸኝነት ችግር እና ብዥታ መፍታት ይገባል ብለዋል፡፡

ፎረሙ ከጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 2 ቀናት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩ የኮሙዩኒኬሽን ቼክ ሊስት፣የመረጃ ነጻነት አዋጅ፣ማሕበራዊ ደህረገጸችን የመጠቀም፣የማበልጸግ እና የመቆጣጠር ቴክኒክ ፣ከብሮድካስት እና ከህትመት ሚዲያዎች ጋር ሊኖር ስለመገባው የስራ መስተጋብር ከመንግስት ኮሙዩኒኬሽን፣ከአዲስ አበባ ዩኒቭርስቲ፣ከፋና ብሮድካቲንግ ኮርፖሬት እና እንባ ጠባቂ ተቋም በመጡ የስራ ኃላፊዎች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡የአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት፣የሚዲያ ዳሰሳ ጥናት በስራ ኃፊዎች የቀረቡ ሲሆን የፌዴራል ማሚያ ቤት ህዝብ ግንኙነት አፈጻጸም እና የከተመረጡ የህዝብ ግኙነት ክፍሎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
ከስልጠና እና ፎረሙ ተሳታፊዎች መካከል ዋ/ኢንስፔክተር ካምላክ ምህረት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ሳጅን ኤልያስ በዙ ከደቡብ ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት ስልጠናው መሰጠቱ በሀገራችን በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ተቀራራቢና በዕውቀት ላይ የተመሰረተ መረጃ ለማሰራጨት ጠቃሚ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ማረሚያ ቤቶች በፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት የሚላኩ የሕግ ታራሚዎችን በመቀበል አርሞና አንጾ ከማውጣት በተጨማሪ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ያከናውናል ያሉት የስልጠና ተካፋዮች በማረሚያ ቤት የተከናወኑ ተግባራትን ለኅብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ለሙያተኞች ተገቢው ስልጠና መስጠት፣ ፕሮፌሽናል ባለሙያችን መመደብ እና የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ማሟላት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

2,511

subscribers

6,080

photos

9

videos